TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ችሎት !

በእነ አቶ እስክንድር ነጋ የክስ መዝገብ ጉዳዩን በዋነኛነት የያዘው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው ችሎት የምስክር አቀራረብ ሒደት ላይ የግራና ቀኝ የህግ ክርክር በመመርመር ፍ/ቤቱ ውሳኔ ሰጥቷል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዐቃቤ ህግ በእነ እስክንድር ነጋ ላይ እንዲመሰክሩ ያዘጋጃቸው 16 ምስክሮች #በግልጽ_ችሎች እንዲመሰክሩ ወስኗል ።

የከፍተኛው ፍርድ ቤት አንደኛ የጸረ ሽብር እና ህገ መንግስታዊ ጉዳዮች ችሎት ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 22 ቀን 2013 ዓ.ም ውሳኔውን ያሳለፈው፤ ምስክሮች “ለደህንነታቸው” ሲባል በዝግ ችሎት ከመጋረጃ ጀርባ እንዲሰሙ በዐቃቤ ህግ በኩል የቀረበውን ጥያቄ በተከሳሾች እና በደጋፊዎቻቸው በኩል ለዐቃቤ ሕግ ምስክሮች ምንም አይነት በቂ የሆነ በምክንያት እና በእውነት አስረጂ የሆኑ የደህንነት ስጋት አላገኘሁም ፤ በማለት ፍ/ቤቱ የዐቃቤ ሕግ የመጋረጃ ጀርባ ምስክርነት ጥያቄ ውድቅ አድርጓል።

የዐቃቤ ሕግ ምስክሮች ሐምሌ 8 እና 9 እንዲሁም ሐምሌ 14 ፣15 እና 16 በአምስት ቀናት ውስጥ እንደሚሰማ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል ።

መረጃው የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ባልደራስ) ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፅ ነው።

@tikvahethiopia