#update ድሬዳዋ⬇️
የፀረ- ሰላም ሃይሎችን ድብቅ አጀንዳ ነቅተው በመከላከልና ለዘመናት የገነቡትን #ፍቅር በማቆየት የተጀመረውን አገራዊ የለውጥ ሂደት ከዳር ለማድረስ እንደሚሰሩ የድሬዳዋ #ገንደ_ተስፋ ወጣቶችና ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ወጣቶቹ #ከፖሊስ ጋር በመስራትና ድብቅ አጀንዳ ያነገቡ አካላትን ሴራ በማክሸፍ ለአካባቢያቸው ለሰላም መስፈን ግንባር ደቀም ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡም ገልፀዋል፡፡
በድሬዳዋ ልዩ ስሙ ገንደ ተስፋ በተባለ አካባቢ በመኖሪያ ቤቶች ላይ ማንነታቸው ለጊዜው ባልታወቁ አካላት ልዩ #የቀለም ምልክት መቀባትን ተከትሎ በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች የተከሰተው ግጭት እዚህም ሊፈጠር ይሆን በሚል ነዋሪዎች ስጋት ውስጥ ገብተው እንደነበር ይታወሳል።
ይህንን ተከትሎ ለችግሩ #መፍትሄ ለማምጣት ውይይት ያደረጉት የአካባቢው ወጣቶችና ነዋሪዎች በድሬዳዋ የሚኖሩ ብሔር ብሔረሰቦች
ለዘመናት የገነቡት ፍቅር ድብቅ አላማን ባነገቡ ፀረ-ሰላም አካላት ሴራ እንደማይደናቀፍ ተናግረዋል።
©ኤዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የፀረ- ሰላም ሃይሎችን ድብቅ አጀንዳ ነቅተው በመከላከልና ለዘመናት የገነቡትን #ፍቅር በማቆየት የተጀመረውን አገራዊ የለውጥ ሂደት ከዳር ለማድረስ እንደሚሰሩ የድሬዳዋ #ገንደ_ተስፋ ወጣቶችና ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ወጣቶቹ #ከፖሊስ ጋር በመስራትና ድብቅ አጀንዳ ያነገቡ አካላትን ሴራ በማክሸፍ ለአካባቢያቸው ለሰላም መስፈን ግንባር ደቀም ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡም ገልፀዋል፡፡
በድሬዳዋ ልዩ ስሙ ገንደ ተስፋ በተባለ አካባቢ በመኖሪያ ቤቶች ላይ ማንነታቸው ለጊዜው ባልታወቁ አካላት ልዩ #የቀለም ምልክት መቀባትን ተከትሎ በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች የተከሰተው ግጭት እዚህም ሊፈጠር ይሆን በሚል ነዋሪዎች ስጋት ውስጥ ገብተው እንደነበር ይታወሳል።
ይህንን ተከትሎ ለችግሩ #መፍትሄ ለማምጣት ውይይት ያደረጉት የአካባቢው ወጣቶችና ነዋሪዎች በድሬዳዋ የሚኖሩ ብሔር ብሔረሰቦች
ለዘመናት የገነቡት ፍቅር ድብቅ አላማን ባነገቡ ፀረ-ሰላም አካላት ሴራ እንደማይደናቀፍ ተናግረዋል።
©ኤዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA via @like
ይሄን ሰው አማራ ኧረ ሚለው ማነው
ይሄን ሰው ኦሮሞ ኧረ ሚለው ማነው
ይሄን ሰው ጉራጌ ኧረ ሚለው ማነው
ይሄ ሰው ከትግራይ ኧረ ሚለው ማነው
ይሄ ሰው ከደቡብ ኧረ ሚለው ማነው
ቢለያይም ቋንቋው ደማችን አንድ ነው።
💉💉ደማችን አንድ ነው💉💉
💚💛❤️ሰላም እደሩ💚💛❤️
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ይሄን ሰው ኦሮሞ ኧረ ሚለው ማነው
ይሄን ሰው ጉራጌ ኧረ ሚለው ማነው
ይሄ ሰው ከትግራይ ኧረ ሚለው ማነው
ይሄ ሰው ከደቡብ ኧረ ሚለው ማነው
ቢለያይም ቋንቋው ደማችን አንድ ነው።
💉💉ደማችን አንድ ነው💉💉
💚💛❤️ሰላም እደሩ💚💛❤️
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ደብረ ማርቆስ⬆️
ኢትዮጵያና ኤርትራ ለሁለት አስርት ዓመታት ያህል ያሳለፉትን ኩርፊያ ይበቃል በማለት የሰላምና የወዳጅነት ስምምነት መፈረማቸውን ተከትሎ በርካታ በጎ ተግባራትን በመስማት ላይ እንገኛለን፡፡
ከወደ ደብረማርቆስ የተሰማው ጉዳይም የዚሁ አዲስ ጅምር አንዱ አካል ነው፡፡
የደብረማርቆስ ህዝብ ከዓመታት መለያየት በኋላ #ከኤርትራ የመጡ አብሮ አደጎቹን ተቀብሏል፡፡
ከ20 ዓመታት በፊት ኑሯቸውን በደብረ ማርቆስ ከተማ አድርገው ነበር፤ የወቅቱ አስከፊ የፖለቲካ ውሳኔ ግን በአካል እንጂ በመንፈስ ካልተለዩት ህዝብ ጋር ሳይፈልጉ ተገደው እንዲለዩ አደረጋቸው፡፡
ዛሬ ታሪክ ተቀይሯል መለያየት በአብሮነት፤ ጥላቻ #በፍቅር ድል ተነስተዋል፡፡
እናም አቶ ተስፋ ሚካኤል ግደይና አቶ መድሃኔ ግደይ ወደ ቀድሞ ከተማቸው ተመልሰዋል፡፡ ደብረ ማርቆስም የትናንት ልጆቿን የዛሬ እንግዶቿን እልል…! ብላ
ተቀብላለች፡፡
ከአቀባበሉ በኋላ ደግሞ የህዝቡን ቃል አክባሪነት እና ታማኝነት ያስመሰከረ አንድ አስገራሚ ዕውነታ ተገለጠ፡፡
ወደ ኤርትራ በሄዱበት ወቅት ትተውት የሄዱት ቤት ተጠብቆ ቆይቶላቸው ነበርና ህዝቡ ለባለቤቶቹ አስረክቧል፡፡
የኢትዮጵዊነት እሴትም በተግባር ታየ በተጨማሪም ህዝቡ ለኤርትራዊያኑ ወንድሞቹ የጋቢ ስጦታም አበርክቶላቸዋል።
©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢትዮጵያና ኤርትራ ለሁለት አስርት ዓመታት ያህል ያሳለፉትን ኩርፊያ ይበቃል በማለት የሰላምና የወዳጅነት ስምምነት መፈረማቸውን ተከትሎ በርካታ በጎ ተግባራትን በመስማት ላይ እንገኛለን፡፡
ከወደ ደብረማርቆስ የተሰማው ጉዳይም የዚሁ አዲስ ጅምር አንዱ አካል ነው፡፡
የደብረማርቆስ ህዝብ ከዓመታት መለያየት በኋላ #ከኤርትራ የመጡ አብሮ አደጎቹን ተቀብሏል፡፡
ከ20 ዓመታት በፊት ኑሯቸውን በደብረ ማርቆስ ከተማ አድርገው ነበር፤ የወቅቱ አስከፊ የፖለቲካ ውሳኔ ግን በአካል እንጂ በመንፈስ ካልተለዩት ህዝብ ጋር ሳይፈልጉ ተገደው እንዲለዩ አደረጋቸው፡፡
ዛሬ ታሪክ ተቀይሯል መለያየት በአብሮነት፤ ጥላቻ #በፍቅር ድል ተነስተዋል፡፡
እናም አቶ ተስፋ ሚካኤል ግደይና አቶ መድሃኔ ግደይ ወደ ቀድሞ ከተማቸው ተመልሰዋል፡፡ ደብረ ማርቆስም የትናንት ልጆቿን የዛሬ እንግዶቿን እልል…! ብላ
ተቀብላለች፡፡
ከአቀባበሉ በኋላ ደግሞ የህዝቡን ቃል አክባሪነት እና ታማኝነት ያስመሰከረ አንድ አስገራሚ ዕውነታ ተገለጠ፡፡
ወደ ኤርትራ በሄዱበት ወቅት ትተውት የሄዱት ቤት ተጠብቆ ቆይቶላቸው ነበርና ህዝቡ ለባለቤቶቹ አስረክቧል፡፡
የኢትዮጵዊነት እሴትም በተግባር ታየ በተጨማሪም ህዝቡ ለኤርትራዊያኑ ወንድሞቹ የጋቢ ስጦታም አበርክቶላቸዋል።
©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጋምቤላ⬆️
የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የተለያዩ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያዎችን ከአንድ ተጠርጣሪ ግለሰብ ጋር በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታወቀ።
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ከሚሽነር ቾል ኩን ለኢዜአ እንደገለጹት ህገ ወጥ መሳሪያዎችን ከትናንት በስቲያ በጋምቤላ ከተማ በቁጥጥር ሥር ማዋል የተቻለው #ከላሬ ወረዳ ወደ #ጋምቤላ ከተማ ለማስገባት ሲሞክር ነው።
በፖሊስ ከተያዙት የጦር መሳሪያዎች መካከል አራት ሽጉጦች፣ አንድ ታጣፊ ክላሽ፣ አንድ ሺህ 133 የተለያዩ ዓይነት ጥይቶች ይገኙበታል።
ከህገ ወጥ የጦር መሳሪያዎች ጋር ከ20 ሺህ 600 ብር በላይ #ገንዘብ ፖሊስ አብሮ በቁጥጥር ሥር መዋሉንም ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።
በተጠርጣሪው ላይ በተደረገው ማጣራትም የጦር መሳሪያዎቹን ወደ #መሀል ሀገር የማስገባት እቅድ እንደነበረውም ኮሚሽነሩ ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት በተጠርጣሪ ግለሰቡ ላይ ማስረጃ የማሰባሰብና የማጠራት ሥራ እየተካሄደ እንደሚገኝ ጠቁመው፣ “የምርመራ ሂደቱ እንደተጠናቀቀ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ይላካል” ብለዋል።
ክልሉ በተለይም ከደቡብ ሱዳን ጋር በስፋት በድንበር የሚዋሰን ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በርካታ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ወደ ክልሉ እየገባ መሆኑን የገለጹት ኮሚሽነሩ፣ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርን ለመግታት በሚደረገው ጥረት የህዝቡ #ተሳተፎውን እንዲያጠናክር
ጠይቀዋል።
ህግ ወጥ የጦር መሳሪዎች በሀገሪቱ ላይ ሊያስከትሉ የሚችሉትን ማህበራዊና ኢኮኖሚዊ ችግሮች በመገንዘብ ኮሚሽነሩ የህዝብ ንቅናቄ በመፍጠር በጋራ #ለመከላከል ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
©ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የተለያዩ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያዎችን ከአንድ ተጠርጣሪ ግለሰብ ጋር በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታወቀ።
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ከሚሽነር ቾል ኩን ለኢዜአ እንደገለጹት ህገ ወጥ መሳሪያዎችን ከትናንት በስቲያ በጋምቤላ ከተማ በቁጥጥር ሥር ማዋል የተቻለው #ከላሬ ወረዳ ወደ #ጋምቤላ ከተማ ለማስገባት ሲሞክር ነው።
በፖሊስ ከተያዙት የጦር መሳሪያዎች መካከል አራት ሽጉጦች፣ አንድ ታጣፊ ክላሽ፣ አንድ ሺህ 133 የተለያዩ ዓይነት ጥይቶች ይገኙበታል።
ከህገ ወጥ የጦር መሳሪያዎች ጋር ከ20 ሺህ 600 ብር በላይ #ገንዘብ ፖሊስ አብሮ በቁጥጥር ሥር መዋሉንም ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።
በተጠርጣሪው ላይ በተደረገው ማጣራትም የጦር መሳሪያዎቹን ወደ #መሀል ሀገር የማስገባት እቅድ እንደነበረውም ኮሚሽነሩ ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት በተጠርጣሪ ግለሰቡ ላይ ማስረጃ የማሰባሰብና የማጠራት ሥራ እየተካሄደ እንደሚገኝ ጠቁመው፣ “የምርመራ ሂደቱ እንደተጠናቀቀ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ይላካል” ብለዋል።
ክልሉ በተለይም ከደቡብ ሱዳን ጋር በስፋት በድንበር የሚዋሰን ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በርካታ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ወደ ክልሉ እየገባ መሆኑን የገለጹት ኮሚሽነሩ፣ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርን ለመግታት በሚደረገው ጥረት የህዝቡ #ተሳተፎውን እንዲያጠናክር
ጠይቀዋል።
ህግ ወጥ የጦር መሳሪዎች በሀገሪቱ ላይ ሊያስከትሉ የሚችሉትን ማህበራዊና ኢኮኖሚዊ ችግሮች በመገንዘብ ኮሚሽነሩ የህዝብ ንቅናቄ በመፍጠር በጋራ #ለመከላከል ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
©ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia