#update ጠ/ሚር ዶ/ር #ዐቢይ_አሕመድ ከኖርዌይ ጠቅላይ ሚኒስትር ኤርና ሶልበርግ ጋር ዛሬ በጽ/ቤታቸው ተወያዩ። በሁለቱ ሀገራት መካከል የሁለትዮሽ ትብብር እኤአ ከ1995 ጀምሮ የተመሰረተ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያን በአፍሪካ የኖርዌይ ትልቋ አለምአቀፍ ትብብር እንድትሆን አስችሏታል። ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ ይህንኑ ትብብር በማድነቅ የስካንዲኔቪያ አገራትን የ # መደመር ተሞክሮ አገራቱ በጋራ እንዲያድጉ እድል እንደከፈተላቸው አውስተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት እንደገለፀው ይህም ለአፍሪካ ቀንድ ቀጠና ውህደት እንደ ተምሳሌት የሚወሰድ ነው ብለዋል። የኖርዌይ ጠ/ሚኒስትር በበኩላቸው በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን ለውጥና የከባቢው ውህደት ጅማሮዎችን በማድነቅ አገራቸው የምታደርገውን እርዳታ በተለይም በትምህርት ዘርፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል አስታውቀዋል።
ምንጭ፦ የጠ/ሚ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምንጭ፦ የጠ/ሚ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወታደራዊ ሔሊኮፕተር ተከሰከሰ‼️
የኢትዮጵያ ወታደራዊ ሔሊኮፕተር #ተከስክሶ ሶስት የበረራ ሰራተኞች ሞቱ። ሔሊኮፕተሩ #በአቢዬ ግዛት ሲከሰከስ 23 መንገደኞች ጭኖ ነበር። የተባበሩት መንግስታት የአቢዬ ግዛት ጸጥታ ጥበቃ ተልዕኮ አካል ነበር።
via Esehete Bekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ወታደራዊ ሔሊኮፕተር #ተከስክሶ ሶስት የበረራ ሰራተኞች ሞቱ። ሔሊኮፕተሩ #በአቢዬ ግዛት ሲከሰከስ 23 መንገደኞች ጭኖ ነበር። የተባበሩት መንግስታት የአቢዬ ግዛት ጸጥታ ጥበቃ ተልዕኮ አካል ነበር።
via Esehete Bekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሔሊኮፕተር ተከሰከሰ‼️
የኢትዮጵያ ወታደራዊ ሔሊኮፕተር በደቡብ ሱዳን አቢዬ ግዛት #ተከስክሶ ሶስት ሰዎች ሞቱ። በአደጋው የሞቱት #ሶስት ሰዎች የሔሊኮፕተሩ የበረራ #ሰራተኞች ናቸው። ከቆሰሉ ስምንት ተሳፋሪዎች ሶስቱ በአስጊ ሁኔታ ውስጥ ናቸው ተብሏል።
የምዝገባ ቁጥሩ UNO 379P የሆነው የኢትዮጵያ ወታደራዊ ሔሊኮፕተር በደቡብ ሱዳን የተባበሩት መንግሥታት የአቢዬ ጊዜያዊ የጸጥታ ኃይል (UNISFA) ቅጥር ግቢ ውስጥ በተከሰከሰበት ቅፅበት 23 መንገደኞች ጭኖ ነበር። የአቢዬ ጊዜያዊ የጸጥታ ኃይል እንዳስታወቀው ኤምአይ ስምንት (MI-8) የተባለው ሔሊኮፕተር በተከሰከሰበት ቅፅበት ካዱግሊ ከተባለ ቦታ ወደ አቢዬ በመቀየር ላይ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ወታደሮች አሳፍሮ ነበር።
በአደጋው ስምንት መንገደኞች ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ሶስቱ በአስጊ ኹኔታ ውስጥ እንደሚገኙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የደቡብ ሱዳን ተልዕኮ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። በአስጊ ኹኔታ ውስጥ የሚገኙት ተሳፋሪዎች በካዱግሊ በኩል ወደ አዲስ አበባ መወሰዳቸውንም አክሎ ገልጿል። በመግለጫው መሠረት ቀሪዎቹ አምስት መንገደኞች በአቢዬ በሚገኝ ሆስፒታል እገዛ እየተደረገላቸው ይገኛል።
ሔሊኮፕተሩን ለመከስከስ ያበቃው ምክንያት እስካሁን አልታወቀም። በደቡብ ሱዳን የተባበሩት መንግሥታት የአቢዬ ጊዜያዊ የጸጥታ ኃይል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ገብሬ አድሐና ጉዳዩ እየተመረመረ መሆኑን ተናግረዋል። "ዛሬ ከሰዓት በኋላ በተፈጠረው ክስተት እጅግ አዝነናል። በአደጋው ለሞቱ ሰዎች ቤተሰቦች የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እንገልፃለን" ብለዋል ሜጀር ጄኔራል ገብሬ።
የኢትዮጵያ ወታደራዊ ሔሊኮፕተር የተከሰከሰው መደበኛ የወታደሮች ዝውውር መርኃ-ግብር ተሰማርቶ በነበረበት ወቅት መሆኑን የአቢዬ ጊዜያዊ የጸጥታ ኃይል ያወጣው መግለጫ አትቷል። ለተባበሩት መንግሥታት የአቢዬ ጊዜያዊ የጸጥታ ኃይል ወታደሮች #በብቸኝነት ያዋጣቸው ኢትዮጵያ 4,500 አባላት ያሉትን ኃይል አሰማርታለች።
ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ወታደራዊ ሔሊኮፕተር በደቡብ ሱዳን አቢዬ ግዛት #ተከስክሶ ሶስት ሰዎች ሞቱ። በአደጋው የሞቱት #ሶስት ሰዎች የሔሊኮፕተሩ የበረራ #ሰራተኞች ናቸው። ከቆሰሉ ስምንት ተሳፋሪዎች ሶስቱ በአስጊ ሁኔታ ውስጥ ናቸው ተብሏል።
የምዝገባ ቁጥሩ UNO 379P የሆነው የኢትዮጵያ ወታደራዊ ሔሊኮፕተር በደቡብ ሱዳን የተባበሩት መንግሥታት የአቢዬ ጊዜያዊ የጸጥታ ኃይል (UNISFA) ቅጥር ግቢ ውስጥ በተከሰከሰበት ቅፅበት 23 መንገደኞች ጭኖ ነበር። የአቢዬ ጊዜያዊ የጸጥታ ኃይል እንዳስታወቀው ኤምአይ ስምንት (MI-8) የተባለው ሔሊኮፕተር በተከሰከሰበት ቅፅበት ካዱግሊ ከተባለ ቦታ ወደ አቢዬ በመቀየር ላይ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ወታደሮች አሳፍሮ ነበር።
በአደጋው ስምንት መንገደኞች ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ሶስቱ በአስጊ ኹኔታ ውስጥ እንደሚገኙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የደቡብ ሱዳን ተልዕኮ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። በአስጊ ኹኔታ ውስጥ የሚገኙት ተሳፋሪዎች በካዱግሊ በኩል ወደ አዲስ አበባ መወሰዳቸውንም አክሎ ገልጿል። በመግለጫው መሠረት ቀሪዎቹ አምስት መንገደኞች በአቢዬ በሚገኝ ሆስፒታል እገዛ እየተደረገላቸው ይገኛል።
ሔሊኮፕተሩን ለመከስከስ ያበቃው ምክንያት እስካሁን አልታወቀም። በደቡብ ሱዳን የተባበሩት መንግሥታት የአቢዬ ጊዜያዊ የጸጥታ ኃይል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ገብሬ አድሐና ጉዳዩ እየተመረመረ መሆኑን ተናግረዋል። "ዛሬ ከሰዓት በኋላ በተፈጠረው ክስተት እጅግ አዝነናል። በአደጋው ለሞቱ ሰዎች ቤተሰቦች የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እንገልፃለን" ብለዋል ሜጀር ጄኔራል ገብሬ።
የኢትዮጵያ ወታደራዊ ሔሊኮፕተር የተከሰከሰው መደበኛ የወታደሮች ዝውውር መርኃ-ግብር ተሰማርቶ በነበረበት ወቅት መሆኑን የአቢዬ ጊዜያዊ የጸጥታ ኃይል ያወጣው መግለጫ አትቷል። ለተባበሩት መንግሥታት የአቢዬ ጊዜያዊ የጸጥታ ኃይል ወታደሮች #በብቸኝነት ያዋጣቸው ኢትዮጵያ 4,500 አባላት ያሉትን ኃይል አሰማርታለች።
ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Alert‼️
የከንቲባ #ታከለ_ኡማ(ኢ/ር) የግል የፌስቡክ ገፅ ሃክ (በግል ለመገልገል ስላዳገተ) በመደረጉ ምክንያት የሚተላለፉ መልክቶችም ሆነ ሃሳቦች የእሳቸው እንዳልሆነ ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
ከንቲባ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የከንቲባ #ታከለ_ኡማ(ኢ/ር) የግል የፌስቡክ ገፅ ሃክ (በግል ለመገልገል ስላዳገተ) በመደረጉ ምክንያት የሚተላለፉ መልክቶችም ሆነ ሃሳቦች የእሳቸው እንዳልሆነ ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
ከንቲባ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Alert‼️
"የከንቲባ ታከለ ኡማ(ኢ/ር) የግል የፌስቡክ ገፅ ላይ "ፌስቡክ ገፄ #አልተጠለፈም" ተብሎ ቢገለፅም አሁንም ገፁ #ሃክ እንደተደረገ መሆኑን እንዲታወቅ እና ማንኛውም የሚተላለፍ መልዕክትም ሆነ ሃሳብ ከንቲባውን እንደማይወክል በድጋሚ ለመግለፅ እንወዳለን፡፡"
ከንቲባ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"የከንቲባ ታከለ ኡማ(ኢ/ር) የግል የፌስቡክ ገፅ ላይ "ፌስቡክ ገፄ #አልተጠለፈም" ተብሎ ቢገለፅም አሁንም ገፁ #ሃክ እንደተደረገ መሆኑን እንዲታወቅ እና ማንኛውም የሚተላለፍ መልዕክትም ሆነ ሃሳብ ከንቲባውን እንደማይወክል በድጋሚ ለመግለፅ እንወዳለን፡፡"
ከንቲባ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢንጂነር ታከለ ኡማ🔝
"ለትብብራችሁ ሁሉንም ከልብ አመሰግናለሁ። ኣሁን በICT team እርዳታና ትብብር hacked የተደረገው FB አካውቴ #ተስተካክሏል። Let me say this ,” When they go low , we go high “. Michelle Obama."
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ለትብብራችሁ ሁሉንም ከልብ አመሰግናለሁ። ኣሁን በICT team እርዳታና ትብብር hacked የተደረገው FB አካውቴ #ተስተካክሏል። Let me say this ,” When they go low , we go high “. Michelle Obama."
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኦሮሞና የሲዳማ ሊህቃን የምክክር መድረክ‼️
“የሲዳማ ህዝብ ራሱን ለማስተዳደር ዝግጅቱን እያጠናቀቀ ነው” - አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ
.
.
የሲዳማ ህዝብ እራሱን በራሱ ለማስተዳደር የሚያስችለውን ዝግጅት በማጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ #ሚሊዮን_ማቴዎስ አስታወቁ፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ ይህን ያሉት ዛሬ በሀዋሳ ከተማ በተካሄደው የኦሮሞና የሲዳማ ሊህቃን የምክክር መድረክ ላይ ነው።
የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ በሀዋሳው ስብሰባ ለተሳተፉ ታዳሚያን ባሰሙት ንግግር “የሲዳማ ህዝብ በዚህች አገር ፖለቲካዊ ለውጥ ለማምጣት ባደረገው አስተዋጽኦ ልክ ተጠቃሚ የመሆን ፍላጎት አለው” ብለዋል፡፡ የሁለቱን ህዝቦች ሊህቃንን ያገናኘው የዛሬው መድረክ “የሲዳማ ህዝብ እራሱን በራሱ ለማስተዳደር ዝግጅት እያደረገ ባለበት ወቅት [መካሄዱ] ልዩ ያደርገዋል” ሲሉም አክለዋል፡፡
የዛሬ የሀዋሳው የምክክር መድረክ ዓላማ “ሁለቱን ህዝቦች የሚወክሉ ፖለቲከኞች ልምዳቸውን ለመጋራት እና በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን ሀሳብ ለመለዋወጥ” እንደሆነ ተገልጿል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይም አንጋፋና ወጣት ፖለቲከኞች ተሳትፈዋል፡፡ በቅርቡ በኢትዮጵያ የተፈጠረውን ፖለቲካዊ ለውጥ ተከትሎ ወደ አገር ቤት የገቡት የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር (ኦዴግ) እና የሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን) መስራቾች እና አመራሮች የውይይቱ ተሳታፊዎች ነበሩ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር (ኦዴግ) ሊቀመንበር አቶ ሌንጮ ለታ “በኢትዮጵያ አሁን የተገኘው የፖለቲካ ለውጥ አዲስ የኢትዮጵያዊነት ፍልስፍና የተገኘበት ነው” ብለዋል፡፡ “ቀደምሲል የነበረው ኢትዮጵያዊነት ከዝንጉርጉርነት ይልቅ አንድ አይነት ቀለም የሚታይበት ነበር” ያሉት አቶ ሌንጮ “ከዚህ በኋላ ማንነትህን ከደጅ ጥለህ ኢትዮጵያዊ ትሆናለህ የሚለው አካሄድ ተቀባይነት የለውም” ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ሌላው የመድረኩ ተናጋሪ የኦዴግ አመራር አቶ #ሌንጮ_ባቲ በበኩላቸው “ወጣቶች ማለቂያ በሌለው ተቃውሞ ውስጥ በመግባት አሁን የተገኘው የፖለቲካ ምህዳር እንዳይበላሽ ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል” ሲሉ አሳስበዋል። ወጣቶች “በተለይም የሚያዳምጥ መንግስት ሲገኝ ጥያቄዎችን በሰከነ እና ሰላማዊና በሆነ መንገድ ማቅረብ እንደሚገባቸው” ምክራቸውን ለግሰዋል፡፡
ምንጭ:- የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
“የሲዳማ ህዝብ ራሱን ለማስተዳደር ዝግጅቱን እያጠናቀቀ ነው” - አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ
.
.
የሲዳማ ህዝብ እራሱን በራሱ ለማስተዳደር የሚያስችለውን ዝግጅት በማጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ #ሚሊዮን_ማቴዎስ አስታወቁ፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ ይህን ያሉት ዛሬ በሀዋሳ ከተማ በተካሄደው የኦሮሞና የሲዳማ ሊህቃን የምክክር መድረክ ላይ ነው።
የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ በሀዋሳው ስብሰባ ለተሳተፉ ታዳሚያን ባሰሙት ንግግር “የሲዳማ ህዝብ በዚህች አገር ፖለቲካዊ ለውጥ ለማምጣት ባደረገው አስተዋጽኦ ልክ ተጠቃሚ የመሆን ፍላጎት አለው” ብለዋል፡፡ የሁለቱን ህዝቦች ሊህቃንን ያገናኘው የዛሬው መድረክ “የሲዳማ ህዝብ እራሱን በራሱ ለማስተዳደር ዝግጅት እያደረገ ባለበት ወቅት [መካሄዱ] ልዩ ያደርገዋል” ሲሉም አክለዋል፡፡
የዛሬ የሀዋሳው የምክክር መድረክ ዓላማ “ሁለቱን ህዝቦች የሚወክሉ ፖለቲከኞች ልምዳቸውን ለመጋራት እና በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን ሀሳብ ለመለዋወጥ” እንደሆነ ተገልጿል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይም አንጋፋና ወጣት ፖለቲከኞች ተሳትፈዋል፡፡ በቅርቡ በኢትዮጵያ የተፈጠረውን ፖለቲካዊ ለውጥ ተከትሎ ወደ አገር ቤት የገቡት የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር (ኦዴግ) እና የሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን) መስራቾች እና አመራሮች የውይይቱ ተሳታፊዎች ነበሩ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር (ኦዴግ) ሊቀመንበር አቶ ሌንጮ ለታ “በኢትዮጵያ አሁን የተገኘው የፖለቲካ ለውጥ አዲስ የኢትዮጵያዊነት ፍልስፍና የተገኘበት ነው” ብለዋል፡፡ “ቀደምሲል የነበረው ኢትዮጵያዊነት ከዝንጉርጉርነት ይልቅ አንድ አይነት ቀለም የሚታይበት ነበር” ያሉት አቶ ሌንጮ “ከዚህ በኋላ ማንነትህን ከደጅ ጥለህ ኢትዮጵያዊ ትሆናለህ የሚለው አካሄድ ተቀባይነት የለውም” ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ሌላው የመድረኩ ተናጋሪ የኦዴግ አመራር አቶ #ሌንጮ_ባቲ በበኩላቸው “ወጣቶች ማለቂያ በሌለው ተቃውሞ ውስጥ በመግባት አሁን የተገኘው የፖለቲካ ምህዳር እንዳይበላሽ ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል” ሲሉ አሳስበዋል። ወጣቶች “በተለይም የሚያዳምጥ መንግስት ሲገኝ ጥያቄዎችን በሰከነ እና ሰላማዊና በሆነ መንገድ ማቅረብ እንደሚገባቸው” ምክራቸውን ለግሰዋል፡፡
ምንጭ:- የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
“የማንታረቀው #ጠላት ቢኖር ድህነት ነው፤ በመሆኑም በቀንደኛው ጠላታችን ድህነት ላይ የከፈትነውን ግብግብ አሁንም አጠናክረን እንቀጥላለን” - የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር #ደብረፅዮን_ገብረሚካኤል
#ቲክቫህኢትዮጵያ #TIKVAHETHIOPIA
#ቲክቫህኢትዮጵያ #TIKVAHETHIOPIA
ስካይ ላይት ሆቴል🔝
ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ለአፍሪካ መሪዎች በስካይ ላይት ሆቴል የእራት ግብዣ አደረጉ። በእራት ግብዣው ላይ ባደረጉት ንግግር ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
• ብዙዎች አፍሪካ ሲባል ወደ አይምሯቸው ምን እንደሚመጣ ቢታወቅም ለኔ ግን መልካም ተስፋ ያለባት አህጉር ናት
• አፍሪካ ከማንም በላይ የመልማት ተስፋ የሰነቀች አህጉር ናት፣ ከእንቅልፏም ነቅታለች
• ነገር ግን አፍሪካ ስኬታማ ለመሆን አሰቀድማ ከተለየችበት ማንነት መግኘት አለባት
• የዚህ ዘመን አፍሪካዊያን መተባበር መተማመን እና መደመር ያስፈልገናል፡፡ ከዚህ የተሻለ ምቹ ሁኔታ አይገኝምና
• አፍሪካ ከረሷ አልፎ በሰላምና ብልጽግና ለአለም ማበርከት ትችላለች
• የለውጥ ባቡር ያገኘውን እየደመረ ጉዞውን ጀምሯል፡፡ ኢትዮጵያም በግስጋሴ ላይ ትገኛለች፤ ባቡሩም ለሁሉም የሚበቃ ነው፡፡
• ከእኛም አልፎ መደመራችን አለም አቃፋዊ ይዘት እንዲኖረው መስራት ይኖርብናል
• የአፍሪካ ህብረት የኢትዮጵያ መሪ ለነበሩት ቀደማዊ ኃይለስላሴ ሃውልት እንዲቆምና እንዲታወሱ በማድረጉ ከፍተኛ ምስጋና አቀርባለሁ፡፡
• የትላንት ሳይኖር የዛሬው እኛ ያሌለን በመሆኑ የትላንቱን ማመስገን ተገቢ ነው።
ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ለአፍሪካ መሪዎች በስካይ ላይት ሆቴል የእራት ግብዣ አደረጉ። በእራት ግብዣው ላይ ባደረጉት ንግግር ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
• ብዙዎች አፍሪካ ሲባል ወደ አይምሯቸው ምን እንደሚመጣ ቢታወቅም ለኔ ግን መልካም ተስፋ ያለባት አህጉር ናት
• አፍሪካ ከማንም በላይ የመልማት ተስፋ የሰነቀች አህጉር ናት፣ ከእንቅልፏም ነቅታለች
• ነገር ግን አፍሪካ ስኬታማ ለመሆን አሰቀድማ ከተለየችበት ማንነት መግኘት አለባት
• የዚህ ዘመን አፍሪካዊያን መተባበር መተማመን እና መደመር ያስፈልገናል፡፡ ከዚህ የተሻለ ምቹ ሁኔታ አይገኝምና
• አፍሪካ ከረሷ አልፎ በሰላምና ብልጽግና ለአለም ማበርከት ትችላለች
• የለውጥ ባቡር ያገኘውን እየደመረ ጉዞውን ጀምሯል፡፡ ኢትዮጵያም በግስጋሴ ላይ ትገኛለች፤ ባቡሩም ለሁሉም የሚበቃ ነው፡፡
• ከእኛም አልፎ መደመራችን አለም አቃፋዊ ይዘት እንዲኖረው መስራት ይኖርብናል
• የአፍሪካ ህብረት የኢትዮጵያ መሪ ለነበሩት ቀደማዊ ኃይለስላሴ ሃውልት እንዲቆምና እንዲታወሱ በማድረጉ ከፍተኛ ምስጋና አቀርባለሁ፡፡
• የትላንት ሳይኖር የዛሬው እኛ ያሌለን በመሆኑ የትላንቱን ማመስገን ተገቢ ነው።
ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የሶማሌ ክልላዊ መንግስት በክልሉ ሰላምና ፀጥታ እንዲረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ በመሰራቱ ውጤት እየተመዘገበ መምጣቱን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ገለጹ። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስተፌ ሙሁመድ የመንግስታቸውን የአምስት ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለክልሉ ምክር ቤት አቀርበዋል። በሪፖርታቸውም አዲሱ የክልሉ አመራር ሥራ ከጀመረ ወዲህ በክልሉ ሲስተዋል የነበረው ብጥብጥ፣ ረብሻና አለመረጋጋት በሙሉ እንዲወገድ መስራቱን አመልክተዋል። በክልሉ ሊከሰቱ የነበሩ ሰላሳ የጎሳ ግጭቶች በውይይት እንዲፈቱ በመደረጉ በአሁኑ ወቅት በክልሉ ውስጥ መረጋጋት እየታየ መምጣቱን ተናግረዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia