አብዲ ኢሌ‼️
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የወንጀል በዛሬ ውሎው በቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት #አብዲ_መሀመድና በሳቸው መዝገብ በተከሰሱ ሌሎች ባለስልጠናት ላይ 14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል።
መርማሪ ፖሊስ ከሀምሌ 26 አስከ 30 ቀን 2010 ዓ.ም በጂግጂጋ ከተማና ሌሎች አካባቢዎች በተከሰተው ሁከት 742 ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን ከክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ባሰባሰበው መርጃ ማረጋገጡን ለችሎቱ አስርድቷል።
መርማሪ ፖሊስ ባለፉት 14 ቀናት ምርመራ ተገኝቷል ከተባለው የ200 ሰዎች የጅምላ መቃብር ጉዳይ ጋር በተያያዘ የ5 ሰዎችን የምስክር ቃል እንዲሁም፥ ከሁከትና ብጥብጡ ጋር በተያያዘ የሌሎች የአራት ሰዎች የምስክርነት ቃል መቀበሉን አስርድቷል።
ከጅምላ መቃብሩ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ተጨማሪ የምስክር ቃል ለመቀበልና የአስከሬን ምርመራ ውጤት የመቀበል ስራዎች እንደሚቀሩት የገለጸው መርማሪ ፖሊስ ከጉዳዩ ጋር በተያያዙ የምርመራ ስራዎቹ የ20 ሰዎችን የምስክር ቃል መቀበሉን አስረድቷል።
ከወንጀሉ ውስብሰብነት፣ ከሟቾች ቁጥር ብዛትና ከጉዳቱ ስፋን አንጻር ምርመራያን ባለማጠናቀቄም የተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ይፈቀድልኝ ሲል ፍርድቤቱን ጠይቋል።
የተጠርጣሪ ጠበቆች በበኩላቸው ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ከዋሉ 116 ቀናት ማስቆጠራቸውን በመግለጽና ምርመራው አለመጠናቀቁ ተገቢ አይደለም፣ መርማሪ ፖሊስ በዚህ ጊዜ ውስጥ የምስክር ቃል ማሰባሰብና ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር የማዋል ተግባሩን ሊያጠናቀቅ ይገባው የነበረ ሲሆን፥ የተጠርጣሪዎችን የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት ህገ ምንግስታዊ መብት የሚጥስ ነው ብለዋል።
ግራና ቀኙን ያዳመጠው ፍርድ ቤቱ የምርመራ ስራው በአግባቡ እየተካሄደ መሆኑን በመግለጽ ጉዳዩ በርካታ ሰዎች የሞቱበትና ውስብስብ በመሆኑ መርማሪ ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ በመቀበል ለታህሳስ 25 ቀን ተለዋጭ ቀጠሩ ሰጥቷል።
ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የወንጀል በዛሬ ውሎው በቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት #አብዲ_መሀመድና በሳቸው መዝገብ በተከሰሱ ሌሎች ባለስልጠናት ላይ 14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል።
መርማሪ ፖሊስ ከሀምሌ 26 አስከ 30 ቀን 2010 ዓ.ም በጂግጂጋ ከተማና ሌሎች አካባቢዎች በተከሰተው ሁከት 742 ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን ከክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ባሰባሰበው መርጃ ማረጋገጡን ለችሎቱ አስርድቷል።
መርማሪ ፖሊስ ባለፉት 14 ቀናት ምርመራ ተገኝቷል ከተባለው የ200 ሰዎች የጅምላ መቃብር ጉዳይ ጋር በተያያዘ የ5 ሰዎችን የምስክር ቃል እንዲሁም፥ ከሁከትና ብጥብጡ ጋር በተያያዘ የሌሎች የአራት ሰዎች የምስክርነት ቃል መቀበሉን አስርድቷል።
ከጅምላ መቃብሩ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ተጨማሪ የምስክር ቃል ለመቀበልና የአስከሬን ምርመራ ውጤት የመቀበል ስራዎች እንደሚቀሩት የገለጸው መርማሪ ፖሊስ ከጉዳዩ ጋር በተያያዙ የምርመራ ስራዎቹ የ20 ሰዎችን የምስክር ቃል መቀበሉን አስረድቷል።
ከወንጀሉ ውስብሰብነት፣ ከሟቾች ቁጥር ብዛትና ከጉዳቱ ስፋን አንጻር ምርመራያን ባለማጠናቀቄም የተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ይፈቀድልኝ ሲል ፍርድቤቱን ጠይቋል።
የተጠርጣሪ ጠበቆች በበኩላቸው ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ከዋሉ 116 ቀናት ማስቆጠራቸውን በመግለጽና ምርመራው አለመጠናቀቁ ተገቢ አይደለም፣ መርማሪ ፖሊስ በዚህ ጊዜ ውስጥ የምስክር ቃል ማሰባሰብና ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር የማዋል ተግባሩን ሊያጠናቀቅ ይገባው የነበረ ሲሆን፥ የተጠርጣሪዎችን የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት ህገ ምንግስታዊ መብት የሚጥስ ነው ብለዋል።
ግራና ቀኙን ያዳመጠው ፍርድ ቤቱ የምርመራ ስራው በአግባቡ እየተካሄደ መሆኑን በመግለጽ ጉዳዩ በርካታ ሰዎች የሞቱበትና ውስብስብ በመሆኑ መርማሪ ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ በመቀበል ለታህሳስ 25 ቀን ተለዋጭ ቀጠሩ ሰጥቷል።
ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia