TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF ህወሓት የምርጫ ቦርድን ውሳኔ ፤ " ጥያቄው ሌላ መልሱ ሌላ " ሲል ውድቅ አድርጎታል። ህወሓት ባወጣው መግለጫ ፥ " የስራ ኃላፊዎቼ ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩና ከሚመለከታቸው የፌደራል መንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን በማካሄድ ሕጋዊ ሰውነታችን እንዲመለስ መግባባት ላይ ተደርሷል " ብሏል። " በአፍሪካ ህብረት ፓናል ውይይትም ይህ ጉዳይ ተነስቶ ህጋዊ ሰውነቱ መመለስ እንዳለበት…
ትግራይን ዳግም ወደ ጦርነት የሚያስገባ ተጨባጭ ስጋት አለ ?
" ይሄ የአንድ ድርጅት ጉዳይ ነው። ወደ ጦርነት የሚያስገባ ምንም ነገር የለም " - አቶ አማኑኤል አሰፋ
በሊቀ - መንበሩ ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የ14ኛው የህወሓት ጉባኤ ቃል አቀባይ አማኑኤል አሰፋ ፤ አሁን ባለው ሁኔታ ወደ ጦርነት የሚያስገባ ነገር የለም ብለዋል።
አቶ አማኑኤል ፥ " በአንድ አዳራሽ ውስጥ ገብቶ ተሰብስቦ ስለ አንድ ድርጅት ውስጣዊ ጉዳዮች መወሰን ወደ ጦርነት የሚያስገባ አንድም ምክንያት የለም " ሲሉ ተናግረዋል።
" ጦርነት በዚህን ያህል ኢትዮጵያ ውስጥ ርካሽ አይደለም " ብለዋል።
" ጦርነት አስፈላጊ ሆኖ አማራጭ ቢሆን ኖሮ ትግራይ ውስጥ ያሉት ችግሮች ሌላ ጦርነት ይጋብዙ ነበር " ሲሉ ተደምጠዋል።
እንዚህ ችግሮች ለተፈጸሙ ወንጀሎች የተጠያቂነት አለመረጋገጥ ፣ በህገመንግስት ላይ የተቀመጠው የክልሉ ግዛት አለመመለስ ፣ የተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው አለመመለስ ፣ የኢኮኖሚ ቀውስ ...ወዘተ እንደሆኑ ነው የጠቆሙት።
" ዛሬም ትግራይ ውስጥ ብዙ ችግሮች አሉ። ህዝቡ መስእዋትነት እየከፈለባቸው ነው ግን የተጀመረውን የሰላም ተስፋ ወደ ከፍተኛ ደረጃ እንዲሸጋገር ህዝቡ መስእዋትነት እየከፈለ እየኖረ ነው " ብለዋል።
" ያሉ ችግሮች ወደ ጦርነት ሳያስገቡ አንድ ህወሓት የሚባል ድርጅት በፕሪቶሪያ ስምምነት አካል የሆነ ባለቤት የሆነ ውስጣዊ ችግሮች አጋጥመውት ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ሰላሙን ዘላቂ ለማድረግ የሚያስችል ስራ በመስራቱ ወደ ጦርነት ሊገባ አይችልም " ሲሉ ተደምጠዋል።
" ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደዚህ ብለዋል ... እንዲህ ብለዋል ተብሎ የተለያየ ትርጉም ከተሰጠው በኃላ ይሄን በሚመለከት ህወሓት ጠቅላይ ሚኒስትሩን engage አድርጓል። " ብለዋል።
" በዚህ ደረጃ ጦርነት ውስጥ የሚያስገባን ነገር እንደሌለ ግልጽ ሆኗል " ሲሉ አክለዋል።
" ህወሓት አንድ ድርጅት ነው " ያሉት አቶ አማኑኤል አሰፋ ፥ " የተለያዩ ስራዎች ሊሰራ ይችላል ፤ ያን ስራ በሚመለከት መወያየትና መነጋገር ይቻላል። ችግሮች ካሉ ለመወያየት እና አብሮ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል የተጀመረ የሰላም ማዕቀፍ አለ ያን መሰረት አድርጎ መወያየት እና መፍታት ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" ኢትዮጵያ ውስጥ በተከታታይ የተደረጉ ጦርነቶች ናቸው የዛሬውን ችግር ያመጡት " የሚሉት አቶ አማኑኤል " ብዙ ችግር ባለበት ሀገር ሆነን አሁንም ጦርነት ውስጥ ለመግባት የሚያስችል ምንም ምክንያት የለም " ብለዋል።
" ስለተሰበሰብን ፣ አንድ አዳራሽ ውስጥ ገብቶ ህወሓት የሆነ ነገር ስላደረገ ጦርነት አይመጣም ፤ እንዴት ጦርነት በዚህ ልክ ርካሽ ይሆናል ? " ሲሉ ጠይቀዋል።
" ይሄ የአንድ ድርጅት ጉዳይ ነው ፤ ውስጣዊ ችግሩን ለመፍታት ነው ጉባኤ የሚደረገው " ሲሉ ለወይን በሰጡት ቃለ መጠየቅ ተናግረዋል።
#TPLF #TIGRAY
@tikvahethiopia
" ይሄ የአንድ ድርጅት ጉዳይ ነው። ወደ ጦርነት የሚያስገባ ምንም ነገር የለም " - አቶ አማኑኤል አሰፋ
በሊቀ - መንበሩ ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የ14ኛው የህወሓት ጉባኤ ቃል አቀባይ አማኑኤል አሰፋ ፤ አሁን ባለው ሁኔታ ወደ ጦርነት የሚያስገባ ነገር የለም ብለዋል።
አቶ አማኑኤል ፥ " በአንድ አዳራሽ ውስጥ ገብቶ ተሰብስቦ ስለ አንድ ድርጅት ውስጣዊ ጉዳዮች መወሰን ወደ ጦርነት የሚያስገባ አንድም ምክንያት የለም " ሲሉ ተናግረዋል።
" ጦርነት በዚህን ያህል ኢትዮጵያ ውስጥ ርካሽ አይደለም " ብለዋል።
" ጦርነት አስፈላጊ ሆኖ አማራጭ ቢሆን ኖሮ ትግራይ ውስጥ ያሉት ችግሮች ሌላ ጦርነት ይጋብዙ ነበር " ሲሉ ተደምጠዋል።
እንዚህ ችግሮች ለተፈጸሙ ወንጀሎች የተጠያቂነት አለመረጋገጥ ፣ በህገመንግስት ላይ የተቀመጠው የክልሉ ግዛት አለመመለስ ፣ የተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው አለመመለስ ፣ የኢኮኖሚ ቀውስ ...ወዘተ እንደሆኑ ነው የጠቆሙት።
" ዛሬም ትግራይ ውስጥ ብዙ ችግሮች አሉ። ህዝቡ መስእዋትነት እየከፈለባቸው ነው ግን የተጀመረውን የሰላም ተስፋ ወደ ከፍተኛ ደረጃ እንዲሸጋገር ህዝቡ መስእዋትነት እየከፈለ እየኖረ ነው " ብለዋል።
" ያሉ ችግሮች ወደ ጦርነት ሳያስገቡ አንድ ህወሓት የሚባል ድርጅት በፕሪቶሪያ ስምምነት አካል የሆነ ባለቤት የሆነ ውስጣዊ ችግሮች አጋጥመውት ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ሰላሙን ዘላቂ ለማድረግ የሚያስችል ስራ በመስራቱ ወደ ጦርነት ሊገባ አይችልም " ሲሉ ተደምጠዋል።
" ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደዚህ ብለዋል ... እንዲህ ብለዋል ተብሎ የተለያየ ትርጉም ከተሰጠው በኃላ ይሄን በሚመለከት ህወሓት ጠቅላይ ሚኒስትሩን engage አድርጓል። " ብለዋል።
" በዚህ ደረጃ ጦርነት ውስጥ የሚያስገባን ነገር እንደሌለ ግልጽ ሆኗል " ሲሉ አክለዋል።
" ህወሓት አንድ ድርጅት ነው " ያሉት አቶ አማኑኤል አሰፋ ፥ " የተለያዩ ስራዎች ሊሰራ ይችላል ፤ ያን ስራ በሚመለከት መወያየትና መነጋገር ይቻላል። ችግሮች ካሉ ለመወያየት እና አብሮ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል የተጀመረ የሰላም ማዕቀፍ አለ ያን መሰረት አድርጎ መወያየት እና መፍታት ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" ኢትዮጵያ ውስጥ በተከታታይ የተደረጉ ጦርነቶች ናቸው የዛሬውን ችግር ያመጡት " የሚሉት አቶ አማኑኤል " ብዙ ችግር ባለበት ሀገር ሆነን አሁንም ጦርነት ውስጥ ለመግባት የሚያስችል ምንም ምክንያት የለም " ብለዋል።
" ስለተሰበሰብን ፣ አንድ አዳራሽ ውስጥ ገብቶ ህወሓት የሆነ ነገር ስላደረገ ጦርነት አይመጣም ፤ እንዴት ጦርነት በዚህ ልክ ርካሽ ይሆናል ? " ሲሉ ጠይቀዋል።
" ይሄ የአንድ ድርጅት ጉዳይ ነው ፤ ውስጣዊ ችግሩን ለመፍታት ነው ጉባኤ የሚደረገው " ሲሉ ለወይን በሰጡት ቃለ መጠየቅ ተናግረዋል።
#TPLF #TIGRAY
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ትግራይን ዳግም ወደ ጦርነት የሚያስገባ ተጨባጭ ስጋት አለ ? " ይሄ የአንድ ድርጅት ጉዳይ ነው። ወደ ጦርነት የሚያስገባ ምንም ነገር የለም " - አቶ አማኑኤል አሰፋ በሊቀ - መንበሩ ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የ14ኛው የህወሓት ጉባኤ ቃል አቀባይ አማኑኤል አሰፋ ፤ አሁን ባለው ሁኔታ ወደ ጦርነት የሚያስገባ ነገር የለም ብለዋል። አቶ አማኑኤል ፥ " በአንድ አዳራሽ ውስጥ ገብቶ…
#TPLF
በሊቀመንበሩ ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የተመራው የህወሓት ጉባኤ አቶ ጌታቸው ረዳን ከምክትል ሊቀመንበርነት አነሳ።
ዶ/ር ደብረጽዮን በድጋሚ ሊቀመንበር ሆነው መመረጣቸው ተነግሯል።
በአቶ ጌታቸው ረዳ ምትክ አቶ አማኑኤል አሰፋ ምክትል ሊመንበር ሆነው ተመርጠዋል።
ሌሎች የስራ አስፈጻሚና የማእከላይ ኮሚቴ ሆነው የተመረጡ የድርጅቱ አባላት ከላይ ስማቸው ተያይዟል።
ምርጫ ቦርድ ከጉባኤው ቀደም ብሎ የቦርዱን አሰራር ያልተከተለ ጠቅላላ ጉባኤ እና በጉባኤው የሚተላለፉ ማንኛውም ውሳኔዎች ተቀባይነት እንደማይኖረው አሳውቆ ነበር።
@tikvahethiopia
በሊቀመንበሩ ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የተመራው የህወሓት ጉባኤ አቶ ጌታቸው ረዳን ከምክትል ሊቀመንበርነት አነሳ።
ዶ/ር ደብረጽዮን በድጋሚ ሊቀመንበር ሆነው መመረጣቸው ተነግሯል።
በአቶ ጌታቸው ረዳ ምትክ አቶ አማኑኤል አሰፋ ምክትል ሊመንበር ሆነው ተመርጠዋል።
ሌሎች የስራ አስፈጻሚና የማእከላይ ኮሚቴ ሆነው የተመረጡ የድርጅቱ አባላት ከላይ ስማቸው ተያይዟል።
ምርጫ ቦርድ ከጉባኤው ቀደም ብሎ የቦርዱን አሰራር ያልተከተለ ጠቅላላ ጉባኤ እና በጉባኤው የሚተላለፉ ማንኛውም ውሳኔዎች ተቀባይነት እንደማይኖረው አሳውቆ ነበር።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF በሊቀመንበሩ ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የተመራው የህወሓት ጉባኤ አቶ ጌታቸው ረዳን ከምክትል ሊቀመንበርነት አነሳ። ዶ/ር ደብረጽዮን በድጋሚ ሊቀመንበር ሆነው መመረጣቸው ተነግሯል። በአቶ ጌታቸው ረዳ ምትክ አቶ አማኑኤል አሰፋ ምክትል ሊመንበር ሆነው ተመርጠዋል። ሌሎች የስራ አስፈጻሚና የማእከላይ ኮሚቴ ሆነው የተመረጡ የድርጅቱ አባላት ከላይ ስማቸው ተያይዟል። ምርጫ ቦርድ ከጉባኤው ቀደም…
#TPLF
በሊቀ-መንበር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በተመራውና ለ7 ቀናት በቆየው የህወሓት 14ኛው ጉባኤ አዳዲስ የቁጥጥር ኮሚሽን አባላት ተመርጠዋል።
የኮሚሽኑ ሊቀመንበር እና ጉባኤውን ሲቃወሙ የቆዩትን አቶ ተኽለብርሃን ኣርኣያ ተነስተው አቶ ገብረ ካሕሳይ ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል።
አሁን ከሊቀመንበር ቦታቸው ተነስተው በአቶ ገብረ የተተኩት አቶ ተኽለብርሃን ይመሩት የነበረው የቁጥጥር ኮሚሽን ፤ የቁጥጥር ኮሚሽን ፥ " ጤናማ ያልሆነ ሂደት ውጤታማና መልካም ጉባኤ መፍጠር ስለማይችል የሚያስከትለው አደጋ የከፋ ነው " በማለት ከጉባኤው ራሱን ማግለሉን ይታወሳል።
በሌላ በኩል ፥ በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የተመራው የህወሓት ጉባኤ ፤ በጉባኤው ላይ ያልተሳተፉ አባላትን አግዷል።
" ጉባኤው እንዳይካሄድ እንቅፋት ፈጥሯል " ያለውን ቡድን ነው ያገደው።
ያታገዱት አባላት ጥያቄቸውን በጹሁፍ የሚያቀርቡ ከሆነ ወደ አባልነታቸው ሊመለሱ ይችላሉ ብሏል።
ቀደም ብሎ የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ ያሉበት 14 የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ጉባኤውን እንደማይሳተፉ ማሳወቃቸው ፤ የቁጥጥር ኮሚሽን አባላትም ራሳቸውን ማግለላቸው ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
በሊቀ-መንበር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በተመራውና ለ7 ቀናት በቆየው የህወሓት 14ኛው ጉባኤ አዳዲስ የቁጥጥር ኮሚሽን አባላት ተመርጠዋል።
የኮሚሽኑ ሊቀመንበር እና ጉባኤውን ሲቃወሙ የቆዩትን አቶ ተኽለብርሃን ኣርኣያ ተነስተው አቶ ገብረ ካሕሳይ ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል።
አሁን ከሊቀመንበር ቦታቸው ተነስተው በአቶ ገብረ የተተኩት አቶ ተኽለብርሃን ይመሩት የነበረው የቁጥጥር ኮሚሽን ፤ የቁጥጥር ኮሚሽን ፥ " ጤናማ ያልሆነ ሂደት ውጤታማና መልካም ጉባኤ መፍጠር ስለማይችል የሚያስከትለው አደጋ የከፋ ነው " በማለት ከጉባኤው ራሱን ማግለሉን ይታወሳል።
በሌላ በኩል ፥ በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የተመራው የህወሓት ጉባኤ ፤ በጉባኤው ላይ ያልተሳተፉ አባላትን አግዷል።
" ጉባኤው እንዳይካሄድ እንቅፋት ፈጥሯል " ያለውን ቡድን ነው ያገደው።
ያታገዱት አባላት ጥያቄቸውን በጹሁፍ የሚያቀርቡ ከሆነ ወደ አባልነታቸው ሊመለሱ ይችላሉ ብሏል።
ቀደም ብሎ የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ ያሉበት 14 የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ጉባኤውን እንደማይሳተፉ ማሳወቃቸው ፤ የቁጥጥር ኮሚሽን አባላትም ራሳቸውን ማግለላቸው ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF በሊቀመንበሩ ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የተመራው የህወሓት ጉባኤ አቶ ጌታቸው ረዳን ከምክትል ሊቀመንበርነት አነሳ። ዶ/ር ደብረጽዮን በድጋሚ ሊቀመንበር ሆነው መመረጣቸው ተነግሯል። በአቶ ጌታቸው ረዳ ምትክ አቶ አማኑኤል አሰፋ ምክትል ሊመንበር ሆነው ተመርጠዋል። ሌሎች የስራ አስፈጻሚና የማእከላይ ኮሚቴ ሆነው የተመረጡ የድርጅቱ አባላት ከላይ ስማቸው ተያይዟል። ምርጫ ቦርድ ከጉባኤው ቀደም…
#TPLF #Tigray
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን ለመምራት ህወሓት " የራሱን ሰዎች መመደብ ይችላል " ሲሉ የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ተናገሩ።
አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመሩት ቡድን " አሁን ህወሓትን መወከል አይችልም ” ብለዋል።
ሊቀመንበሩ ፤ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙበት ትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር " ህወሓትን ወክሎ ነው የገባው። አሁን ህወሓትን መወከል አይችልም " ሲሉ ተናግረዋል።
በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር " የህወሓት ሰዎች መመደብ አለባቸው " ብለው በጉዳዩ ላይ ጊዜያዊ አስተዳደሩን " ካቋቋሙ ወገኖች ጋር ውይይት ያስፈልጋል " ብለዋል።
በጊዜያዊ አስተዳደሩ ውስጥ ከህወሓት በተጨማሪ የትግ ራይ ሠራዊት፣ ምሁራን እና ተቃዋሚው ባይቶና ድርሻ አላቸው።
በጉዳዩ ዙሪያ ከፌድራሉ መንግስት ጋር ውይይት ማድረግ እንደሚያስፈልግ ጠቁመው ፥ " እኛ ትግራይ ውስጥ ብቻ የምንጨርሰው አይደለም" ሲሉ ተናግረዋል።
ከሰሞኑን ህወሓት " የድርጅቱን አመራሮች የከፋፈለ ነው " የተባለለትን 14ኛ ጠቅላላ ጉባኤ አድርጎ ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤልን በድጋሚ ሊቀመንበር አድርጎ መምረጡ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑትን አቶ ጌታቸው ረዳን በማንሳት አቶ አማኑኤል አሰፋን እንዲሁም ሌሎችንም አዳዲስ የማዕከላዊና የስራ አስፈጻሚዎችን መምረጡ ይታወቃል።
ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግን ቀደም ብሎ ጉባኤው ሳይጀመር የቦርዱን አሰራር ላልተከተለ ጉባኤ እና በጉባኤው ለሚተላለፉ ማንኛውም ውሳኔዎችና ለውጦች እውቅና እንደማይሰጥ በይፋ አሳውቋል።
#TPLF #EthiopiaInsider
@tikvahethiopia
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን ለመምራት ህወሓት " የራሱን ሰዎች መመደብ ይችላል " ሲሉ የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ተናገሩ።
አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመሩት ቡድን " አሁን ህወሓትን መወከል አይችልም ” ብለዋል።
ሊቀመንበሩ ፤ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙበት ትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር " ህወሓትን ወክሎ ነው የገባው። አሁን ህወሓትን መወከል አይችልም " ሲሉ ተናግረዋል።
በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር " የህወሓት ሰዎች መመደብ አለባቸው " ብለው በጉዳዩ ላይ ጊዜያዊ አስተዳደሩን " ካቋቋሙ ወገኖች ጋር ውይይት ያስፈልጋል " ብለዋል።
በጊዜያዊ አስተዳደሩ ውስጥ ከህወሓት በተጨማሪ የትግ ራይ ሠራዊት፣ ምሁራን እና ተቃዋሚው ባይቶና ድርሻ አላቸው።
በጉዳዩ ዙሪያ ከፌድራሉ መንግስት ጋር ውይይት ማድረግ እንደሚያስፈልግ ጠቁመው ፥ " እኛ ትግራይ ውስጥ ብቻ የምንጨርሰው አይደለም" ሲሉ ተናግረዋል።
ከሰሞኑን ህወሓት " የድርጅቱን አመራሮች የከፋፈለ ነው " የተባለለትን 14ኛ ጠቅላላ ጉባኤ አድርጎ ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤልን በድጋሚ ሊቀመንበር አድርጎ መምረጡ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑትን አቶ ጌታቸው ረዳን በማንሳት አቶ አማኑኤል አሰፋን እንዲሁም ሌሎችንም አዳዲስ የማዕከላዊና የስራ አስፈጻሚዎችን መምረጡ ይታወቃል።
ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግን ቀደም ብሎ ጉባኤው ሳይጀመር የቦርዱን አሰራር ላልተከተለ ጉባኤ እና በጉባኤው ለሚተላለፉ ማንኛውም ውሳኔዎችና ለውጦች እውቅና እንደማይሰጥ በይፋ አሳውቋል።
#TPLF #EthiopiaInsider
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ጊዜያዊ አስተደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የስልጣን ሽምሹር አደረጉ። ፕሬዜዳንቱ በህወሓት የፓሊት ቢሮ አባልዋ ወ/ሮ ሊያ ካሳ ምትክ ፀጋይ ገብረተኽለ ገ/ክርስቶስ የደቡባዊ ምስራቅ ዞን አስተዳዳሪ በማድረግ ሾመዋል። በአቶ ጌታቸው ረዳ ተፈርሞ ነሃሴ 14/2016 ዓ.ም የወጣው ደብዳቤ ፤ ፀጋይ ገብረተኽለ የዞኑ አስተዳዳሪ በመሆን የሚገባቸው ጥቅም ተጠብቆላቸው ሃላፊነቱን በአግባቡ…
#TPLF #Tigray
በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ማንኛውም አይነት የስልጣን ሹምሽር አልቀበልም አለ።
በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " በማንኛው የሃላፊነት እርከን በራስ ፍላጎት የሚደረግ የስራ ምደባና ሹምሽር ተቀባይነት የለውም " ብሏል።
የእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ህወሓት ለሁሉም የዞንና የወረዳ የድርጅቱ ፅህፈት ጠቅሶ ባሰራጨው ደብዳቤ ፥ " ከሰርዓታዊና ተቋማዊ አሰራር ውጪ የሚካሄዱ የስራ ምደባዎች ኢህጋዊ ብቻ ሳይሆኑ ተጠያቂነትን ያስከትላሉ " ሲል አስጠንቅቋል።
የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ነሃሴ 17/2016 ዓ.ም በህወሓት የፓሊት ቢሮ አባልዋ ወ/ሮ ሊያ ካሳ ምትክ ፀጋይ ገብረተኽለ ገ/ክርስቶስ የደቡባዊ ምስራቅ ዞን አስተዳዳሪ በማድረግ መሾማቸው ዘግበናል።
ነሃሴ 18/2016 ዓ.ም የወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ደግሞ በሰሜናዊ ምዕራብ ዋና አስተዳዳሪና በቅርቡ ህወሓት ባካሄደው ጉባኤ የፓሊት ቢሮ አባል ሆነው በተመረጡት ተክላይ ገ/መድህን ምትክ የክልሉ የስፓርት ኮሚሽን ኮምሽነር የነበሩት ተኽላይ ፍቓዱ ተሹመዋል።
ትግራይ ካሉዋት ሰባት የዞን አስተዳደሮች በአሁኑ ጊዜ ስድስቱ የእነ ዶ/ር ደብረፂዮን አካሄድ በሚቃወሙ የሚመሩ ሲሆኑ የመቐለ ከተማ ብቻ በቅርቡ በተካሄደ ጉባኤ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ሆኖው በተመረጡት ይመራል።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ማንኛውም አይነት የስልጣን ሹምሽር አልቀበልም አለ።
በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " በማንኛው የሃላፊነት እርከን በራስ ፍላጎት የሚደረግ የስራ ምደባና ሹምሽር ተቀባይነት የለውም " ብሏል።
የእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ህወሓት ለሁሉም የዞንና የወረዳ የድርጅቱ ፅህፈት ጠቅሶ ባሰራጨው ደብዳቤ ፥ " ከሰርዓታዊና ተቋማዊ አሰራር ውጪ የሚካሄዱ የስራ ምደባዎች ኢህጋዊ ብቻ ሳይሆኑ ተጠያቂነትን ያስከትላሉ " ሲል አስጠንቅቋል።
የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ነሃሴ 17/2016 ዓ.ም በህወሓት የፓሊት ቢሮ አባልዋ ወ/ሮ ሊያ ካሳ ምትክ ፀጋይ ገብረተኽለ ገ/ክርስቶስ የደቡባዊ ምስራቅ ዞን አስተዳዳሪ በማድረግ መሾማቸው ዘግበናል።
ነሃሴ 18/2016 ዓ.ም የወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ደግሞ በሰሜናዊ ምዕራብ ዋና አስተዳዳሪና በቅርቡ ህወሓት ባካሄደው ጉባኤ የፓሊት ቢሮ አባል ሆነው በተመረጡት ተክላይ ገ/መድህን ምትክ የክልሉ የስፓርት ኮሚሽን ኮምሽነር የነበሩት ተኽላይ ፍቓዱ ተሹመዋል።
ትግራይ ካሉዋት ሰባት የዞን አስተዳደሮች በአሁኑ ጊዜ ስድስቱ የእነ ዶ/ር ደብረፂዮን አካሄድ በሚቃወሙ የሚመሩ ሲሆኑ የመቐለ ከተማ ብቻ በቅርቡ በተካሄደ ጉባኤ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ሆኖው በተመረጡት ይመራል።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
#TPLF #እንዳስላሰሽረ
በሊቀ መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ተከለከለ።
ህወሓት ሰላማዊ ስልፍ ለማካሄድ ከጳጉሜን 3 - 5 ባሉት ቀናት የጠየቀ ሲሆን ሰልፉ የሚካሄድበት ቦታ ደግሞ በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን እንዳስላሰ ሽረ ከተማ ነው።
የህወሓት ፅህፈት ቤት እንዳስላሰ ሽረ ቅርንጫፍ ነሃሴ 29/2016 ዓ.ም በፃፈው የሰላማዊ ሰልፍ የፍቃድ ደብዳቤ በክልሉ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ በሰላማዊ መንገድ ድምፁ ለማሰማት መፈለጉ ያትታል።
ቅርንጫፍ ፅህፈቱ ፍቃድ በጠየቀበት ሰላማዊ ሰልፍ ፦
"
- ከባቢያዊ መለያየትና አገር የሚበትኑ ተግባራት ይቁሙ !
- ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ይመለሱ !!
- የፀለምቲና ራያ ተመላሽ ተፈናቃዮች ድህንነታቸው ይጠበቅ !
- የህዝበኝነት ፓለቲካ በትግራይ እንቃወማለን !
- የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ ይተግበር !
- ጊዚያዊ አስተዳደር የተቋቋመለት ዓላማ ይተግብር !
- ህወሓትን ለማፍረስ የሚደረግ እንቅስቃሴ ይቁም !
- ህወሓት ሰላምን ይደግፋል !
- ጦርነት የሚናፍቅ የህወሓት መሪ የለም ! "
የሚሉና ሌሎች መፈክሮች እንደሚያሰማ በፍቃድ መጠየቂያ ደብዳቤው ላይ ገልጿል።
ቅርንጫፍ ፅህፈቱ ለጠየቀው ' ሰላማዊ ሰልፍ ' የማካሄድ ጥያቄ መልስ የሰጠው የእንዳስላሰ ሽረ ከተማ አስተዳደር በወቅቱ ባለው የፓለቲካ ትኩሳት እና የአዲስ ዓመት መለወጫ በመሆኑ ምክንያት የፀጥታ ሃይሉ የተደራረቡ ስራዎች ስላሉበት ሰላማዊ ስልፉ እንዳልተፈቀደ አሳውቋል።
በጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ ልኡክ በተምቤን ዓብዩ ዓዲ ዓዲግራትን ማይጨው ካካሄዳቸው ህዝባዊ ውይይቶች በመቀጠል በአክሱምና በእንዳስላሰ ሽረ ከተማዎች ለማካሄድ አቅዶ የነበረ ቢሆንም አቶ ጌታቸው ባጋጣመቸው የጤና እክል ምክንያቱ ውይይቱ ለሌላ ጊዜ መዛወሩን የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል መዘገቡ ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
በሊቀ መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ተከለከለ።
ህወሓት ሰላማዊ ስልፍ ለማካሄድ ከጳጉሜን 3 - 5 ባሉት ቀናት የጠየቀ ሲሆን ሰልፉ የሚካሄድበት ቦታ ደግሞ በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን እንዳስላሰ ሽረ ከተማ ነው።
የህወሓት ፅህፈት ቤት እንዳስላሰ ሽረ ቅርንጫፍ ነሃሴ 29/2016 ዓ.ም በፃፈው የሰላማዊ ሰልፍ የፍቃድ ደብዳቤ በክልሉ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ በሰላማዊ መንገድ ድምፁ ለማሰማት መፈለጉ ያትታል።
ቅርንጫፍ ፅህፈቱ ፍቃድ በጠየቀበት ሰላማዊ ሰልፍ ፦
"
- ከባቢያዊ መለያየትና አገር የሚበትኑ ተግባራት ይቁሙ !
- ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ይመለሱ !!
- የፀለምቲና ራያ ተመላሽ ተፈናቃዮች ድህንነታቸው ይጠበቅ !
- የህዝበኝነት ፓለቲካ በትግራይ እንቃወማለን !
- የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ ይተግበር !
- ጊዚያዊ አስተዳደር የተቋቋመለት ዓላማ ይተግብር !
- ህወሓትን ለማፍረስ የሚደረግ እንቅስቃሴ ይቁም !
- ህወሓት ሰላምን ይደግፋል !
- ጦርነት የሚናፍቅ የህወሓት መሪ የለም ! "
የሚሉና ሌሎች መፈክሮች እንደሚያሰማ በፍቃድ መጠየቂያ ደብዳቤው ላይ ገልጿል።
ቅርንጫፍ ፅህፈቱ ለጠየቀው ' ሰላማዊ ሰልፍ ' የማካሄድ ጥያቄ መልስ የሰጠው የእንዳስላሰ ሽረ ከተማ አስተዳደር በወቅቱ ባለው የፓለቲካ ትኩሳት እና የአዲስ ዓመት መለወጫ በመሆኑ ምክንያት የፀጥታ ሃይሉ የተደራረቡ ስራዎች ስላሉበት ሰላማዊ ስልፉ እንዳልተፈቀደ አሳውቋል።
በጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ ልኡክ በተምቤን ዓብዩ ዓዲ ዓዲግራትን ማይጨው ካካሄዳቸው ህዝባዊ ውይይቶች በመቀጠል በአክሱምና በእንዳስላሰ ሽረ ከተማዎች ለማካሄድ አቅዶ የነበረ ቢሆንም አቶ ጌታቸው ባጋጣመቸው የጤና እክል ምክንያቱ ውይይቱ ለሌላ ጊዜ መዛወሩን የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል መዘገቡ ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray " እየተደረገ ያለውን እንቅስቃሴና መሳሳብ ህዝብ ስላልወደደው አሁኑኑ መቆም አለበት !! " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ም/ ፕሬዚደንትና የሰላምና ፀጥታ ሴክሬታሪያት ካቢኔ ሃላፊ ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር። በዚሁ ጋዜጣዊ መግለጫ ፥ " በአሁኑ ወቅት ለሁለት በተከፈለው ህወሓት መካከል እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴና መሳሳብ ህዝብ ስላልወደደው…
#TPLF
" በሕወሓት ውሳኔ መሰረት አቶ ጌታቸው ረዳ ከኤርትራ መንግስት ባለሥልጣናት ጋር ዱባይ ላይ ተገናኝተዋል " - ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር)
ዛሬ የህዝባዊ ወያነ ትግራይ (ህወሓት) ሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ዛሬ በጽሕፈት ቤታቸው መግለጫ ሰጥተው ነበር።
በአብዛኛው በእርሳቸው እና በፓርቲያቸው ዙርያ የሚቀርቡ ክሶች አስመልክተው ማብራርያ መስጠታቸው ነው የተነገረው።
በተለይ " ከኤርትራ ጋር ግንኙነት አላቸው " ተብሎ ለሚቀርበው ክስ ምላሽ ሰጥተዋል።
ደብረፅዮን (ዶ/ር) ፥ በሕወሓት ውሳኔ መሰረት አቶ ጌታቸው ረዳ ከኤርትራ መንግስት ባለሥልጣናት ጋር ከወራት በፊት በተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ፣ ዱባይ መገናኘታቸውን ገልጸዋል።
" ፕሬዝደንት ጌታቸው ከኤርትራ መሪዎች ጋር ግንኙነት አድርጓል። ሥራ አስፈፃሚው እና እኔ የማውቀው ግንኙነት ተደርጓል። " ብለዋል።
" ይህ መጥፎ አይደለም። ለሰላም ብለን ነው። ያለፈው በተጠያቂነት አሠራር ይታያል፥ አሁን ግን ወደ ችግር አታስገቡን፣ ወሰኖች ነፃ አድርጉ፣ ሰው ያግቱ ነበር አታግቱ ለማለት፣ እንስሳት ይዘርፉ ነበረ ሰዎች ያስሩ ነበር አቁሙ ለማለት ከኤርትራ መሪዎች ጋር በውጭ ሀገር ግንኙነቱ ተደርጓል " ሲሉ አስረድተዋል።
" ይህን ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ እንዲያውቁት ተደርጓል። እሳቸውም ከእናንተ ጋር ቅሬታ አላቸው ተገናኙ ብለዋል። ይህ የታወቀ ነው። ይህ ስህተት የለውም። ጌታቸው ግን አይጠቅስም፣ ' ሌሎች አሉ የሚገናኙ ነው ' የሚለው " ሲሉ አክለዋል።
መረጃው የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
" በሕወሓት ውሳኔ መሰረት አቶ ጌታቸው ረዳ ከኤርትራ መንግስት ባለሥልጣናት ጋር ዱባይ ላይ ተገናኝተዋል " - ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር)
ዛሬ የህዝባዊ ወያነ ትግራይ (ህወሓት) ሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ዛሬ በጽሕፈት ቤታቸው መግለጫ ሰጥተው ነበር።
በአብዛኛው በእርሳቸው እና በፓርቲያቸው ዙርያ የሚቀርቡ ክሶች አስመልክተው ማብራርያ መስጠታቸው ነው የተነገረው።
በተለይ " ከኤርትራ ጋር ግንኙነት አላቸው " ተብሎ ለሚቀርበው ክስ ምላሽ ሰጥተዋል።
ደብረፅዮን (ዶ/ር) ፥ በሕወሓት ውሳኔ መሰረት አቶ ጌታቸው ረዳ ከኤርትራ መንግስት ባለሥልጣናት ጋር ከወራት በፊት በተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ፣ ዱባይ መገናኘታቸውን ገልጸዋል።
" ፕሬዝደንት ጌታቸው ከኤርትራ መሪዎች ጋር ግንኙነት አድርጓል። ሥራ አስፈፃሚው እና እኔ የማውቀው ግንኙነት ተደርጓል። " ብለዋል።
" ይህ መጥፎ አይደለም። ለሰላም ብለን ነው። ያለፈው በተጠያቂነት አሠራር ይታያል፥ አሁን ግን ወደ ችግር አታስገቡን፣ ወሰኖች ነፃ አድርጉ፣ ሰው ያግቱ ነበር አታግቱ ለማለት፣ እንስሳት ይዘርፉ ነበረ ሰዎች ያስሩ ነበር አቁሙ ለማለት ከኤርትራ መሪዎች ጋር በውጭ ሀገር ግንኙነቱ ተደርጓል " ሲሉ አስረድተዋል።
" ይህን ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ እንዲያውቁት ተደርጓል። እሳቸውም ከእናንተ ጋር ቅሬታ አላቸው ተገናኙ ብለዋል። ይህ የታወቀ ነው። ይህ ስህተት የለውም። ጌታቸው ግን አይጠቅስም፣ ' ሌሎች አሉ የሚገናኙ ነው ' የሚለው " ሲሉ አክለዋል።
መረጃው የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#TPLF
በእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ቡድን የሚመራው ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙባቸው 16 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ማባረሩና ከነበራቸው ድርጅታዊ ሃላፊነት ማንሳቱን አስታወቀ።
ድርጅቱ መስከረም 6/2017 ዓ.ም አካሄድኩት ያለውን ስብሰባ አስመልክቶ ባወጣው ባለ ሦስት ገፅ መግለጫ :-
1. አቶ ጌታቸው ረዳ
2. አቶ በየነ ምክሩ
3. ፕ/ር ክንደያ ገ/ሂወት
4. ዶ/ር ሓጎስ ጎዲፈይ
5. ወ/ሮ ኣልማዝ ገ/ፃዲቕ
6. አቶ ረዳኢ ሓለፎም
7. ወ/ሮ ሰብለ ካሕሳይ
8. አቶ ኢሳያስ ታደሰ
9. አቶ ሰለሞን መዓሾ
10. አቶ ሺሻይ መረሳ
11. ዶ/ር ገ/ሂወት ገ/ሄር
12. አቶ ርስቁ አለማው
13. አቶ ሃፍቱ ኪሮስ
14. አቶ ብርሃነ ገ/የሱስ
15. አቶ ሩፋኤል ሽፋረ
16. አቶ ነጋ ኣሰፋ
ከአባልነትና ከድርጅት ሃላፊነት " አባርሪያችኃለሁ " ብሏል።
የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ህወሓት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና የነፈገውና የድርጅቱ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ ጌታቸው ረዳና በርካታ የማእከለዊ ኮሚቴ አባላት " ህገወጥ " ያሉትን 14ኛ ጉባኤ በማካሄድ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል መልሶ የድርጅቱ ሊቀመንበር አድርጎ መምረጡ ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
በእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ቡድን የሚመራው ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙባቸው 16 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ማባረሩና ከነበራቸው ድርጅታዊ ሃላፊነት ማንሳቱን አስታወቀ።
ድርጅቱ መስከረም 6/2017 ዓ.ም አካሄድኩት ያለውን ስብሰባ አስመልክቶ ባወጣው ባለ ሦስት ገፅ መግለጫ :-
1. አቶ ጌታቸው ረዳ
2. አቶ በየነ ምክሩ
3. ፕ/ር ክንደያ ገ/ሂወት
4. ዶ/ር ሓጎስ ጎዲፈይ
5. ወ/ሮ ኣልማዝ ገ/ፃዲቕ
6. አቶ ረዳኢ ሓለፎም
7. ወ/ሮ ሰብለ ካሕሳይ
8. አቶ ኢሳያስ ታደሰ
9. አቶ ሰለሞን መዓሾ
10. አቶ ሺሻይ መረሳ
11. ዶ/ር ገ/ሂወት ገ/ሄር
12. አቶ ርስቁ አለማው
13. አቶ ሃፍቱ ኪሮስ
14. አቶ ብርሃነ ገ/የሱስ
15. አቶ ሩፋኤል ሽፋረ
16. አቶ ነጋ ኣሰፋ
ከአባልነትና ከድርጅት ሃላፊነት " አባርሪያችኃለሁ " ብሏል።
የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ህወሓት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና የነፈገውና የድርጅቱ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ ጌታቸው ረዳና በርካታ የማእከለዊ ኮሚቴ አባላት " ህገወጥ " ያሉትን 14ኛ ጉባኤ በማካሄድ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል መልሶ የድርጅቱ ሊቀመንበር አድርጎ መምረጡ ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ከሚመራው የህወሓት ቡድን ጋር ያላቸው ልዩነት በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ እንደሚሰራ በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው የህወሓት ቡድን ተናግሯል። በምክትል ሊቀመንበሩ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ አባላትና ከፍተኛ ካድሬዎች መስከረም 20/2017 ዓ.ም በመቐለ ውይይት ማካሄድ ጀምሯል። ውይይቱ ለሁለት የተከፈለው ድርጅት ለማዳንና የትግራይ ህዝብ…
#TPLF
" ህጋዊ እና ትክክለኛ 14ኛ ጉባኤ ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ እንገኛለን " - በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት
" ህዝብ እና ህወሓት በማዳን የትግራይ ህዝብ ህልውና ማረጋገጥ " በሚል መሪ ቃል ሰብሰባ የተቀመጠው በምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት ሰብሰባውን ቀጥሏል።
የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት እና ከፍተኛ ካድሬዎች " ህዝብ እና ህወሓት በማዳን የትግራይ ህልውና ማረጋገጥ " በሚል ርእስ በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ተወያይተዋል።
በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ ህወሓት ህጋዊ እና ትክክለኛ የድርጅቱ 14ኛ ጉባኤ ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅት በመደረግ ላይ መሆኑ በውይይት መድረኩ ገልጿል።
" ድርጅቱ አሁን ለደረሰበት የመከፋፈል አደጋ ዋና መንስኤው በድርጅቱ ስር የሰደደው ፀረ ዴሞክራሲ አካሄድና ተጠያቂነት አለመኖር ነው " ብለዋል ተሳታፊዎቹ።
" የድርጅትና የመንግስት አሰራር መደባላለቅ ይቁም " በማለት አቋም የያዘው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ቡድን " በነበረው ይቀጥል " ከሚለው በዶ/ር ደብረፅዮን የሚመራው ቡድን እንደ አንድ የመለያያ ነጥብ ሆኖ በመድረኩ ውይይት እንደተካሄደበት ታውቋል።
በዶ/ር ደብረፅዮን የተመራው 14ኛው ጉባኤ እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቦለት ያልተቀበለው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው በዱን አሁን በተራው " ህጋዊና ትክክለኛ " በማለት ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅት እያደረገለት በሚገኘው 14ኛው ጉባኤ ከዶ/ር ደብረፅዮን ጎን የወገኑት " ከያዙት የተሳሳተ መንገድ በመውጣት ጉባኤው ላይ እንዲሳተፉ " ከወዲሁ ጥሪ አቅርቧል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል መሪነት የተካሄደው ጉባኤ ቀደም ብሎ ጉባኤውም ሆነ ውሳኔዎቹ ቅቡልነት እንደሌለው ማሳወቁ መዘገባችን ይታወሳል ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።
#TikvahEthiopiaMekelleFamily
@tikvahethiopia
" ህጋዊ እና ትክክለኛ 14ኛ ጉባኤ ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ እንገኛለን " - በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት
" ህዝብ እና ህወሓት በማዳን የትግራይ ህዝብ ህልውና ማረጋገጥ " በሚል መሪ ቃል ሰብሰባ የተቀመጠው በምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት ሰብሰባውን ቀጥሏል።
የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት እና ከፍተኛ ካድሬዎች " ህዝብ እና ህወሓት በማዳን የትግራይ ህልውና ማረጋገጥ " በሚል ርእስ በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ተወያይተዋል።
በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ ህወሓት ህጋዊ እና ትክክለኛ የድርጅቱ 14ኛ ጉባኤ ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅት በመደረግ ላይ መሆኑ በውይይት መድረኩ ገልጿል።
" ድርጅቱ አሁን ለደረሰበት የመከፋፈል አደጋ ዋና መንስኤው በድርጅቱ ስር የሰደደው ፀረ ዴሞክራሲ አካሄድና ተጠያቂነት አለመኖር ነው " ብለዋል ተሳታፊዎቹ።
" የድርጅትና የመንግስት አሰራር መደባላለቅ ይቁም " በማለት አቋም የያዘው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ቡድን " በነበረው ይቀጥል " ከሚለው በዶ/ር ደብረፅዮን የሚመራው ቡድን እንደ አንድ የመለያያ ነጥብ ሆኖ በመድረኩ ውይይት እንደተካሄደበት ታውቋል።
በዶ/ር ደብረፅዮን የተመራው 14ኛው ጉባኤ እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቦለት ያልተቀበለው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው በዱን አሁን በተራው " ህጋዊና ትክክለኛ " በማለት ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅት እያደረገለት በሚገኘው 14ኛው ጉባኤ ከዶ/ር ደብረፅዮን ጎን የወገኑት " ከያዙት የተሳሳተ መንገድ በመውጣት ጉባኤው ላይ እንዲሳተፉ " ከወዲሁ ጥሪ አቅርቧል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል መሪነት የተካሄደው ጉባኤ ቀደም ብሎ ጉባኤውም ሆነ ውሳኔዎቹ ቅቡልነት እንደሌለው ማሳወቁ መዘገባችን ይታወሳል ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።
#TikvahEthiopiaMekelleFamily
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray " የህወሓትን ህጋዊነት መመለስ አስመልክቶ ከፌደራል መንግስት እና የአፍሪካ ህብረት ፓነል የሚወያይ ልኡክ እንደ አዲስ ይደራጃል ሲል " በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ ህወሓት ገለጸ። በህወሓት ምክትል ሊቀመንበር የሚመራው ህወሓት ከመስከረም 20 አስከ 22 /2017 ዓ.ም ለሦስት ቀናት ያካሄደውን የማእከላዊ ኮሚቴ እና የከፍተኛ ካድሬዎች ስብሰባ ማጠቃለሉ በማስመልከት የአቋም መግለጫ አውጥቷል። …
#TPLF
" ህዝብ በማደናገር ላይ ይገኛሉ " - በዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት የማዕከላዊ ቁጥጥር ኮሚሽን
በህወሓት አመራሮች መካከል ያለው ክፍፍል ተቀራርቦ ከመፈታት ይልቅ ከቀን ወደ ቀን ይበልጥ እየተካረረ መጥቷል።
" ከህወሓት አባልነት የተባረሩ በማንኛውም ቦታና ጊዜ በህወሓት ስም ፓለቲካዊ ስራና እንቅስቃሴ ማድረግ አይችሉም " ሲል በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት የማእከላዊ ቁጥጥር ኮሚሽን አሳውቋል።
የቁጥጥር ኮሚሽኑ ባወጣው የአቋም መግለጫ ፥ ጉባኤ ያካሄደው በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት " ህጋዊ ነው " ብሏል።
" የህወሓት መተዳደሪያ ደንብ አንቀፅ 8 ቁጥር 4 በውሳኔ አሰጣጥ ላይ አነስተኛ ቁጥር ያላቸው በብዙሃን ተገዢ መሆን እንዳለባቸው ያስቀምጣል " ያለው መግለጫው " በዚሁ መሰረት በ14ኛው የህወሓት ጉባኤ ከጠቅላላ ተሳታፊ 83 በመቶ ጉባኤተኛ የተገኘበት " ህጋዊ ነው !! " ብሎታል።
ስለሆነም " ህጋዊ አለመሆኑን እያወቀ ህጋዊ መስሎ ማደናገር አግባብነት እና ተቀባይነት ያለው አይደለም " ሲል በምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራውን ህወሓት ከሷል።
" ከጉባኤ ራሳችን አግልለናል ወይም ወደ ጉባኤ አንገባም ያሉት በድርጅቱ መተዳደሪያ ህገ ደንብ መሰረት ከድርጅት አባልነታቸው እንደተባረሩ እውነት ነው ፤ በተግባር ግን የህወሓት ስም ፣ አርማ ፣ ሎጎ እና የድርጅቱ ሃላፊነት በመጠቀም ህዝብ በማድናገር ላይ ተጠምደዋል " ብሏል የማእከላዊ የቁጥጥር ኮሚሽን መግለጫ።
" ከጉባኤ በመሸሽ ሁሉም አይነት ክህደት በድርጅቱ ላይ ፈፅመህ ስታበቃ እኔ ህወሓትን ነኝ የሚል የከሰረ የማደናገር ፓለቲካ ማራመድ ህጋዊ ፣ ፓለቲካዊ ፣ ሞራላዊ እና ታሪካዊ ተጠያቂነት የሚያስከትል ሆኖ አግኝተነዋል " ሲል አክሏል።
" የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ከድርጅቱ የተባረሩት አካላት #ከያዙት_ፓለቲካዊ_ስልጣን_እንዲነሱ ፤ በህወሓት ስም የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ እንዲያቆሙ የማድረግ ሃላፊነቱን እንዲወጣ እንጠይቃለን " ብሏል።
ቁጥጥር ኮሚሽኑ ፥ " ህዝብ በማድናገር ላይ ይገኛሉ " ሲል ክስ ያቀረበባቸው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራውን የህወሓት ቡድን " ህዝብ እንዲታገላቸው " ሲል ጥሪ አስተላልፏል።
" ህወሓት ለ2 እንደተከፈለ ተደርጎ የሚቀርበው ተረክ ከህወሓት አልፎ ህዝብ ስለሚጎዳ በፍጥነት መታረም አለበት " ብሏል።
በምክትል ሊቀ-መንበር ጌታቸው ረዳ የሚመራ ህወሓት መስከረም 23 /2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ " የህወሓት ህጋዊነት መመለስ አስመልክቶ ከፌደራል መንግስት እና የአፍሪካ ህብረት ፓነል የሚወያይ ልኡክ እንደ አዲስ ይደራጃል " ማለቱን መዘገባችን ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ህዝብ በማደናገር ላይ ይገኛሉ " - በዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት የማዕከላዊ ቁጥጥር ኮሚሽን
በህወሓት አመራሮች መካከል ያለው ክፍፍል ተቀራርቦ ከመፈታት ይልቅ ከቀን ወደ ቀን ይበልጥ እየተካረረ መጥቷል።
" ከህወሓት አባልነት የተባረሩ በማንኛውም ቦታና ጊዜ በህወሓት ስም ፓለቲካዊ ስራና እንቅስቃሴ ማድረግ አይችሉም " ሲል በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት የማእከላዊ ቁጥጥር ኮሚሽን አሳውቋል።
የቁጥጥር ኮሚሽኑ ባወጣው የአቋም መግለጫ ፥ ጉባኤ ያካሄደው በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት " ህጋዊ ነው " ብሏል።
" የህወሓት መተዳደሪያ ደንብ አንቀፅ 8 ቁጥር 4 በውሳኔ አሰጣጥ ላይ አነስተኛ ቁጥር ያላቸው በብዙሃን ተገዢ መሆን እንዳለባቸው ያስቀምጣል " ያለው መግለጫው " በዚሁ መሰረት በ14ኛው የህወሓት ጉባኤ ከጠቅላላ ተሳታፊ 83 በመቶ ጉባኤተኛ የተገኘበት " ህጋዊ ነው !! " ብሎታል።
ስለሆነም " ህጋዊ አለመሆኑን እያወቀ ህጋዊ መስሎ ማደናገር አግባብነት እና ተቀባይነት ያለው አይደለም " ሲል በምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራውን ህወሓት ከሷል።
" ከጉባኤ ራሳችን አግልለናል ወይም ወደ ጉባኤ አንገባም ያሉት በድርጅቱ መተዳደሪያ ህገ ደንብ መሰረት ከድርጅት አባልነታቸው እንደተባረሩ እውነት ነው ፤ በተግባር ግን የህወሓት ስም ፣ አርማ ፣ ሎጎ እና የድርጅቱ ሃላፊነት በመጠቀም ህዝብ በማድናገር ላይ ተጠምደዋል " ብሏል የማእከላዊ የቁጥጥር ኮሚሽን መግለጫ።
" ከጉባኤ በመሸሽ ሁሉም አይነት ክህደት በድርጅቱ ላይ ፈፅመህ ስታበቃ እኔ ህወሓትን ነኝ የሚል የከሰረ የማደናገር ፓለቲካ ማራመድ ህጋዊ ፣ ፓለቲካዊ ፣ ሞራላዊ እና ታሪካዊ ተጠያቂነት የሚያስከትል ሆኖ አግኝተነዋል " ሲል አክሏል።
" የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ከድርጅቱ የተባረሩት አካላት #ከያዙት_ፓለቲካዊ_ስልጣን_እንዲነሱ ፤ በህወሓት ስም የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ እንዲያቆሙ የማድረግ ሃላፊነቱን እንዲወጣ እንጠይቃለን " ብሏል።
ቁጥጥር ኮሚሽኑ ፥ " ህዝብ በማድናገር ላይ ይገኛሉ " ሲል ክስ ያቀረበባቸው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራውን የህወሓት ቡድን " ህዝብ እንዲታገላቸው " ሲል ጥሪ አስተላልፏል።
" ህወሓት ለ2 እንደተከፈለ ተደርጎ የሚቀርበው ተረክ ከህወሓት አልፎ ህዝብ ስለሚጎዳ በፍጥነት መታረም አለበት " ብሏል።
በምክትል ሊቀ-መንበር ጌታቸው ረዳ የሚመራ ህወሓት መስከረም 23 /2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ " የህወሓት ህጋዊነት መመለስ አስመልክቶ ከፌደራል መንግስት እና የአፍሪካ ህብረት ፓነል የሚወያይ ልኡክ እንደ አዲስ ይደራጃል " ማለቱን መዘገባችን ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia