#Ethiopia #USA
በአሜሪካ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ጄ ትራምፕ ጋር በነጩ ቤተመንግስት የመጀመሪያ ግንኙነታቸዉን አካሂደዋል።
አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም ነጩ ቤተመንግስት ሲደርሱ በኢትዮጵያና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ግንኙነት የሚያንጸባርቅ ዲፕሎማሲያዊ አቀባበል እንደተደረገላቸው በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳውቋል።
" ይኸው ግንኙነት በቀጣይ ጊዜአት ለሚደረጉ በርካታ ውይይቶች መጠናከር ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል " ያለው ኤባሲው " ኢትዮጵያና አሜሪካ ከ120 ዓመታት በላይ የዘለቀ ጠንካራ ግንኙነት ያላቸው ናቸው በሁለቱ አገራት መካከል እንደ ሰላም፣ ጸጥታና ኢኮኖሚያዊ መስኮች ጠንካራ አጋርነት ከመፍጠር አንጻር ያሉ ዕድሎችም ሰፊ ናቸው " ብሏል።
አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም በውይይቱ ወቅት የተገኙትን ስቴት ሴክሬተሪ ማርኮ ሩቢዮ ጋርም ተገናኝተዋል።
Photo credit: The White House
@tikvahethiopia
በአሜሪካ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ጄ ትራምፕ ጋር በነጩ ቤተመንግስት የመጀመሪያ ግንኙነታቸዉን አካሂደዋል።
አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም ነጩ ቤተመንግስት ሲደርሱ በኢትዮጵያና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ግንኙነት የሚያንጸባርቅ ዲፕሎማሲያዊ አቀባበል እንደተደረገላቸው በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳውቋል።
" ይኸው ግንኙነት በቀጣይ ጊዜአት ለሚደረጉ በርካታ ውይይቶች መጠናከር ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል " ያለው ኤባሲው " ኢትዮጵያና አሜሪካ ከ120 ዓመታት በላይ የዘለቀ ጠንካራ ግንኙነት ያላቸው ናቸው በሁለቱ አገራት መካከል እንደ ሰላም፣ ጸጥታና ኢኮኖሚያዊ መስኮች ጠንካራ አጋርነት ከመፍጠር አንጻር ያሉ ዕድሎችም ሰፊ ናቸው " ብሏል።
አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም በውይይቱ ወቅት የተገኙትን ስቴት ሴክሬተሪ ማርኮ ሩቢዮ ጋርም ተገናኝተዋል።
Photo credit: The White House
@tikvahethiopia
❤958👏161😡78😭64🤔41🙏38🕊22😢17😱9🥰4
#ETHIOPIA #USA
ዛሬ ጥዋት ላይ የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ከአሜሪካ ማሪን ኮርፕስ ጄኔራል እና አፍሪኮም አዛዥ ከሆኑት ጄነራል ማይክል ላንግሌይ ጋር ውይይት ማድረጋቸውን አሳውቀዋል።
ውይይቱ የጋራ ፍላጎት በሆኑ የሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ እንዳተኮረ አመልክተዋል።
አሜሪካም ጄነራሏ ከኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር ውይይት ማድረጉን አሳውቃለች።
ውይይቱ በአፍሪካ ቀንድ የአልሸባብ እና የአይኤስ የሽብር ስጋትን መከላከል ላይ ያተኮረ እንደነበረም ጠቁማለች።
በሌላ በኩል ፥ የአሜሪካ በአፍሪካ ዕዝ አዛዥ (AFRICOM) ጀነራል ማይክል ላንግሌይ ኢትዮጵያን እንደጎበኙ አሜሪካ አሳውቃለች።
በዚህም ወቅት ከኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ጋር መምከራቸውን ገልጻለች።
ምክክራቸው ፦
- ቀጠናዊ ሰላምና ደህንነት፣
- በቀጠናው ላይ ያሉ ችግሮችን በጋራ የመፍታት ጥረት፣
- በሱማሊያ ያለውን ሽብርተኝነት መዋጋት ላይ፣
- በአፍሪካ ቀንድ የረዥም ጊዜ መረጋጋትን ስለ መደገፍ ትኩረት ያደረገ እንደሆነ አሜሪካ አሳውቃለች።
የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ምን አለ ?
ሀገር መከላከያ የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የአሜሪካ በአፍሪካ ዕዝ አዛዥ (አፍሪኮም) ጀነራል ሚካሄል ላንግሌይ የተመራ ልዑክን ተቀብለው እንዳነጋገሩ ገልጿል።
ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ " አሜሪካና ኢትዮጵያ ከመቶ ዓመት በላይ ግንኙነት አላቸው " ያሉ ሲሆን " ሁለቱ ወዳጅ ሀገራት በመከላከያ ዘርፉ በቀጣይም በጋራ ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መግባባት ላይ ደርሰዋል " ሲሉ ገልፀዋል።
በውይይቱ በቀጠናው ባለው ሁኔታ የጋራ መግባባት የተያዘበትና በተለይም በቀይ ባህር ፣ በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ በሚታዩ የፀጥታ ጉዳዮች ላይ ለጋራ ተጠቃሚነት በጋራ ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መስማማታቸውን አመልክተዋል።
የአፍሪኮም አዛዥ ጀነራል ሚካኤል ላንግለይ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድና በቀጠናው ከፍተኛ ሚና ያላት ሀገር መሆኗን እንደተናገሩ መከላከያ አሳውቋል።
በቀጣይ በወታደራዊና በፀጥታ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን እንደተናገሩም አክሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
Photo ፦ PM Office & US Embassy
@tikvahethiopia
ዛሬ ጥዋት ላይ የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ከአሜሪካ ማሪን ኮርፕስ ጄኔራል እና አፍሪኮም አዛዥ ከሆኑት ጄነራል ማይክል ላንግሌይ ጋር ውይይት ማድረጋቸውን አሳውቀዋል።
ውይይቱ የጋራ ፍላጎት በሆኑ የሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ እንዳተኮረ አመልክተዋል።
አሜሪካም ጄነራሏ ከኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር ውይይት ማድረጉን አሳውቃለች።
ውይይቱ በአፍሪካ ቀንድ የአልሸባብ እና የአይኤስ የሽብር ስጋትን መከላከል ላይ ያተኮረ እንደነበረም ጠቁማለች።
በሌላ በኩል ፥ የአሜሪካ በአፍሪካ ዕዝ አዛዥ (AFRICOM) ጀነራል ማይክል ላንግሌይ ኢትዮጵያን እንደጎበኙ አሜሪካ አሳውቃለች።
በዚህም ወቅት ከኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ጋር መምከራቸውን ገልጻለች።
ምክክራቸው ፦
- ቀጠናዊ ሰላምና ደህንነት፣
- በቀጠናው ላይ ያሉ ችግሮችን በጋራ የመፍታት ጥረት፣
- በሱማሊያ ያለውን ሽብርተኝነት መዋጋት ላይ፣
- በአፍሪካ ቀንድ የረዥም ጊዜ መረጋጋትን ስለ መደገፍ ትኩረት ያደረገ እንደሆነ አሜሪካ አሳውቃለች።
የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ምን አለ ?
ሀገር መከላከያ የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የአሜሪካ በአፍሪካ ዕዝ አዛዥ (አፍሪኮም) ጀነራል ሚካሄል ላንግሌይ የተመራ ልዑክን ተቀብለው እንዳነጋገሩ ገልጿል።
ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ " አሜሪካና ኢትዮጵያ ከመቶ ዓመት በላይ ግንኙነት አላቸው " ያሉ ሲሆን " ሁለቱ ወዳጅ ሀገራት በመከላከያ ዘርፉ በቀጣይም በጋራ ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መግባባት ላይ ደርሰዋል " ሲሉ ገልፀዋል።
በውይይቱ በቀጠናው ባለው ሁኔታ የጋራ መግባባት የተያዘበትና በተለይም በቀይ ባህር ፣ በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ በሚታዩ የፀጥታ ጉዳዮች ላይ ለጋራ ተጠቃሚነት በጋራ ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መስማማታቸውን አመልክተዋል።
የአፍሪኮም አዛዥ ጀነራል ሚካኤል ላንግለይ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድና በቀጠናው ከፍተኛ ሚና ያላት ሀገር መሆኗን እንደተናገሩ መከላከያ አሳውቋል።
በቀጣይ በወታደራዊና በፀጥታ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን እንደተናገሩም አክሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
Photo ፦ PM Office & US Embassy
@tikvahethiopia
❤1.23K😡410🙏51🤔50🕊36😭30👏18💔17😢12
#Ethiopia
" ኢትዮጵያ በሚቀጥለው መስከረም ወር ላይ የመጀመሪያ ዙር የጋዝ ምርት ለገቢያ ታቀርባለች " ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስት ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ይህንን ጉዳይ የተናገሩት ከሚዲያ እና ከኮሚኒኬሽን ባለሞያዎች ጋር ባደረጉት የውይይት መድረክ ነው።
" ላለፉት ዓመታት በዚህ ጉዳይ ምን ሲሰራ እንደነበር አታውቁም " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " ከነገርናችሁ ከውስጥም ከውጭም ጣጣው ስለሚበዛ ነው ዝም ብለን የሰራነው " ሲሉ ገልጸዋል።
ይህ ምርት የት አከባቢ እንደሆነ በቀጥታ ባይናገሩም በንግግራቸው ወቅት " ላለፉት ሁለት ሦስት ዓመታት እኔ የምጎበኘው ጋዙን ነው እናንተ የምታዩት ስንዴውን " ሲሉ ተናግረዋል።
" እስካሁን ያልነገርናችሁ በህዳሴ ላይ የከፈልነውን ዋጋ ከፍተኛ ስለሆነ ነው " ሲሉ ፕሮጀክቱ ላለፉት ዓመታት በተለያዩ መንገዶች በሚዲያው ከሚደርስበት ጫና ለመላቀቅ በዝምታ መስራታቸውን አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ኢትዮጵያ በሚቀጥለው መስከረም ወር ላይ የመጀመሪያ ዙር የጋዝ ምርት ለገቢያ ታቀርባለች " ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስት ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ይህንን ጉዳይ የተናገሩት ከሚዲያ እና ከኮሚኒኬሽን ባለሞያዎች ጋር ባደረጉት የውይይት መድረክ ነው።
" ላለፉት ዓመታት በዚህ ጉዳይ ምን ሲሰራ እንደነበር አታውቁም " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " ከነገርናችሁ ከውስጥም ከውጭም ጣጣው ስለሚበዛ ነው ዝም ብለን የሰራነው " ሲሉ ገልጸዋል።
ይህ ምርት የት አከባቢ እንደሆነ በቀጥታ ባይናገሩም በንግግራቸው ወቅት " ላለፉት ሁለት ሦስት ዓመታት እኔ የምጎበኘው ጋዙን ነው እናንተ የምታዩት ስንዴውን " ሲሉ ተናግረዋል።
" እስካሁን ያልነገርናችሁ በህዳሴ ላይ የከፈልነውን ዋጋ ከፍተኛ ስለሆነ ነው " ሲሉ ፕሮጀክቱ ላለፉት ዓመታት በተለያዩ መንገዶች በሚዲያው ከሚደርስበት ጫና ለመላቀቅ በዝምታ መስራታቸውን አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤3.25K😡738🤔343👏289😭150🙏101🕊57😢36😱31💔30🥰23
#Ethiopia
ኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት በቅርቡ ከናይጄሪያው ባለኃብት ዳንጎቴ ጋር እንደምትፈራረም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፈረንጆቹ ሐምሌ ወር አጋማሽ የስምምነት ፊርማው እንደሚደረግ የገለጹ ሲሆን " በቀጣይ 3 ዓመታት ኢትዮጵያ ማዳበሪያ ይኖራታል " ሲሉ በንግግራቸው ጠቅሰዋል።
ይህ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ በጎዴ አከባቢ እንደሚገባ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) የ3 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት መሆኑን መግለጻቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት በቅርቡ ከናይጄሪያው ባለኃብት ዳንጎቴ ጋር እንደምትፈራረም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፈረንጆቹ ሐምሌ ወር አጋማሽ የስምምነት ፊርማው እንደሚደረግ የገለጹ ሲሆን " በቀጣይ 3 ዓመታት ኢትዮጵያ ማዳበሪያ ይኖራታል " ሲሉ በንግግራቸው ጠቅሰዋል።
ይህ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ በጎዴ አከባቢ እንደሚገባ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) የ3 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት መሆኑን መግለጻቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤2.14K👏393😡162🤔115🙏77😭44🕊40😱31😢27💔17🥰9
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ የ2017 ዓ/ም #የአረንጓዴ_አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ዛሬ ተጀምሯል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ #TikvahEthiopiaFamilyAA @tikvahethiopia
#Ethiopia🌱
የ2017 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ዛሬ ተጀመረ።
በአጠቃላይ 7.5 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ዕቅድ ተይዟል።
በዛሬው ዕለት በወንዝ ዳርቻ ልማት አንዱ ክፍል በሆነው በእንጦጦ ዙሪያ ጠ/ሚ ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ፣ የናይጄሪያ ምክትል ፕረዚዳንት ካቲም ሼቲማን ጨምሮ የክልል አመራሮችና ሚኒስትሮች በተገኙበት የችግኝ ተከላ ተካሂዷል።
በዚህ ወቅት መልዕክት ያስተላለፉት ጠ/ሚ ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ፥ የሚስማማውን ችግኝ በሚስማማው ቦታ እንዲተከል ጥሪ አቅርበዋል።
የአረንጓዴ አሻራ በቀጣይ አመት ይጠናቀቃል የተባለ ሲሆን ኢትዮጵያ በአጠቃላይ በስምንት ዙር የችግኝ ተከላ መርኃግብር (የአረንጓዴ አሻራ ሲጠናቀቀ) የተከለቻቸውና የምትተክላቸው ችግኞች አጠቃላይ ብዛት 50 ቢሊዮን እንደሚደርሱ ይጠበቃል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የ2017 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ዛሬ ተጀመረ።
በአጠቃላይ 7.5 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል ዕቅድ ተይዟል።
በዛሬው ዕለት በወንዝ ዳርቻ ልማት አንዱ ክፍል በሆነው በእንጦጦ ዙሪያ ጠ/ሚ ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ፣ የናይጄሪያ ምክትል ፕረዚዳንት ካቲም ሼቲማን ጨምሮ የክልል አመራሮችና ሚኒስትሮች በተገኙበት የችግኝ ተከላ ተካሂዷል።
በዚህ ወቅት መልዕክት ያስተላለፉት ጠ/ሚ ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ፥ የሚስማማውን ችግኝ በሚስማማው ቦታ እንዲተከል ጥሪ አቅርበዋል።
የአረንጓዴ አሻራ በቀጣይ አመት ይጠናቀቃል የተባለ ሲሆን ኢትዮጵያ በአጠቃላይ በስምንት ዙር የችግኝ ተከላ መርኃግብር (የአረንጓዴ አሻራ ሲጠናቀቀ) የተከለቻቸውና የምትተክላቸው ችግኞች አጠቃላይ ብዛት 50 ቢሊዮን እንደሚደርሱ ይጠበቃል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤653😡397👏21😭19🕊15🤔14😱14🙏13💔6🥰3😢2
#Ethiopia
የንብረት ታክስ በክልሎች በሚቀጥለው በጀት ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ይደረጋል ተባለ።
የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ " በሚቀጥለው በጀት ዓመት ክልሎች የንብረት ታክስን ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ማድረግ ይጀምራሉ " አሉ።
ይህን ያሉት በህዝብ ተ/ም/ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 41ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው በፌዴራል መንግስት የ2018 ረቂቅ በጀት ላይ ከም/ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው።
" ከዚህ በፊት ባልተለመደ መልኩ እዳ እየከፈለ የሚገኘው መንግስት በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ገቢ እያገኘ መምጣቱን መጥቷል " ያሉ ሲሆን " ገቢ የማያስገኝ አገልግሎት አክሳሪ ነው " ብለዋል።
በአዲስ አበባ የንብረት ታክስ ክፍያ ተግባራዊ መደረጉን በማስታወስ " በሚቀጥለው በጀት ዓመት የንብረት ታክስ በክልሎች ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ማድረግ ይጀመራል " ነው ያሉት።
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
የንብረት ታክስ በክልሎች በሚቀጥለው በጀት ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ይደረጋል ተባለ።
የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ " በሚቀጥለው በጀት ዓመት ክልሎች የንብረት ታክስን ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ማድረግ ይጀምራሉ " አሉ።
ይህን ያሉት በህዝብ ተ/ም/ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 41ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው በፌዴራል መንግስት የ2018 ረቂቅ በጀት ላይ ከም/ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው።
" ከዚህ በፊት ባልተለመደ መልኩ እዳ እየከፈለ የሚገኘው መንግስት በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ገቢ እያገኘ መምጣቱን መጥቷል " ያሉ ሲሆን " ገቢ የማያስገኝ አገልግሎት አክሳሪ ነው " ብለዋል።
በአዲስ አበባ የንብረት ታክስ ክፍያ ተግባራዊ መደረጉን በማስታወስ " በሚቀጥለው በጀት ዓመት የንብረት ታክስ በክልሎች ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ማድረግ ይጀመራል " ነው ያሉት።
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
😡554❤333😭25💔19😱13👏9😢4🕊4
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ #ረቂቅአዋጅ የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ መሬትን በሊዝ በባለቤትነት መያዝ የሚያስችላቸው የአዋጅ ረቂቅ ነገ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይቀርባል። የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት " ባለቤት ' ወይም " ባለይዞታ " የሚሆኑበትን አግባብ ለመደንገግ የወጣው ይህ " የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበት " ወይም " ለመኖሪያ ቤት ግንባታ የሚውል መሬት የሚያገኙበትን…
#Ethiopia
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ሀገር ዜጎች የማይንቀሳቀስ የመኖሪያ ቤት ባለቤት የመሆን መብት አዋጅን አጽድቋል።
በምክር ቤቱ የከተማ፣ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ " መሬት የመንግስት እና የህዝብ እንደመሆኑ ለኢንቨስትመንት የሚመጡ ዜጎች መሬቱን የመሸጥ እና የመለወጥ መብት የላቸውም " ብሏል።
የኢትዮጵያዊያንን መብት በማይነካ መልኩ የውጭ ሀገር ዜጎች የመኖርያ ቤት ባለቤት በመሆን ኢንቨስትመንት ላይ እንዲሰማሩ ሥራዎች ይሰራሉ ሲል ገልጷል።
የውጭ ሀገር ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው በመኖሪያ ቤት ባለቤትነት ላይ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የተቀመጠው የገንዘብ መጠን 150 ሺህ ዶላር ነው።
የተቀመጠው የገንዘብ መጠን 150 ሺህ ዶላር ሲሆን በጊዜ ሂደት እየተሻሻለ ይሄዳል ተብሏል። #HoPR #FMC
@tikvahethiopia
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ሀገር ዜጎች የማይንቀሳቀስ የመኖሪያ ቤት ባለቤት የመሆን መብት አዋጅን አጽድቋል።
በምክር ቤቱ የከተማ፣ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ " መሬት የመንግስት እና የህዝብ እንደመሆኑ ለኢንቨስትመንት የሚመጡ ዜጎች መሬቱን የመሸጥ እና የመለወጥ መብት የላቸውም " ብሏል።
የኢትዮጵያዊያንን መብት በማይነካ መልኩ የውጭ ሀገር ዜጎች የመኖርያ ቤት ባለቤት በመሆን ኢንቨስትመንት ላይ እንዲሰማሩ ሥራዎች ይሰራሉ ሲል ገልጷል።
የውጭ ሀገር ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው በመኖሪያ ቤት ባለቤትነት ላይ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የተቀመጠው የገንዘብ መጠን 150 ሺህ ዶላር ነው።
የተቀመጠው የገንዘብ መጠን 150 ሺህ ዶላር ሲሆን በጊዜ ሂደት እየተሻሻለ ይሄዳል ተብሏል። #HoPR #FMC
@tikvahethiopia
❤420😭197😡164🤔21😱14🕊13😢8💔8🙏3🥰2
TIKVAH-ETHIOPIA
#HoPR🇪🇹 " 3.5 ቢሊየን ዶላር ከዚህ ቀደም የነበሩ መንግስታት የተበደሩትን ገንዘብ ያለፉትን ሶስት እና አራት አመታት ተደራድረን የእዳ ሽግሽግ እንዲኖር አድርገናል የገንዘብ ሚንስቴር በትላንትናው እለት በፈረንሳይ ተፈራርሟል" - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ። የበጀት አመቱን አፈጻጸም…
#Ethiopia 🇪🇹
#GERD🇪🇹
" መስከረም ላይ ዝናብ ጋብ ሲል ህዳሴን እናስመርቃለን !!! "
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በሚመለከት ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምን አሉ ?
