TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ🔝

‹‹ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ቀለምን እንጅ #ዘርን መቁጠር የለባቸውም፡፡›› የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር #ደሳለኝ_መንገሻ
.
.
.
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ‹‹ኪነ- ጥበብ ለሰላም›› በሚል ሃሳብ ለተማሪዎች መድረክ አዘጋጅቷል። ዩኒቨርሲቲው መድረኩን ያዘጋጀው በግብርናና ገጠር ትራንስፎርሜሽን የትምህርት መርሃ ግብር በሚሰጥበት ጠዳ ካምፓስ ለሚገኙ ተማሪዎች ነው።

የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችም በተለያዩ ማህበራዊ የትስስር መረቦች የሚሰራጬ መረጃዎችን እውነታነት በማመዛዘን ያስተማራቸውን ማህበረሰብ የመጥቀም ሃገራዊ ሃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚገባቸው ተገልጿል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ደሳለኝ መንገሻ እንዳሉት ተማሪዎች ለግጭት የሚዳርጉ አስተሳሰቦችንና ተግባራትን በመታገል በልዩነት አብሮ የመኖር እሴትን ማጎልበት አለባቸው። ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ቀለም ለመቁጠር እንጅ ዘር ለመቁጠር መሆን እንደሌለበትም ነው ያስገነዘቡት።

የጎንደር ዩኒቨርሲቲም ኪነ ጥበብ ለሰላም ያለውን ዋጋ በመገንዘብ መድረኮችን በመፍጠር ተማሪዎች ለሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደቱ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ አቅም የመፍጠር ተግባራችንን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት ያነጋገራቸው ተማሪዎች በበኩላቸው ቤተሰብና ሃገርን የመጥቀም ህልማቸው እንዲሳካ ተማሪዎች #በተሳሳተ_መረጃ ሳይረበሹ በመተሳሰብ ስሜት እውቀት መቅሰም እንዳለባቸው ነው የተናገሩት። ለዚህ እውን መሆን ደግሞ የበኩላቸውን አስተዋፆ እያደረጉ መሆኑን ነው የተናገሩት።

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ባዘጋጀው የኪነ ጥበብ መድረክ ሃገራዊ አንድነትን የሚያጎሉ የጥበብ ስራዎች ቀርበዋል።

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia