TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
በአዲስ አበባ 29 የቤት አልሚ ኩባንያዎች ቦታቸውን #እንዲነጠቁ ተወሰነ‼️

የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ #ታከለ_ኡማ አስተዳደራቸው ባስጠናው ጥናት መሠረት ዝቅተኛ አፈፃፀም ያስመዘገቡ 29 የቤት አልሚ (‘ሪል ኢስቴት’) ኩባንያዎች ቦታቸው ተነጥቆ በቤቶች ልማትና አስተዳደር በኩል በማኅበር ለሚደራጁ ኗሪዎች እንደሚያስተላለፉ መወሰኑን አስታወቁ።

ዛሬ፣ የካቲት 6 በጽሕፈት ቤታቸው የአጥኚ ቡድኑ ግኝት በቀረበበት ወቅት እንደተገለጸው ጥናቱ በቦሌ፣ በየካ፣ በንፍስ ስልክ ላፍቶ፣ በኮልፌ ቀራኒዮ እና በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተሞች ቤት ለማልማት መሬት የተረከቡ ኩባንያዎች ላይ መካሔዱ ተጠቁሟል። በጥናቱ ውጤት መሰረት በአምስቱ ክፍለ ከተሞች መሬት ከተረከቡት ቤት አልሚ ኩባንያዎች መካከል 19 ኩባንያዎች የተሻለ አፈፃፀም በማስመዝገብ ቤት ገንብተው ለባለ ቤቶቹ ያስረከቡ ሲሆን 52ቱ ኩባንያዎች ደግሞ መካከለኛ አፈፃፀም በማስመዝገብ በተለያዩ የግንባታ ደረጃ ላይ የሚገኙ መሆኑም ታውቋል።

ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ
@tsegabwolde @tikvahethiopia