TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.1K photos
1.5K videos
211 files
4.09K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኮሎኔል አሰፋ ዮሃንስ‼️

የቀድሞው የመከላከያ ፓዎር ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ስራ አስኪያጅ ኮሎኔል #አሰፋ_ዮሃንስ ከ2 ሚሊዮን ዶላር በላይ የህዝብ ሀብት በማባከን #መጠርጠራቸውን ፓሊስ አስታወቀ፡፡

ፖሊስ እንዳለው ተጠርጣሪው የበለስ ቁጥር 1 የስኳር ፕሮጀክት ከአንድ የቻይና ኩባንያ ጋር ፈርሞት የነበረው ኮንትራት ያለጨረታ በ5 ሚሊዮን 720 ሺህ ዶላር እንዲሻሻል አስደርገዋል፡፡

ኩባንያውም ገንዘቡን ተቀብሎ ምንም ሳይሰራ ከሀገር እንዲሸሽ በማድረግ ራሳቸውንና ኩባንያውን ብቻ አላግባብ ተጠቃሚ አድርገዋል፡፡

በዚህም የህዝብና የመንግስት ሀብት መዝብረው አስመዝብረዋል በሚል በሙስና ወንጀል ተጠርጥረዋል፡፡

ኮሎኔል አሰፋ የ6 ሚሊዮን 400 ሺህ ዶላር ሌላ የፕሮጀክት ኮንትራት ፈርሞ የነበረ ሌላ ኩባንያም ከዚህ ውስጥ 1 ሚሊዮን 920 ሺህ ዶላር በቅድሚያ ተቀብሎ ግዴታውን ሳይፈፅም እንዲጠፋ አስደርገዋል በሚል ተጨማሪ የሙስና ወንጀልም ተጠርጥረዋል ብሏል ፖሊስ፡፡

ተጠርጣሪው የተከላካይ ጠበቃ ለመቅጠር አቅም እንደሌላቸው በመግለፅ መንግስት እንዲመድብላቸው ፍርድ ቤቱን የጠየቁ ሲሆን ፍርድ ቤቱ በበኩሉ ግራ ቀኙን አዳምጦ ውሳኔ ለመስጠት ለመጪው ሰኞ ተለዋጭ ቀጠሮ ጥሏል፡፡

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia