TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
58.9K photos
1.5K videos
211 files
4.07K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
" መላው የሎስ አንጀለስ ግዛት በእሳት ስጋት ውስጥ ይገኛል " - ባለስልጣናት በአሜሪካ ፤ ሎስ አንጀለስ የተነሳው ሰደድ እሳት አሁንም መቆጣጠር ያልተቻለ ሲሆን የሟቾች ቁጥርም ወደ 24 ከፍ ብሏል። 16 ሰዎች ደግሞ የገቡበት አይታወቅም። በሎስ አንጀለስ ዙሪያ 3 አካባቢዎች መቃጠላቸውን ቀጥለዋል። በአሁኑ ላይ ትልቁ እሣት ሚገኘው በፓሊሳድስ ሲሆን 9307 ሔክታር መሬትን ሲያቃጥል 11 በመቶውን መቆጣጠር…
#Update

በአሜሪካ ፤ ሎስ አንጀለስ የተነሳው ከፍተኛ ሰደድ እሳት አሁንም መቆጣጠር ያልተቻለ ሲሆን እሳቱ አሁንም ሎስ አንጀለስን ማንደዱን ቀጥሏል።

እሳቱ እስካሁን ካደረሰው ውድመት በላይ ሊያደርስ ይችላል ተብሏል።

በአካባቢው ያለው የንፋስ ሁኔታ እሳቱን እያባባሰው ነው ተብሏል።

ከተነሱት ሰደድ እሳቶች አንዱን ብቻ ነው ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር የተቻለው።

ባለስልጣናት
#ቀጣዮቹ ንፋሶች አደጋ ሊያስከትሉ የሚችሉ የንፋስ ሁኔታዎች ሊሆኑ ይችላሉ በማለት መላው የሎስ አንጀለስ ግዛት በእሳት ስጋት ውስጥ እንደሚገኝ ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል።

እስከ ትላንት ባለው 24 ሰዎች ሲሞቱ 16 ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም።

የግል ትንበያ ተቋም የሆነው " አኩዌዘር " እስከ ትላንት ባለው በእሳት ቃጠሎ የተነሳ የደረሰው ኪሳራ ግምት ከ250 እስከ 275 ቢሊዮን ዶላር ሊደርስ ይችላል ብሏል።

@tikvahethiopia