TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኢንጂነር ታከለ ኡማ ለአምባ መርጃ ማህበር ቤት ለመስጠት ቃል ገቡ!

ኢ/ር ታከለ ኡማ በዛሬው ዕለት አምባ ትምህርት ለተቸገሩ መርጃ ማህበርን ጎብኝተዋል፡፡ ከ9 ዓመት በፊት በተለያዩ ህፃናት ማሳደጊያዎች አድገው በተለያዩ ስራዎች ላይ በተሰማሩ ግለስቦች የተቋቋመው ማእከሉ ወላጅ አልባ እና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ አካል ጉዳተኛ ህፃናትን ተቀብሎ #የምገባ አገልግሎትን ያካተተ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ ይሁን እንጂ ማእከሉ ባጋጠመው #የገንዘብ_እጥረት የቤት ኪራይ ለመክፈል መቸገሩን እና ሊዘጋ መቃረቡን የተመለከቱት ኢንጂነር ታከለ ኡማ ማእከሉ ባለበት አካባቢ የሚገኝ እና ለበርካታ ዓመታት ተዘግቶ የተቀመጠ ቤት ለማእከሉ በስጦታ ለማስረከብ ቃል ገብተዋል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ መሰል ትውልድ ላይ የሚሰሩ ማእከላትን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

ምንጭ፡- የከንቲባ ጽ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia