TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አምቦ ዩኒቨርሲቲ🔝

በአምቦ ዩኒቨርሲቲ አዋሮ ካምፓስ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄዳ። ሰልፍ የወጡት ተማሪዎች የአማራ የኦሮሞ ልጆች የሚባል የለም ሁላችንም አንድ ነን፤ እዚህ የመጣንበት አላማ አንድ ነው እሱም ትምህርት ነው ብለዋል። በተጨማሪም ሁላችንም በሰላም መመለሳችንን የምትጠብቅ #ድሀ_እናት ነው ያለችን ሙሉ ሰው ልካ እሬሳ የምትቀበልበት ጊዜ አልፏል እናም ከመቼውም ጊዜ በላይ የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ልንጠነቀቅ ይገባል ብለዋል። በአጠቃላይ የተሰጠንን እድል ብናውቅ እንኳን ልንጋደል ቀርቶ ልንፋቀር ጊዜ አይበቃንም ስለዚህ እኛ #ኢትዮጵያ_ነን ሲሉ ገልፀዋል። የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ በቦታው ተገኝቶ ተማሪዎቹን አነጋግሯል።
.
.
ተጨማሪ

በሰልፉ ላይ ከተሰሙት መፈክሮች መሀከል...

🔹እኛ አንድ ኢትዮጵያ፤ አንዲት ሀገር ነን!
🔹እኛ አማራ፣ ኦሮሞ፣ ትግሬ አንድ ነን!
🔹ኢትዮጵያ ማደግ የምትችለው በሌብነት ሳይሆን በስራ ነው!
🔹ሌባ እምነት፤ ብሄር የለውም!!

ምንጭ፦ TIKVAH-ETH(አቢቲ)
@tsegabwolde @tikvhethiopia