TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የስራ ማቆም አድማ⬇️

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ‹‹ላለፉት ስምንት ዓመታት ላነሳናቸው ፍትሐዊ የሆኑ ከሙያ ዕውቅና፣ ከደመወዝና ከጥቅማ ጥቅም ጋር ለተገናኙ ጥያቄዎች በቂና ወቅታዊ ምላሽ አላገኘንም፤›› በማለት፣ ከሰኞ ነሐሴ 21 ቀን 2010 ዓ.ም. ጠዋት ጀምሮ የሥራ ማቆም #አድማ እንደሚያደርጉ አስታወቁ፡፡

በዚህም መሠረት #ከሰኞ ጠዋት አንድ ሰዓት ጀምሮ ከአምቡላንስ፣ ከቪአይፒና ከወታደራዊ በረራዎች ውጪ አናስተናግድም ሲሉም፣ ለባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ጽሕፈት ቤት ባስገቡት ደብዳቤ አስታውቀዋል፡፡

ተቆጣጣሪዎቹ ሰኔ 11 ቀን 2010 ዓ.ም. ለጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ባስገቡት ደብዳቤ በአፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጣቸው፣ ምላሽ ካላገኙ ግን ሥራቸውን #እንደሚለቁ ማስታወቃቸው ይታወሳል፡፡

©ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia