TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 10ኛ የወንጀል ችሎት በእነ #ጎሃ_አፅበሃ መዝገብ የተካተቱ በሰብዓዊ መብት ጥሰት በተጠረጠሩ 33 ግለሰቦች ላይ ለፖሊስ ከ10 እስከ 14 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፈቀደ። መርማሪ ፖሊስ ያላጠናቀቃቸው የምርመራ ስራዎች እንዳሉት በመግለፅ ተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው ፍርድ ቤቱን ጠይቆ ነበር።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር #ወርቅነህ_ገበየሁ በምዕራብ አርሲ ዞን በሻሸመኔ ወረዳ የሚገኘውን የኩየራ ሆስፒታል በዛሬው ዕለት ጎብኝተዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኮንጎ ዴሞክራሲያዊት ሪፐብሊክ ውስጥ ከነገ በስተያ - ዕሁድ ይካሄዳል ለተባለው ምርጫ ኮሚሽኑ ዝግጁ መሆኑንና ፀጥታና ደኅንነቱም ሙሉ በሙሉ እንደሚጠበቅ ፕሬዚዳንቱ #ጆዜፍ_ካቢላ ዛሬ አስታውቀዋል።

Via~VOA
@tsegabwolde @tikvhethiopia
የሟቾች ቁጥር 19 ደርሷል‼️

በሱዳን የነዳጅና የዳቦ ዋጋ #መጨመርን ተከትሎ በተከሰተው የኑሮ ውድነት ምክንያት በተቀሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞ #የሞቱት ሰዎች ቁጥር 19 መድረሱ ተገለፀ።ለተቃውሞ በወጡ ሰልፈኞችና በፖሊስ መካከል በተፈጠረ ግጭትም እስካሁን ሁለት የፖሊስ አባላትን ጨምሮ የ19 ሰዎች ህይዎት ማለፉን የሱዳን መንግስት ቃል አቀባይ ቦሻራ ጁማ አስታውቀዋል።

ምንጭ፦ አፍሪካ ኒውስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"የጦርነት እና የጥላቻ ንግግሮችን #እቃወማለሁ። "ሌላውን" ህዝብ በመሳደብ የሚገኝ "ጀግንነት" ይቅርብኝ። የሚያለማኝን ሰላም ትቼ የሚያጠፋኝን ግጭት አልመኝም። ሰው ሁሉ ወገኔ ነው። ለጥላቻ ሳይሆን ለህዝብ ፍቅር አሜን በሉ። አሜን!" #አብርሃ_ደስታ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በምዕራብ ጉጅ ዞን ዱግዳ ዳዋ ወረዳ ፊንጨዋ ከተማ ላይ የመከላከያ ሰራዊት አደረሰ በተባለ ጥቃት 11 ሰዎች ሲገደሉ ከ20 በላይ ቆስለዋል መኖሪያ ቤቶችና ተሽከርካሪዎች ተቃጥለዋል። በተመሳሳይ በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ከተማ ዛሬ በመከላከያ ሰራዊት በተተኮሰ ጥይት የ5 ሰዎች ህይወት አልፏል። በተጨማሪ በሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን ሻምቡ ከተማ ቢያንስ የ7 ሰዎች ህይወት አልፏል።

ምንጭ፦ ኢትዮጵያ ላይቭ ሀፕዴት

🔹በደረሰው አሳዛኝ ክስተት መንግስት የሚሰጠው መግለጫ ካለ ወድእናተ አደርሳለሁ።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መነ ቤኛ‼️

ሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላት በምዕራብ ኦሮሚያ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ውስጥ መነ ቤኛ ተብሎ በሚጠራ ስፍራ ላይ በጥይት ተመተው #መገደላቸውን የአካባቢው ባለስልጣናት ለቢቢሲ ተናገሩ።

የዞኑ የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ተረፈ፤ የተገደሉት ሁለቱ የፌደራል ፖሊስ አባላት የፊንጫአ ኃይል ማመንጫ እና ጌዶ ከተማ ላይ የሚገኝ የኃይል ማከማቻ ጠባቂዎች ነበሩ ብለዋል።

''መኪና ላይ ሆነው ወደ ፊንጫአ እየተጓዙ ሳሉ ተኩስ ተከፈተባቸው'' በማለት አቶ ደሳለኝ ሁኔታውን ያስረዳሉ።

ጥቃቱን ማን እንደሰነዘረ አልታወቀም የሚሉት አቶ ደሳለኝ የፌደራል ፖሊስ አባላቱ ትናንት እኩለ ቀን ገደማ መገደላቸውን ተናግረዋል።
በምዕራብ ኦሮሚያ አከባቢዎች የጸጥታ መደፍረስ ካጋጠመ ሰንብቷል።

