TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ፈንሳይ-ፓሪስ⬆️ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር #አብይ_አህመድ ከፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ሚ/ር #ኢማኑኤል_ማክሮ ጋር ኤሊሴ ፓላስ ተወያዩ።

በውይይታቸውም:-

1) የላሊበላን አብያተ-ክርስቲያናት የጥገና ስራ ፈረንሳይ #እንድትደግፍ:

2) የፈረንሳይ ኢንቨስተሮች ወደ #ኢትዮጵያ መጥተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ:

3) ለልማት የሚያግዝ:- ቀጥታ የበጀት ድጋፍ ለማድረግ፣ በፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ፣ በአይ.ኤም.ኤፍ. እና በአለም ባንክ በኩል በቀጥታ እና በቦርድ በኩል #ድጋፍ ለማድርግ:

4) በአፍሪካ ቀንድ በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል የመጣውን ሰላም በማስቀጠል በኤርትራና በጅቡቲ መካከል ሰላም እንዲጠናከር ለማድረግ:

5) ፕሬዚዳንት ማርኮ ኢትዮጵያን #እንዲጎብኙ: ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ከትላንት በስቲያ የላሊበላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያናት ከጥገና እና እንክብካቤ አንጻር የሚገኙበትን ሁኔታ መጎብኝታቸው ይታወሳል።

ምንጭ፦ አቶ ፍፁም አረጋ
@tsegabwolde @tikvahethiopia