#update በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውና በአይነቱ የተለየ #የመልእክት እና #የገንዘብ መላላኪያ የስልክ መተግበሪያ በትላንትናው እለት በኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል ተመርቆአል። ይህ 'ሜዳ ቻት' የተሰኘ መተግበሪያ #360_ግራውንድ በተባለ ሀገራዊ ድርጅት የተሰራ ሲሆን በአማርኛ, በኦሮምኛ, በትግርኛ እና በኢንጊሊዘኛ ቻት ማድረግ ያስችላል። የገንዘብ መላላኪያው አዲሱን የዳሽን ባንክን አሞሌ ኦንላይን ገንዘብ የሚጠቀም ሲሆን Wechat እንደተሰኘው የቻይናዊውያን መተግበሪያ ገንዘብን ልክ እንደመልክት እጅግ በቀለለ መልኩ መላክ እና መቀበል ያስችላል። ሜዳ ቻት በየቀኑ የሚያሸልም ጨዋታ, በርካታ ሀገራዊ ስቲከሮች እና ሌሎችም አገልግሎቶችን የያዘ ሲሆን መተግበሪያውን ለመስራት ከሶስት አመት በላይ ፈጅቷል።
ምንጭ፦ ብሩክ(ከሜዳ ቻት)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምንጭ፦ ብሩክ(ከሜዳ ቻት)
@tsegabwolde @tikvahethiopia