የክልሉ መንግሥት በአከባቢው ለሚደርሱ ጥቃቶች የኦሮሞ ነጻነት ግንባርን ተጠያቂ ያደርጋል። በቅርቡ የኦዲፒ መአከላዊ ኮሚቴ አባል እና የገጠር ፖለቲካ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ በሰጡት መግለጫ ኦነግ የመንግሥት ባለስልጣናትን ይገድላል፣ የአስተዳደር ስርዓቱን ያፈራርሳል፣ ዘረፋ እና ሚሊሻዎችን ጦር ያስፈታል ሲሉ ኦነግን ከሰዋል።

በሌላ በኩል የኦነግ ሊቀመንበር አቶ #ዳውድ_ኢብሳ ድርጅታቸው ከመንግሥት ጋር ከስምምነት ላይ የደረሰባቸው ጉዳዮች በመንግሥት እየተጣሱ ነው በማለት ቅሬታቸውን ይናገራሉ።

ምንጭ፦ ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#የቁልቢ ገብርዔል ዓመታዊ ንግሥ በሰላም ተጠናቋል፡፡ በተመሳሳይ #የሀዋሳ የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል በሰላም ተጠናቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
Audio
ሲአን‼️

ኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ ያለውን የለውጥ ሂደት “ለመቀልበስ የሚደረጉ” ያላቸውን እንቅስቃሴዎች እንደሚቃወም የሲዳማ አርነት ንቅናቄ - ሲአን አስታውቋል፡፡

ለውጡን “ከፍተኛ መስዋዕትነት የተከፈለበት” ብሎታል ሲአን። የተለያየ ስብጥር ባላቸው #የሃዋሳ ከተማ ነዋሪዎች መካከል “አለመተማመን እንዲኖርና #ሁከት እንዲፈጠር የሚያደርጉ ኃይሎችን አወግዛለሁ" ብሏል ሲአን ትላንት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ።

“በሃሳብ ልዕልናና በሰላማዊ መንገድ እንጂ ሁከት በመፍጠርና ሰላም በመንሳት የሚደረግ ትግል ተቀባይነት የለውም” ብሏል ንቅናቄው።

"የሲዳማ ህዝብ ጥያቄ ነው" ያለው የሲዳማ ክልልነት ጥያቄ ውሣኔ-ሕዝብ ሂደት የደረሰበትን ደረጃ መንግሥት ለህዝብ እንዲያሳውቅ ሲአን ጠይቋል፡፡

Via~VOA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መቐለ ዩኒቨርሲቲ ሰላም ነው!!

"በመቐለ ዩኒቨርሲቲ የመማር ማስተማር ሂደት በሰላም ሁኔታ እየተከናወነ ሲሆን በማህበራዊ ድረገፅ የሚራገበው #የተሳሳተ መረጃ ትክክል እንዳልሆነ እየገልፅን ዩኒቨርሲቲው በአሁን ወቅት ፍፁም ሰላማዊ እና በተረጋጋ መንገድ የትምህርት እና ማህበራዊ አገልግሎትን እየሰጠ ይገኛል።" የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ፕሮፌሰር #ብርሃኑ_ነጋ የአንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ አባል በመሆን ተሹመዋል። ፕሮፌሰሩ እስከ ምርጫ 97 ድረስ በዩኒቨርሲቲው የኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል ያለምንም ክፍያ በመምህርነት ማገልገላቸው የሚታወቅ ነው።

Via Petros Ashenafi Kebede
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በአቶ #ገለሣ_ዲልቦ የሚመራው የኦሮሞ ነጻ አውጭ ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ዛሬ ንጋት ላይ አዲስ አበባ ገብተዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሶሪያ ስደተኞች በኢትዮጵያ‼️

የኢሚግሬሽንና የዜግነት ጉዳይ መምሪያ የኢትዮጵያን ህግ ተላልፈው #በልመና ላይ የተሰማሩ የሶሪያ ዜጎችን አሰሳ በማካሄድ ህጋዊ መስመር እንዲይዙ በማድረግ ላይ መሆኑንና እስካሁንም 118 ስደተኞችን መዝግቦ ለስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ አስተዳደር ማስረከቡን አስታወቀ፡፡

በስድስት ወር ጊዜ ውስጥም 559 #ሶሪያውያን በቱሪስት ቪዛ ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸው ጠቅሷል፡፡

በመምሪያው የህዝብ ግንኙነት ምክትል ኃላፊ አቶ የማነ ገብረመስቀል ለጋዜጣው ሪፖርተር እንደገለጹት፣ የቁጥጥርና ክትትል ሥራ በሚያከናውነው የመምሪያው ክፍል አማካኝነት ቦሌ ሚካኤል፣ ቦሌ መድኃኒዓለም፣ መርካቶ አንዋር መስጂድ፣ በእንግዳ ማረፊያዎች፣ ሆቴሎችና በሌሎችም ይገኙባቸዋል ተብለው በተጠረጠሩ አካባቢዎች አሰሳ በማካሄድ በህዳርና ታህሳስ ወሮች ብቻ 77፣ ቀደም ሲል ደግሞ 41 ሶሪያውያንን መዝግቦ ለስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ አስተዳደር በማስረከብ ህጋዊ ስደተኞች እንዲሆኑ ማድረግ ችሏል፡፡

ምንጭ፦ ኢ.ፕ.ኤ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ላይቤሪያ‼️

ላይቤሪያ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች #በነጻ እንዲማሩ ወሰነች...
.
.
የላይቤሪያው ፕሬዝዳንት ጆርጅ ዊሃ በሀገሪቱ በየትኛውም የመንግስት ዩኒቨርሲቲ የሚማሩ ተማሪዎች ከከፍያ ነጻ ሆነው እንዲማሩ አወጁ፡፡

የቀድሞው የእግር ኳስ ኮከብ እና የአሁኑ የላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ጆርጅ ዊሃ ላይቬርያውያን የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከክፍያ ነጻ ሆነው እንዲማሩ አውጇል፡፡

ፕሬዝዳንት ዊሃ ይህን አዋጅ ያሳወቁት ሰሞኑን በላይቤሪያ ዩኒቨርሲቲ ባደረጉበት ጉብኝት ነው፡፡ ማንኛውም የሀገሪቱ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ከዚህ በኋላ ወጪው በሀገሪቱ እንዲሸፈን ለተሰበሰበው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ እና ተማሪዎች አስታውቀዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ ይህን ያደረጉትም የተማሪዎች ወጪ በመንግስት በኩል መሸፈን አለበት በማለት ለአፍሪካም ፈር ቀዳጅ መሪነታቸውን አሳይተዋል ነው የተባለው፡፡

ላይቤሪያውያን ተማሪዎች ለአንድ ክሬዲት 4 የአሜሪካን ዶላር ክፍያ ይጠየቁ ነበር፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የክፍያው መጨመርም በተማሪዎች ዘንድ ተቃውሞን አስከትሏል፡፡ፕሬዝዳንቱ ባልተጠበቀ መልኩ ማወጃቸው በሀገሪቱ ተማሪዎች አግራሞትን ፈጥሯል፡፡
ላይቬሪያ 9 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች አሏት።

ጆርጅ ዊሃ 23ኛ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ሆነው ባለፈው ዓመት መመረጣቸው ይታወሳል፡፡

ምንጭ፡-አፍሪካን ስታንድ(አብመድ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዳዲስ ክልሎች‼️

የጋና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስድስት #አዳዲስ ክልሎችን ለመፍጠር የምርጫ ድምጽ እያሰጠ ነው፡፡ ጋናውያን በምዕራብ አፍሪካ ሀገራት ስድስት አዳዲስ ክልሎችን ለመፍጠር በተደረገው ሕዝበ ውሳኔ በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ድምጽ ይሰጣሉ፡፡ የምርጫ ኮሚሽኑ ከትላንት በስቲያ የድምፅ መስጫ መሳሪያዎችን በተገቢው ቀጠናዎች ላይ ያሰማራ ሲሆን ድምጽ የመስጠት ውሳኔው ትላንት ተከናውኗል፡፡

ምንጭ፦አፍሪካ ኒውስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይሳቅ ከኦነግ ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ ጋር ስለ ሰላም ተወያዩ። ፕሮፌሰር ኤፍሬም ምርጫ 97ን ተከትሎ መንግስትንና ተቃዋሚዎች ለማስታረቅ የተዋቀረውን የሽማግሌዎች ቡድን መምራታቸው ይታወሳል።

Via~ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia