TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ፎቶ⬆️የቀድሞው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ #ኃይለማርያም_ደሳለኝ እና የአሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር #ዐብይ_አህመድ በዛሬው ዕለት ተገናኝተዋል። አቶ ኃይለማርያም በፕሬዘዳንት ኢሳያስ ቅበላ ወቅትም ነበሩ።

ፎቶ፦ አቶ ፍፁም አረጋ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ እና የኤርትራው ፕሬዚደንት ኢሳያስ አፈወቂ #ኦሞ_ኩራዝ ቁጥር ሶስትን መርቀው ከፍተዋል ፋብሪካውንም ተዘዋውረው ጎብኝተዋል::

©etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አርባ ምንጭ!! ጠ/ሚ ዶክተር አብይ እና ፕሬዘዳንት ኢሳያስ አርባ ምንጭ ከተማ ናቸው። ለጋሞ ሽማግሌዎችም ጠ/ሚኒስትሩ ምስጋና ያቀርባሉ። አርባ ምንጭ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ነው የተደረገላቸው።

አዳዲስ ጉዳዮችን ይዤ እመለሳለሁ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አርባ ምንጭ! ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ እና ለፕሬዘዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የተደረገው ደማቅ አቀባበል።

ቪድዮ፦ አቶ ፍፁም አረጋ
@tsegabwolse @tikvahethiopia
#update የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በኬንያ አቻው 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አርባ ምንጭ⬆️

ክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር #አብይ_አህመድ ለጋሞ ሽማግሌዎች #የሰላም ተምሳሌትነት ምስጋ ለማቅረብ ከክቡር ፕሬዚዳንት አቶ #ኢሳያስ_አፈወርቂ ጋር በውቧና ለምለሚቷ የ40 ምንጮች ባለቤት በሆነችው በአርባምንጭ ከተማ በምስጋና ፕሮግራም ላይ በጋሞ ሽማግሌዎች፣ የኪነጥበብ ባለሙያዎች እና በአካባቢው ነዋሪዎች ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው።

ምንጭ፦ አቶ ፍፁም አረጋ
@tsegabwolde @tikvahehiopia
በTIKVAH-ETH የማስታወቂያ ውል ያለን እና ማስታወቂያዎችን እያስነገራችሁ የምትገኙ የቻናላችን ደንበኞች @tsegabwolde2 በዚህ አድራሻ ብቻ አግኙኝ! ቢቻል አሁን!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከወልቂጤ⬇️

"ሀይ ፀግሽ እንዴት ነህ? የፊታችን ጥቅምት 10 የጉራጌ ዞን የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነት እና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ አስተባባሪ ኮሚቴ የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች እና ተጋባዥ እንግዶች ለመቀበል ከፍተኛ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡ @ዘርማ@"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በርካቶች የተቀባበሉት የዛሬው ፎቶ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ የጋሞ የሀገር ሽማግሌዎች እና ወጣቶች የሠላም አብነት ናችሁ ሲሉ የሠላም መገለጫ የሆነችውን #እርግብ አበርክተዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰው #ይቅርታ የሚጠይቅህ ስህተት ስለሰራ ብቻ ሳይሆን ከሰራው ስህተት ይልቅ #ፍቅርህ ስለሚበልጥበት ነው!

ፈጣሪ ይቅርታን የሚጠይቅ አንደበትና ይቅርታን የሚያደርግ ልብ ይስጠን!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፍቅር ከሌለህ የከንቱ ከንቱ ነህ!!

"እውነተኛ #ፍቅር ቀለም፣ ብሄር፣ ጎሳ፣ ክልል፣ ዜግነት፣ ሀገር፣ የኑሮ ደረጃ... አይመርጥም ሁሉንም #ያቅፋል፤ ሁሉንም #ይስማል!"
.
.
እውነተኛ ፍቅር በውስጥህ ሳይኖር ስለሰው ልጅ ክቡርነት ሳትረዳ ስለብሄር፣ ጎሳ፣ ክልል፣ ሀገር፣ ባንዲራ ብታወራ የከንቱ ከንቱ ነህ እልሃለው። አጠገብህ ያሉትን ወንድሞችህንና እህቶችህን ወደው ባላመጡት ብሄራቸው እየለየህ #እያቋሸሽክና #እየሰደብክ፤ እያሳደድክና እያዋረድክ፤ እየገደልክ እና እያፈናቀልክ ስለዴሞክራሲ እየታገልኩ ነው፤ ስለብሄሬ እና ማንነቴ እየታገልኩ ነው ብትል የ ዓለም #ማፈሪያ እልሃለሁ።
.
.
እውነተኛ #ፍቅር ቀለም፣ ብሄር፣ ጎሳ፣ ክልል፣ ዜግነት፣ ሀገር፣ የኑሮ ደረጃ... አይመርጥም ሁሉንም #ያቅፋል፤ ሁሉንም #ይስማል!
.
.
ዶክተር አብይን #ማድነቅ እና #መስማት፤ መደገፍ እና መከተል ብቻ በቂ አይደለም የሚሰራውን እያዩም መማር ትልቅነትና አዋቂነትም ጭምር ነው!

🔹ፀጋአብ ወልዴ ኢትዮጵያ🔹
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Forwarded from Kal Act
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
KAL Original Products
We provide your needs beyond your want.

በአይነታቸዉ ለየት ያሉ ነገር ግን ለህይወትዎ እጅግ ጠቃሚ የሆኑ እቃዎችን አቅርበናል፤ በቀጣይም ምናቀርባቸውን እቃዎች ለማየት ቻናላችንን ይቀላቀሉን።

@kaloriginalproducts
📲 +251909509595
#update መንግስት ጠንካራ እርምጃ ወሰደ⬇️

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ህገ ወጥ ወታደራዊ ስልጠና ሲወስዱ በነበሩ ፀረ ሰላም ሃይሎች ላይ #እርምጃ መዉሰዱን የክልሉ መንግስት አስታወቀ፡፡

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሶሳ ወረዳ ገንገን ቀበሌ ልዩ ቦታዉ ዛለን ወንዝ በሚባል ስፍራ በተደራጀ መልኩ ወታደራዊ ስልጠና ሲወስዱ
በነበሩ የጥፋት ሃይሎች ላይ እርምጃ መዉሰዱን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሰይፈዲን ሃሩን ለኢቢሲ እንደተናገሩት ህዝቡ ባደረሰን መረጃ መሰረት ቁጥራቸዉ በአሶሳ ወረዳ ገንገን ቀበሌ ልዩ ቦታዉ ዛለን ወንዝ በሚባል ስፍራ በተደራጀ መልኩ ወታደራዊ ስልጠና ሲወስዱ የነበሩ የጥፋት ሃይሎች ላይ የክልሉ ልዩ ሃይል ፖሊስ እርምጃ ወስዷል፡፡

በተደረገዉ ወታደራዊ ኦፕሬሽን 31 የሚሆኑ የጥፋት ሃይሎችን በቁጥጥር ስር ያዋለ ሲሆን ከ1 መቶ በላይ የሚሆኑ የሰልጣኝ ቤቶች እንዲወድሙ ተደርጓል ብለዋል፡፡

ከ20 በላይ የሚሆኑ ወጣቶች በፈቃደኝነት #እጃቸዉን መስጠታቸዉንም ኮሚሽነሩ ተናግረዋል፡፡

ሲሰለጥኑበት የነበረ አንድ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ከተያዙት ሰልጣኞች በተገኘዉ መረጃ መሰረት ለጊዜዉ በተሰወሩ የጥፋት ሃይሎች ጋር ከ12 በላይ የሚገመት የጦር መሳሪያ አብሮ እንደተሰወረ ለማወቅ ተችሏል ብለዋል፡፡

ስልጠናዉን የሚወስዱት በተደራጀ ካምፕ ዉስጥ የነበረ ሲሆን የህክምናና የምግብ አገልግሎት በተሟላ መልኩ ይቀርብ እንደነበር መታወቁን የገለፁት ኮሚሽነሩ ልዩ ሃይሉ በወሰደዉ እርምጃ ካምፑን ሙሉ በሙሉ መደምሰስ ተችሏል ብለዋል፡፡

የጥፋት ሃይሎች ዓላማ የክልሉን ሰላም ማደፍረስና የተለያዩ የጥፋት አጀንዳዎችን በማንገብ ህብረተሰቡ የተረጋጋ ኑሮ እንዳይኖር ማድረግ መሆኑን ኮሚሽነሩ ተናግረዋል፡፡

ለኮሚሽኑ በደረሰዉ መረጃ መሰረት ከ4 መቶ በላይ የሚሆኑ የጥፋት ሃይሎች በተደራጀ መልኩ ከ 1 ወር በላይ ህገ ወጥ ወታደራዊ ስልጠና ሲወስዱ እንደነበር ታዉቋል ብለዋል፡፡

ሸሽተዉ ወደ ጎረቤት አገር ሱዳን ብሉ ናይል ግዛት ገቡትን በቁጥጥር ስር ለማዋል የኦፕሬሽን ስራዉ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡

አብዛኞቹ የጥፋት ሃይል ሰልጣኞች 10 ዓመት ከዚያ በላይ የዕድሜ ክልል ዉስጥ ያሉ #ታዳጊና #ጎልማሶች ናቸዉ፡፡
በጥፋት ሃይሎች ወታደራዊ ስልጠና ዉስጥ ከመመልመል አንስቶ እስከ የጦር ትጥቅና የፋይናንስ ድጋፍ ያደረጉ አካላት የመለየት ስራ እየተሰራ ነዉ ብለዋል፡፡

አኩራፊ ሃይሎች እና አፈንጋጭ የቤህነን ወታደሮች እንዳሉበት ተደርሶበታል ያሉት ኮሚሽነሩ የምርመራ ሂደቱን በቀጣይ ለህዝቡ የምናሳዉቅ ይሆናል ብለዋል፡፡

ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ደብዛው የጠፋው ጋዜጠኛ⬇️

የቱርክ ፕሬዚዳንት #ጣይብ_ኤርዶሃንና የሳዑዲው ንጉስ #ሳልማን_ቢን አብዱልአዚዝ ደብዛው በጠፋው ጋዜጠኛ ጉዳይ ላይ በስልክ #ተወያዩ

ጋዜጠኛ #ጀማል_ካሾጊ ከሁለት ሳምንት በፊት ቱርክ በሚገኘው የሳዑዲ ዓረቢያ ኮንስላ ጽህፈት ቤት ጉዳይ #ሊያስፈፅም እንደገባ ደብዛው ከጠፋ 13 ቀናት ተቆጥረዋል።

የቱርክ ፕሬዚዳንት ጣይብ ኤርዶሃንና የሳዑዲው ንጉስ ሳልማን ትናንት ሌሊት በስልክ ባደረጉት ውይይት የጋዜጠኛው መጥፋት ጉዳይ አጀንዳቸው ነበር ተብሏል።

ኤርዶሃን በጀማል ካሾጊ ጉዳይ ላይ ጥምር ቡድን ተቋቁሞ ምርመራ እንዲካሄድ በአፅንኦት መናገራቸው ተሰምቷል።

ካሾጊ በሳዑዲ ቆንስላ ጽህፈት ቤት በነበረበት ወቅት 10 ሳዑዲዎች እና የመንግስት ባለስልጣናት በሁለት አውሮፕላኖች ወደ ኢስታንቡል በማምራት ጽህፈት ቤቱን በተመሳሳይ ቀን መጎብኘታቸውን የቱርክ ፖሊስ መረጃዎች ያሳያሉ።

የዋሽንግተን ፖስት ጋዜጣ አምደኛ የሆነው የሳዑዲ ዜግነት ያለው ጋዜጠኛ ጀማል ካሾጊ የት እንደገባ አለመታወቁን ተከትሎ ቱርክ፣ አሜሪካ እና ብሪታኒያ ከሳዑዲ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

ቱርክ ጋዜጠኛው #መገደሉን የሚያሳዩ መረጃዎችን አግኝቻለሁ እያለች ነው።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንዳሉት ጋዜጠኛው በቆንስላ ጽህፈት ቤቱ ውስጥ መገደሉ ከተረጋገጠ ሳዑዲ ከባድ #ቅጣት ይጠብቃታል ብለዋል።

ይህን ተከትሎም ሳዑዲ በሰጠችው ምላሽ ማንኛውም ሀገር በጀማል ካሾጊ ጉዳይ ሀሰተኛ ውንጀላ የሚያቀርብ፣ ኢኮኖሚያዊም ሆነ ፖለቲካዊ ጫና ለመፍጠር የሚያስብ ሀገር ካለ የአፀፋ ምላሽ እንደምትወስድ አስጠንቅቃለች።

ምንጭ፦ አናዶሉና ሮይተርስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia