TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አርፈን ቀሎ🔝

የአንጋፋው የኦሮሞ አርቲስቶች ባንድ አርፈን ቀሎ አባላት ወደ ሀገራቸው #ተመለሱ። ዛሬ አዲስ አበባ የገቡት የባንዱ አባላት 17 ሲሆኑ፥ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በኦሮሚያ ክልል የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና በአድናቂዎቻቸው አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

የባንዱ አባላት ከአፄ ኃይለሥላሴ ዘመን ጀምሮ ህዝቡ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ መነቃቃት እንዲፈጥር የበኩላቸውን ሲያበረክቱ ቆይተዋል።

ኤፍ ቢ ሲ እንደዘገበው ኢትዮጵያ የገቡት የባንዱ አባላት በአርቲስት አሊ ሸቦ፣ አርቲስት ቱሬ ሌንጮ፣ አርቲስት ሸንተም ሹቢሳ፣ አርቲስት ጃፋር አሊ፣ አርቲስት አደም ሀሩን እና ፕሮፌሰር #ጀማል_ሀሰን ተመርተዋል፡፡

ወደ ሀገር ቤት የተመለሱትን አርቲስቶች ጨምሮ አዳዲስና ነባር የኦሮሞ አርቲስቶችን የሚያሳትፍ የሙዚቃና የጥበብ ኮንሰርት ለጥር 18 ቀን 2011 በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ እየተዘጋጀ ይገኛል።

Via fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia