ኢቦላ‼️
በዲሞክራሲያዊት ኮንጎ ሪፖብሊክ ኢቦላን ለመላከል እየተከናወነ ያለውን ስራ ለጋሾች እንዲደገፉ የአለም ጤና ድርጅት ጠየቀ፡፡
የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር #ቴድሮስ_አድሀኖም የገንዘብ እጥረት ቁልፍ ውጤቶችን እንዳይሸረሸራቸው ስጋት መኖሩን ተናግረዋል፡፡
ከስፍራ ወደ ስፍራ የሚንቀሳቀስ ማህበረሰብ ባለበት አካባቢ ያለው የጤና ስርአት ክፍተት እና የፀጥታ ሁኔታ ሌሎች ፈተናዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
በሀገሪቱ በኢቦላ የተጠቁትን ቡቴምቦና እና ካትዋን ለመመልከት እንዲሁም ከአዲሱ ኘሬዚዳንት ፊሊክስ ተሲኬዳ ጋር ለመነጋገር ቀጠሮ መያዛቸውን ዶክተር ቴድሮስ አስታውቀዋል፡፡
በሀገሪቱ የሚከናወነውን የመከላከል ስራ ለማጠናከር የሚያግዝ የግብአት ድጋፍ መላኩንም አስታውቀዋል፡፡
በኮንጎ የተከሰተውን ኢቦላን ለመከላከል የአለም ጤና ድርጅት ከጠየቀው የ1መቶ 48 ሚሊዮን ዶላር አለም አቀፍ ድጋፍ እስካሁን ያገኘው ከ1ዐ ሚሊዮን ዶላር የዘለለ አይደለም፡፡
በመጨረሻው ምዕራፍ ላይ የደረሰውን ትግል ውጤታማ ለማድረግ የለጋሾች ድጋፍ ለአለም ጤናማነት ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳዩበት እንደሆነ ዶክተር ቴድሮስ አስገንዝበዋል፡፡
ምንጭ፡- ሲጂቲኤን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በዲሞክራሲያዊት ኮንጎ ሪፖብሊክ ኢቦላን ለመላከል እየተከናወነ ያለውን ስራ ለጋሾች እንዲደገፉ የአለም ጤና ድርጅት ጠየቀ፡፡
የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር #ቴድሮስ_አድሀኖም የገንዘብ እጥረት ቁልፍ ውጤቶችን እንዳይሸረሸራቸው ስጋት መኖሩን ተናግረዋል፡፡
ከስፍራ ወደ ስፍራ የሚንቀሳቀስ ማህበረሰብ ባለበት አካባቢ ያለው የጤና ስርአት ክፍተት እና የፀጥታ ሁኔታ ሌሎች ፈተናዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
በሀገሪቱ በኢቦላ የተጠቁትን ቡቴምቦና እና ካትዋን ለመመልከት እንዲሁም ከአዲሱ ኘሬዚዳንት ፊሊክስ ተሲኬዳ ጋር ለመነጋገር ቀጠሮ መያዛቸውን ዶክተር ቴድሮስ አስታውቀዋል፡፡
በሀገሪቱ የሚከናወነውን የመከላከል ስራ ለማጠናከር የሚያግዝ የግብአት ድጋፍ መላኩንም አስታውቀዋል፡፡
በኮንጎ የተከሰተውን ኢቦላን ለመከላከል የአለም ጤና ድርጅት ከጠየቀው የ1መቶ 48 ሚሊዮን ዶላር አለም አቀፍ ድጋፍ እስካሁን ያገኘው ከ1ዐ ሚሊዮን ዶላር የዘለለ አይደለም፡፡
በመጨረሻው ምዕራፍ ላይ የደረሰውን ትግል ውጤታማ ለማድረግ የለጋሾች ድጋፍ ለአለም ጤናማነት ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳዩበት እንደሆነ ዶክተር ቴድሮስ አስገንዝበዋል፡፡
ምንጭ፡- ሲጂቲኤን
@tsegabwolde @tikvahethiopia