TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update እንቦጭ አረምን ለመቆጣጠር የተሰበሰበው 54 ሚሊዮን ብር እስካሁን ሥራ ላይ #አለመዋሉን ሸገር ዘግቧል፡፡ ከአምና ጀምሮ የአማራ ክልል ሃላፊዎች የሚመሩት የጣና ትረስት ፈንድ ተቋቁሞ የገንዘብ ድጋፍ ማሰባሰቡ ይታወሳል፡፡ ቦርዱ እስካሁን በተለያዩ ቸግሮች ሳቢያ ብሩን ፈሰስ ማድረግ አልቻለም ነበር፡፡ በቅርቡ ግን 23 ሚሊዮን ብር ያህል ለመልቀቅ ወስኗል፡፡ ገንዘቡ አረሙን በጉልበታቸው ለሚያሰወግዱ የአካባቢው አርሶ አደሮች ክፍያ፣ ለጀልባ ግዥና ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ለጀመረው አረም የሚበላ ጥንዚዛ ማራባት ሥራ ይውላል፡፡ አሁን እንቦጭ የወረረው የሐይቁ ስፋት 2 ሺህ 300 ሄክታር ያህል ይገመታል፡፡

Via wazemaradio
@tsegabwolde @tikvahethiopia