" ህዳሴ አልቋል። ህዳሴን እናስመርቃለን። ህዳሴ ከመመረቁ በፊት ' ብንረብሽ ' ብለው የሚያስቡ ሰዎች አሉ ፤ እናስመርቃለን።
ህዳሴን እንዳይመረቅ ለማድረግ የሚያስችል ነገር አሁን የለም። የሚመረቀውም አሁን ነው ነገ ክረምቱ ሲያልቅ።
ለታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ያለኝ መልዕክት ህዳሴ ለሱዳን ህዳሴ ለግብፅ በረከት ነው። በፍጹም ጉዳት አያመጣባቸውም። ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ልማት ልማታቸው ነው ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ኢነርጂ ለሁሉም ጎረቤቶች የሚዳረስ ነው።
የኛ ግድብ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራትን የሚጎዳ ቢሆን ኖሮ ቱርካና አጀንዳ አይሆንም ነበር። ታስታውሳላችሁ ግቤ 3 ሲሰራ 'ቱርካና ይደርቃል የሚል ከፍተኛ ችግር ነበር። እንኳን ሊደርው ከግድቡ በኋላ ይኸው ሞልቶ እያስቸገረ ነው ያለው።
አሁንም ግብፅ ብትሄዱ የግብፅ አስዋን ግድብ አንድ ሊትር ውሃ አልቀነሰም። ወደፊትም ኢትዮጵያ እስከበለጸገች ድረስ እስካለች ድረስ የግብፅ ወንድሞቻችንን ጉዳት እኛ አናይም ተባብረን ከወንድሞቻች ጋር ማደግ እንፈልጋለን።
ግብፅ እንድትጎዳ ፣ ሱዳን እንድትጎዳ አንፈልግም። ኢነርጂውን በጋራ እንጠቀማለን ውሃውን በጋራ እንጠቀማለን ልማት በጋራ ይመጣል። ንግግር ካስፈለገ እንነጋገራለን ችግር የለም።
እኛ ለረጅም ጊዜ ስናነሳ የነበረው ' አትስሩ ' አትበሉን ነው ያልነው እንጂ በኛ ገንዘብ በኛ ምድር የሚሰራውም ስራ አታግዱ ነው ያልነው እንጂ ያን እስካልከለከሉ ድረስ አሁንም ከግብፆች ጋር ለመነጋገር፣ ለመደራደር ፣ ለመስራት ኢትዮጵያ ዝግጁ ናት፤ምንም ችግር የለብንም።
በእርግጠኝነት የምናገረው ህዳሴ ለግብፅም ለሱዳንም ጉዳት አያመጣም።
በዚሁ አጋጣሚ በኢትዮጵያ ውስጥ ትልቁ የስልጣን ባለቤት ይህ የተከበረው ምክር ቤት ስለሆነ ለግብፅ መንግሥት ፣ ለሱዳን መንግሥት እንዲሁም ለተፋሰሱ ሀገራት መንግሥታት በሙሉ መስከረም ዝናብ ጋብ ሲል ህዳሴን ስናስመርቅ የደስታችን ተካፋይ እንዲሆኑ ግብዣ አቀርብላቸዋለሁ።
የጋራ ሃብታችን ነው ፤ በጋራ እናስመርቀዋለን በጋራ እናየዋለን፣ የሚታዩ ጉዳዮች ካሉ በጋራ እናያለን።
ከድርቅ ጋር ተያይዞ ግብፅ የሚነሳው ነገር ' ድርቅ በሚሆንበት ሰዓት ግብፅ ትጎዳለች ' ነው ፤ ድርቅ የሚባለው ኢትዮጵያ ነው ኢትዮጵያ ከደረቀች ውሃዋ የለም ማለት ነው እዛ አይደለም ድርቅ የሚባለው፤ ኢትዮጵያ ደግሞ እንዳትደርቅ Green Legacy (አረንጓዴ አሻራ) እየሰራን ነው እኛ አንደርቅም ማለት ነው እኛ ዝናብ ካገኘን እኛም ግብፅም ሱዳንም ሌሎቹም ይጠቀማሉ። በቅንነት አይተን በጋራ ለልማት እንድንሰራ አደራ እላለሁ። "
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#GERD
" መስከረም ላይ ዝናብ ጋብ ሲል ህዳሴን እናስመርቃለን !!! "
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በሚመለከት ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምን አሉ ?
" ህዳሴ አልቋል። ህዳሴን እናስመርቃለን። ህዳሴ ከመመረቁ በፊት ' ብንረብሽ ' ብለው የሚያስቡ ሰዎች አሉ ፤ እናስመርቃለን።
ህዳሴን እንዳይመረቅ ለማድረግ የሚያስችል ነገር አሁን የለም። የሚመረቀውም አሁን ነው ነገ ክረምቱ ሲያልቅ።
ለታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ያለኝ መልዕክት ህዳሴ ለሱዳን ህዳሴ ለግብፅ በረከት ነው። በፍጹም ጉዳት አያመጣባቸውም። ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ልማት ልማታቸው ነው ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ኢነርጂ ለሁሉም ጎረቤቶች የሚዳረስ ነው።
የኛ ግድብ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራትን የሚጎዳ ቢሆን ኖሮ ቱርካና አጀንዳ አይሆንም ነበር። ታስታውሳላችሁ ግቤ 3 ሲሰራ 'ቱርካና ይደርቃል የሚል ከፍተኛ ችግር ነበር። እንኳን ሊደርው ከግድቡ በኋላ ይኸው ሞልቶ እያስቸገረ ነው ያለው።
አሁንም ግብፅ ብትሄዱ የግብፅ አስዋን ግድብ አንድ ሊትር ውሃ አልቀነሰም። ወደፊትም ኢትዮጵያ እስከበለጸገች ድረስ እስካለች ድረስ የግብፅ ወንድሞቻችንን ጉዳት እኛ አናይም ተባብረን ከወንድሞቻች ጋር ማደግ እንፈልጋለን።
ግብፅ እንድትጎዳ ፣ ሱዳን እንድትጎዳ አንፈልግም። ኢነርጂውን በጋራ እንጠቀማለን ውሃውን በጋራ እንጠቀማለን ልማት በጋራ ይመጣል። ንግግር ካስፈለገ እንነጋገራለን ችግር የለም።
እኛ ለረጅም ጊዜ ስናነሳ የነበረው ' አትስሩ ' አትበሉን ነው ያልነው እንጂ በኛ ገንዘብ በኛ ምድር የሚሰራውም ስራ አታግዱ ነው ያልነው እንጂ ያን እስካልከለከሉ ድረስ አሁንም ከግብፆች ጋር ለመነጋገር፣ ለመደራደር ፣ ለመስራት ኢትዮጵያ ዝግጁ ናት፤ምንም ችግር የለብንም።
በእርግጠኝነት የምናገረው ህዳሴ ለግብፅም ለሱዳንም ጉዳት አያመጣም።
በዚሁ አጋጣሚ በኢትዮጵያ ውስጥ ትልቁ የስልጣን ባለቤት ይህ የተከበረው ምክር ቤት ስለሆነ ለግብፅ መንግሥት ፣ ለሱዳን መንግሥት እንዲሁም ለተፋሰሱ ሀገራት መንግሥታት በሙሉ መስከረም ዝናብ ጋብ ሲል ህዳሴን ስናስመርቅ የደስታችን ተካፋይ እንዲሆኑ ግብዣ አቀርብላቸዋለሁ።
የጋራ ሃብታችን ነው ፤ በጋራ እናስመርቀዋለን በጋራ እናየዋለን፣ የሚታዩ ጉዳዮች ካሉ በጋራ እናያለን።
ከድርቅ ጋር ተያይዞ ግብፅ የሚነሳው ነገር ' ድርቅ በሚሆንበት ሰዓት ግብፅ ትጎዳለች ' ነው ፤ ድርቅ የሚባለው ኢትዮጵያ ነው ኢትዮጵያ ከደረቀች ውሃዋ የለም ማለት ነው እዛ አይደለም ድርቅ የሚባለው፤ ኢትዮጵያ ደግሞ እንዳትደርቅ Green Legacy (አረንጓዴ አሻራ) እየሰራን ነው እኛ አንደርቅም ማለት ነው እኛ ዝናብ ካገኘን እኛም ግብፅም ሱዳንም ሌሎቹም ይጠቀማሉ። በቅንነት አይተን በጋራ ለልማት እንድንሰራ አደራ እላለሁ። "
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤2.38K😡338👏127🙏55🤔36🕊27😱17😭14🥰13😢9💔3
TIKVAH-ETHIOPIA
" በፔይሮል የሚያገኘውን ብቻ በማሳደድ ሀገር ማሳደግ አይቻልም ! " የገንዘብ ሚኒስቴር ከሠራተኛ የሚቀነስ ግብርን ጨምሮ ሌሎች የገቢ ጉዳዮችን የሚመለከተውን የገቢ ግብር አዋጅ ለማሻሻል ባስደረገው ጥናት በየወሩ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ከግብር ነፃ የሚሆነው የትኛው የደሞዝ መጠን ላይ ነው ለሚለው ሦስት አማራጮችን አቅርቧል። እነዚህም 1,200፣ 1,600፣ ወይስ 2,000 ብር ከሚከፈላቸው ላይ ይሁን…
#Ethiopia🇪🇹
የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ እንደሚሻሻል ተገልጿል።
ዛሬ 48ኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ተካሂዶ የአዋጁ መሻሻል ላይ ውሳኔ አሳልፏል።
ምክር ቤቱ " ቀደም ሲል ሲሰራበት የነበረው የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ አሁን ከምንገኝበት ሀገራዊ እና አለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ አንጻር ሲታይ በርካታ ክፍተቶች ያሉበት ነው " ብሏል።
" የአዋጁን ድንጋጌዎች በማሻሻል የታክስ ስርአቱ መሠረታዊ የታክስ መርሆዎችን ለማሳካት በሚያስችል መልኩ እንዲቀረጽ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ የማሻሻያ አዋጁ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል " ሲል ገልጿል።
ምክር ቤቱ በማሻሻያ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ በሙሉ ድምጽ አጽድቆ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ መወሰኑን አሳውቋል።
ከሳምንታት በፊት የገንዘብ ሚኒስቴር ከሠራተኛ የሚቀነስ ግብርን ጨምሮ ሌሎች የገቢ ጉዳዮችን የሚመለከተውን የገቢ ግብር አዋጅ ለማሻሻል ባስደረገው ጥናት በየወሩ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ከግብር ነፃ የሚሆነው የትኛው የደሞዝ መጠን ላይ ነው ለሚለው ሦስት አማራጮችን አቅርቦ እንደነበር ፤ እነዚህም 1,200፣ 1,600፣ ወይስ 2,000 ብር ከሚከፈላቸው ላይ ይሁን የሚል እንደነበር መዘገቡ ይታወሳል።
የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማሕበራት ኮንፌደሬሽን በበኩሉ ዝቅተኛው ከግብር ነፃ መሆን ያለበት የደሞዝ መጠን 8,300 ብር ነው መሆን ያለበት በሚል ሲከራከር እንደነበር አይዘነጋም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ እንደሚሻሻል ተገልጿል።
ዛሬ 48ኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ተካሂዶ የአዋጁ መሻሻል ላይ ውሳኔ አሳልፏል።
ምክር ቤቱ " ቀደም ሲል ሲሰራበት የነበረው የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ አሁን ከምንገኝበት ሀገራዊ እና አለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ አንጻር ሲታይ በርካታ ክፍተቶች ያሉበት ነው " ብሏል።
" የአዋጁን ድንጋጌዎች በማሻሻል የታክስ ስርአቱ መሠረታዊ የታክስ መርሆዎችን ለማሳካት በሚያስችል መልኩ እንዲቀረጽ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ የማሻሻያ አዋጁ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል " ሲል ገልጿል።
ምክር ቤቱ በማሻሻያ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ በሙሉ ድምጽ አጽድቆ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ መወሰኑን አሳውቋል።
ከሳምንታት በፊት የገንዘብ ሚኒስቴር ከሠራተኛ የሚቀነስ ግብርን ጨምሮ ሌሎች የገቢ ጉዳዮችን የሚመለከተውን የገቢ ግብር አዋጅ ለማሻሻል ባስደረገው ጥናት በየወሩ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ከግብር ነፃ የሚሆነው የትኛው የደሞዝ መጠን ላይ ነው ለሚለው ሦስት አማራጮችን አቅርቦ እንደነበር ፤ እነዚህም 1,200፣ 1,600፣ ወይስ 2,000 ብር ከሚከፈላቸው ላይ ይሁን የሚል እንደነበር መዘገቡ ይታወሳል።
የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማሕበራት ኮንፌደሬሽን በበኩሉ ዝቅተኛው ከግብር ነፃ መሆን ያለበት የደሞዝ መጠን 8,300 ብር ነው መሆን ያለበት በሚል ሲከራከር እንደነበር አይዘነጋም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤578😭87😡55🙏24😢9🥰6🤔3🕊1
#Ethiopia🇪🇹
የ1 ቢሊየን ዶላር የፋይናንስ ስምምነት በኢትዮጵያ እና ዓለም ባንክ መካከል ተፈርሟል።
የገንዘብ ሚኒስቴር ይህ የድጋፍ ስምምነት የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አካታች የኢኮኖሚ እድገትን ለማገዝ ይውላል ብሏል።
ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ እና የዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ማሪያም ሳሊም ነው የተፈራረሙት።
Via Ministry of Finance
@tikvahethiopia
የ1 ቢሊየን ዶላር የፋይናንስ ስምምነት በኢትዮጵያ እና ዓለም ባንክ መካከል ተፈርሟል።
የገንዘብ ሚኒስቴር ይህ የድጋፍ ስምምነት የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አካታች የኢኮኖሚ እድገትን ለማገዝ ይውላል ብሏል።
ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ እና የዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ማሪያም ሳሊም ነው የተፈራረሙት።
Via Ministry of Finance
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
😡684❤336😭74😱26👏24🤔23🕊16🙏5
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia🇪🇹 የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ እንደሚሻሻል ተገልጿል። ዛሬ 48ኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ተካሂዶ የአዋጁ መሻሻል ላይ ውሳኔ አሳልፏል። ምክር ቤቱ " ቀደም ሲል ሲሰራበት የነበረው የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ አሁን ከምንገኝበት ሀገራዊ እና አለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ አንጻር ሲታይ በርካታ ክፍተቶች ያሉበት ነው " ብሏል። " የአዋጁን ድንጋጌዎች በማሻሻል የታክስ ስርአቱ…
#Ethiopia🇪🇹
" አሁን የ2,000 ብር ደሞዝ የለም በሌለ ነገር ከዚያ በታች ያለው ነጻ ነው ብንል ታክስ መቀነስ አይደለም ! " - የምክር ቤት አባል
በገቢ ግብር ማሻሽያ አዋጅ ላይ ዝቅተኛ የግብር ከፋይ መነሻ ደመወዝ 5,000 ብር እንዲሆን በምክር ቤት ተጠየቀ፡፡
ይህ ጥያቄ የተጠየቀው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ዛሬ ከሰዓት በጠራው ልዩ መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው፡፡
አሁን በስራ ላይ ያለው የገቢ ግብር አዋጅ ከዘመኑ የኢኮኖሚ ሁኔታ አብሮ እንደማይሄድ እና ከዲጂታል ኢኮኖሚ ጋር እንደማይጣጣም በአዋጁ ላይ በቀረበው አጭር ማብራርያ ተመላክቷል፡፡
የማሻሽያ አዋጁን በተመለከተ ሃሳብ የሰጡት የምክርቤት አባሉ አቶ ባርጠማ ፍቃዱ ምን አሉ ?
- በአዋጁ አንቅጽ 11 ላይ የቀድሞው ተሰርዞ አዲስ ሃሳብ ገብቷል። ከዚህ በፊት ተቀጣሪ ከደሞዘ የሚከፍለው ግብር ከ600 ብር በላይ ጀምሮ ነው። ተሻሽሎ በቀረበው አዋጅ ግን ከ600 ብር ወደ 2,000 ብር አድጓል።
- በመሰረቱ 2 ሺ ብር አሁን በአገራችን የሚቀጠር ሰው የለም።
- ከዚህ ቀደም በመንግስት ተቋም ጽዳት ፣የጉልበት ስራ እና የመሳሰሉ ስራዎች ነበሩ ከ600 ብር እስከ 1,000 ብር ደሞዝ አሁን ባለው ሁኔታ ከ4,500 ብር በላይ ነው ቅጥር ያለው።
- አሁን የ2,000 ብር ደሞዝ የለም በሌለ ነገር ከዚያ በታች ያለው ነጻ ነው ብንል ታክስ መቀነስ አይደለም።
- ቢያንስ እንኳን ዝቅተኛ ተቀጣሪው ከግብር ነጻ ቢሆን ጥሩ ነው።
- ግብር ከፋይዉም ከ5,000 በላይ ያለው ስራተኛ ቢሆን።
- የ35 በመቶ ግብር እንዲከፍል የተቀመጠው ከ14ሺ 100 በላይ ነው። ይህም ከወቅቱ ገበያ አንጻር ሲታይ ምንም ነው፤ በዚህ ላይ 35 በመቶ ግብር ሲቆረጥበት ደግሞ በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ ወደ 20 ሺ በላይ ከፍ ቢል።
- በስራ ላይ ባለው አዋጅ #መነሻ_ግብር 10 በመቶ ነው። ተሻሽሎ በቀረበው ረቂቅ አዋጁ ግን 15 በመቶ ብሎ ነው የሚጀምረው ይህም ወደ ቀድሞው ወደ 10 በመቶ ቢመለስ ሲሉ ጥሩ ነው።
የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን በስራ ላይ ባለው አዋጅ ላይ ያለው ከፍተኛ ግብር የሚከፈልበት ደሞዝ በተሸሻለው አዋጅ የዝቅተኛ ግብር መነሻ እንዲሆን መጠየቁ ይታወሳል።
ኮንፌደሬሽኑ የሰራተኛውን ኑሮ ያገናዘበ የገቢ ግብር ማሻሽያ እንዲደረግም ጠይቆ ነበር፡፡
ዝቅተኛ ገቢ ያለው የህበረተሰብ ክፍል ፦
- የሚያርፍበትን የግብር ጫና መቀነስ፤
- የግብር መሰረትን ማስፋት፤
- የግብር ስርአቱ ላይ የሚታዩ የፍትሃዊነት ችግሮችን መቅረፍ፤
- የአነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች የግብር አከፋፈል ስርአት ቀላል እንዲሆን ማድረግ፤
- ከአዋጁ አላማዎች ውስጥ ጥቂቶቹ ናቸው ተብሏል፡፡
ም/ቤቱ እነዚህን እና ሌሎች ከአባላት የተነሱ ሃሳቦች ታክለውበት ረቂቅ አዋጁ ለፕላን በጀት እና ፋይናንስ ጉዳይዎች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምጽ መርቶታል፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
#ShegerFM
@tikvahethiopia
" አሁን የ2,000 ብር ደሞዝ የለም በሌለ ነገር ከዚያ በታች ያለው ነጻ ነው ብንል ታክስ መቀነስ አይደለም ! " - የምክር ቤት አባል
በገቢ ግብር ማሻሽያ አዋጅ ላይ ዝቅተኛ የግብር ከፋይ መነሻ ደመወዝ 5,000 ብር እንዲሆን በምክር ቤት ተጠየቀ፡፡
ይህ ጥያቄ የተጠየቀው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ዛሬ ከሰዓት በጠራው ልዩ መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው፡፡
አሁን በስራ ላይ ያለው የገቢ ግብር አዋጅ ከዘመኑ የኢኮኖሚ ሁኔታ አብሮ እንደማይሄድ እና ከዲጂታል ኢኮኖሚ ጋር እንደማይጣጣም በአዋጁ ላይ በቀረበው አጭር ማብራርያ ተመላክቷል፡፡
የማሻሽያ አዋጁን በተመለከተ ሃሳብ የሰጡት የምክርቤት አባሉ አቶ ባርጠማ ፍቃዱ ምን አሉ ?
- በአዋጁ አንቅጽ 11 ላይ የቀድሞው ተሰርዞ አዲስ ሃሳብ ገብቷል። ከዚህ በፊት ተቀጣሪ ከደሞዘ የሚከፍለው ግብር ከ600 ብር በላይ ጀምሮ ነው። ተሻሽሎ በቀረበው አዋጅ ግን ከ600 ብር ወደ 2,000 ብር አድጓል።
- በመሰረቱ 2 ሺ ብር አሁን በአገራችን የሚቀጠር ሰው የለም።
- ከዚህ ቀደም በመንግስት ተቋም ጽዳት ፣የጉልበት ስራ እና የመሳሰሉ ስራዎች ነበሩ ከ600 ብር እስከ 1,000 ብር ደሞዝ አሁን ባለው ሁኔታ ከ4,500 ብር በላይ ነው ቅጥር ያለው።
- አሁን የ2,000 ብር ደሞዝ የለም በሌለ ነገር ከዚያ በታች ያለው ነጻ ነው ብንል ታክስ መቀነስ አይደለም።
- ቢያንስ እንኳን ዝቅተኛ ተቀጣሪው ከግብር ነጻ ቢሆን ጥሩ ነው።
- ግብር ከፋይዉም ከ5,000 በላይ ያለው ስራተኛ ቢሆን።
- የ35 በመቶ ግብር እንዲከፍል የተቀመጠው ከ14ሺ 100 በላይ ነው። ይህም ከወቅቱ ገበያ አንጻር ሲታይ ምንም ነው፤ በዚህ ላይ 35 በመቶ ግብር ሲቆረጥበት ደግሞ በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ ወደ 20 ሺ በላይ ከፍ ቢል።
- በስራ ላይ ባለው አዋጅ #መነሻ_ግብር 10 በመቶ ነው። ተሻሽሎ በቀረበው ረቂቅ አዋጁ ግን 15 በመቶ ብሎ ነው የሚጀምረው ይህም ወደ ቀድሞው ወደ 10 በመቶ ቢመለስ ሲሉ ጥሩ ነው።
የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን በስራ ላይ ባለው አዋጅ ላይ ያለው ከፍተኛ ግብር የሚከፈልበት ደሞዝ በተሸሻለው አዋጅ የዝቅተኛ ግብር መነሻ እንዲሆን መጠየቁ ይታወሳል።
ኮንፌደሬሽኑ የሰራተኛውን ኑሮ ያገናዘበ የገቢ ግብር ማሻሽያ እንዲደረግም ጠይቆ ነበር፡፡
ዝቅተኛ ገቢ ያለው የህበረተሰብ ክፍል ፦
- የሚያርፍበትን የግብር ጫና መቀነስ፤
- የግብር መሰረትን ማስፋት፤
- የግብር ስርአቱ ላይ የሚታዩ የፍትሃዊነት ችግሮችን መቅረፍ፤
- የአነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች የግብር አከፋፈል ስርአት ቀላል እንዲሆን ማድረግ፤
- ከአዋጁ አላማዎች ውስጥ ጥቂቶቹ ናቸው ተብሏል፡፡
ም/ቤቱ እነዚህን እና ሌሎች ከአባላት የተነሱ ሃሳቦች ታክለውበት ረቂቅ አዋጁ ለፕላን በጀት እና ፋይናንስ ጉዳይዎች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምጽ መርቶታል፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
#ShegerFM
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤1.84K👏244🙏64😡60😢43🕊23😭22🤔20😱19🥰7
#Ethiopia🇪🇹
በግለሰቦች፣ በብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች መካከል " ስጋት፣ ግጭትን፣ ጥርጣሬን እና አለመተማመንን የሚፈጥር ድርጊት ፈጽሟል " ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከምዝገባ እንዲሰርዝ ስልጣን የሚሰጥ የአዋጅ ማሻሻያ ለፓርላማ ቀረበ።
ቦርዱ የሌላ ፖለቲካ ፓርቲን " ህጋዊ እና ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ያደናቀፈ " የፖለቲካ ፓርቲ ላይ ተመሳሳይ እርምጃ የመውሰድ ስልጣንም በአዋጅ ማሻሻያው ተሰጥቶታል።
ላለፉት አምስት ዓመታት በስራ ላይ የቆየውን " የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ስነምግባር አዋጅ " ያሻሻለው የህግ ረቂቅ ለፓርላማ ቀርቧል።
ዛሬ በአዋጅ ማሻሻያው ላይ የፓርላማ አባላት መታየት ያለባቸውን ጉዳዮች በጥቂቱ ካቀረቡ በኋላ በዝርዝር እንዲታይ ለምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርተውታል።
ያለምንም ተቃውሞ እና ድምጸ ተዐቅቦ ለቋሚ ኮሚቴ የተመራው ይህ የአዋጅ ማሻሻያ ከተዘጋጀባቸው ምክንያቶች አንዱ፤ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስፈጸመው ጠቅላላ ምርጫ ወቅት የተስተዋሉ " የህግ ክፍተቶች " እንደሆነ የህግ ረቂቁን ለማብራራት በቀረበ ሰነድ ላይ ተጠቅሷል።
በዝርዝር ያንብቡ : https://ethiopiainsider.com/2025/16239/
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገጽ ነው።
@tikvahethiopia
በግለሰቦች፣ በብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች መካከል " ስጋት፣ ግጭትን፣ ጥርጣሬን እና አለመተማመንን የሚፈጥር ድርጊት ፈጽሟል " ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከምዝገባ እንዲሰርዝ ስልጣን የሚሰጥ የአዋጅ ማሻሻያ ለፓርላማ ቀረበ።
ቦርዱ የሌላ ፖለቲካ ፓርቲን " ህጋዊ እና ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ያደናቀፈ " የፖለቲካ ፓርቲ ላይ ተመሳሳይ እርምጃ የመውሰድ ስልጣንም በአዋጅ ማሻሻያው ተሰጥቶታል።
ላለፉት አምስት ዓመታት በስራ ላይ የቆየውን " የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ስነምግባር አዋጅ " ያሻሻለው የህግ ረቂቅ ለፓርላማ ቀርቧል።
ዛሬ በአዋጅ ማሻሻያው ላይ የፓርላማ አባላት መታየት ያለባቸውን ጉዳዮች በጥቂቱ ካቀረቡ በኋላ በዝርዝር እንዲታይ ለምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርተውታል።
ያለምንም ተቃውሞ እና ድምጸ ተዐቅቦ ለቋሚ ኮሚቴ የተመራው ይህ የአዋጅ ማሻሻያ ከተዘጋጀባቸው ምክንያቶች አንዱ፤ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስፈጸመው ጠቅላላ ምርጫ ወቅት የተስተዋሉ " የህግ ክፍተቶች " እንደሆነ የህግ ረቂቁን ለማብራራት በቀረበ ሰነድ ላይ ተጠቅሷል።
በዝርዝር ያንብቡ : https://ethiopiainsider.com/2025/16239/
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገጽ ነው።
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤644😡157🤔32🙏27🕊15😭11🥰5😱2😢2
#Ethiopia🇪🇹
የሰነደ መዋዕለ ንዋዮች ገበያ በሚቀጥለው ሳምንት ይፋዊ ግብይት ሊጀምር እንደሆነ ካፒታል ጋዜጣ አስነብቧል።
ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረው የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋዮች ( ስቶክ ገበያ) በሚቀጥለው ሳምንት ሥራ ሊጀምር መሆኑ ተሰምቷል።
ይህ እርምጃ ለአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ ተነግሯል።
ገበያዉ በኖቬምበር 2023 በተደረገ የካፒታል ማሰባሰቢያ ዘመቻ 1.5 ቢሊዮን ብር በማሰባሰብ ከታሰበው ግብ በ631% በልጧል። ይህ ገንዘብ ከ48 የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ተቋማት የተገኘ ነው።
በሕዝብና በግል ሽርክና የሚሰራው አዲሱ የበይነመረብ ንግድ ልዉዉጥ መድረክን መንግሥት 25%፣ የግል ዘርፍ ደግሞ 75% ድርሻ አላቸዉ።
አሁን ላይ ገዳ ባንክ አ.ማ. እና ወጋገን ካፒታል ኢንቨስትመንት ባንክ አ.ማ. በገበያው ላይ ከተመዘገቡት ኩባንያዎች መካከል ይጠቀሳሉ።
የሰነደ መዋዕለ ንዋይ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ውስጥ እስከ 50 ኩባንያዎችን፣ በአሥር ዓመታት ውስጥ ደግሞ ከ90 በላይ ንግዶችን ለማካተት አቅዷል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የካፒታል ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
የሰነደ መዋዕለ ንዋዮች ገበያ በሚቀጥለው ሳምንት ይፋዊ ግብይት ሊጀምር እንደሆነ ካፒታል ጋዜጣ አስነብቧል።
ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረው የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋዮች ( ስቶክ ገበያ) በሚቀጥለው ሳምንት ሥራ ሊጀምር መሆኑ ተሰምቷል።
ይህ እርምጃ ለአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ ተነግሯል።
ገበያዉ በኖቬምበር 2023 በተደረገ የካፒታል ማሰባሰቢያ ዘመቻ 1.5 ቢሊዮን ብር በማሰባሰብ ከታሰበው ግብ በ631% በልጧል። ይህ ገንዘብ ከ48 የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ተቋማት የተገኘ ነው።
በሕዝብና በግል ሽርክና የሚሰራው አዲሱ የበይነመረብ ንግድ ልዉዉጥ መድረክን መንግሥት 25%፣ የግል ዘርፍ ደግሞ 75% ድርሻ አላቸዉ።
አሁን ላይ ገዳ ባንክ አ.ማ. እና ወጋገን ካፒታል ኢንቨስትመንት ባንክ አ.ማ. በገበያው ላይ ከተመዘገቡት ኩባንያዎች መካከል ይጠቀሳሉ።
የሰነደ መዋዕለ ንዋይ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ውስጥ እስከ 50 ኩባንያዎችን፣ በአሥር ዓመታት ውስጥ ደግሞ ከ90 በላይ ንግዶችን ለማካተት አቅዷል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የካፒታል ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤614👏58🤔19🕊19🥰16💔14😭8😱7😢6
TIKVAH-ETHIOPIA
ኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ምን ውሳኔ አሳለፈ ? የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ዛሬ ውይይት አካሂዶ የተለያዩ ውሳኔዎች አሳልፏል። 1. በሁሉም ንግድ ባንኮች ላይ የተጣለው አስገዳጅ የቦንድ ግዥ እንዲነሳ ወስኗል። ሁሉም ንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ (Treasury Bond) እንዲገዙ የሚያስገድደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ (MFAD/TRBO/001/2022)…
#Ethiopia🇪🇹
አስገዳጅ የቦንድ ግዢ መመሪያው መነሳቱ ለባንኮች ምን ትርጉም አለው ?
ሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ባካሔደው ሶስተኛ ስብሰባ፣ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ ከውሳኔዎቹ አንዱም የንግድ ባንኮች ሲገዙት ከነበረው የግምጃ ቤት ቦንድ ጋር የሚያያዝ ነው፡፡
ኮሚቴው፣ የንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ እንዲገዙ የሚያስገድደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ እንዲነሳ መወሰኑን አስታውቋል፡፡
ይህም የሆነው በአሁኑ ወቅት የመንግስት ገቢ የማሰባሰብ አቅም በእጅጉ በመሻሻሉና መንግስት የበጀት ጉድለቱን ለማሟላት የውጭና ገበያ መር ከሆኑ የሀገር ውስጥ የመበደሪያ አማራጮችን እየተጠቀመ በመሆኑ ነው ብሏል፡፡
የንግድ ባንኮች ቦንድ እንዲገዙ ሲደርግ የነበረው አስገዳጅ መመሪያ በመነሳቱ፣ ለባንኮቹ ምን ፋይዳ አለው ? በማለት ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቃቸው አንድ ከፍተኛ የባንክ ባለሙያ፣ " አሰራሩ በባንኮች ዘንድ የገንዘብ እጥረት እንዲፈጠር አስተዋፅኦ ስለነበረው፣ ይህ ውሳኔ በጣም ጠቃሚ ነው " ሲሉ ገልፀዋል፡፡
የባንክ ባለሙያው በዝርዝር ምን አሉ ?
" ቦንዱ እንኳን ተነሳ፡፡ በቦንዱ ምክንያት ለአምስት አመት ታስሮ የሚቀመጥ ገንዘብ ነበር፡፡ ባንኮቹ ቦንድ የገዙበት ገንዘብ ከአምስት አመት በኋላ ነው የሚመለስላቸው፡፡
ይህ አስገዳጅ የቦንድ ግዢ መመሪያ፣ በባንኮች የገንዘብ እጥረት/የሊኩዲቲ ችግር እንዲመጣ አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡ ለሊኩዲቲ ችግር መከሰት አንዱ መንስኤ የነበረው እሱ ነው፡፡
የሆነ ብድር በሰጠህ ቁጥር የተወሰነ ፐርሰንት ቦንድ እድትገዛ ትገደድ ነበር፡፡ ብድር በሰጠህ ቁጥር የብድሩን 20 በመቶ ቦንድ ግዛ ትባላለህ፡፡ እስከ 20 በመቶ እንድተገዛ ትገደድ ነበር፡፡ ለአንድ ሰው አምስት ጊዜ ካበደርክ ያስቀመጥከውን ገንዘብ በሙሉ ወሰደው ማለት ነው የቦንድ ግዢው፡፡ በዚህ መልኩ ባንኮች ብድር በሰጡ ቁጥር ተደራራቢ የቦንድ ግዢ ስለሚፈፅሙ እና ገንዘቡም የሚመለሰው ከአምስት አመት በኋላ ስለነበረ ለገንዘብ እጥረት አጋልጧቸዋል።
አሁን ይኼ በመቆሙ ትልቅ እፎይታ ነው የሚሰጣቸው፡፡ ለችግራቸው መፍትሔ ይሆናል፡፡ ለገንዘብ እጥረቱ ማስተንፈሻ ነው፡፡ ብሔራዊ ባንክ የወሰደው እርምጃ በእጅጉ አጋዥ ነው፣ የሚያስመሰግነው ነው፡፡
በቦንድ ግዢ ከባንኮች ሲሔድ የነበረው የገንዘብ መጠን፣ ባንኮቹ በሚሰጡት የብድር መጠን ላይ የሚመሰረት ነበር፡፡ አሁን ይሔ አሰገዳጅ የቦንድ ግዢ መመሪያ በመቅረቱ፣ የባንኮቹን የገንዘብ እጥረት በምን ያህል መጠን ሊያቃልለው እንደሚችል ማወቅ ይከብዳል፣ ግን በእጅጉ ያቃልላል፡፡
ይሔ ጥሩ እርምጃ ሆኖ፣ የንግድ ባንኮች የሚሰጡት ዓመታዊ የብድር ዕድገት ጣሪያ ደግሞ አልተነሳም፡፡ ከ18 በመቶ እንዳይበልጥ የተቀመጠው የብድር ጣሪያ እስከ መስከረም ወር እንዲቀጥል ተወስኗል፡፡
ብሔራዊ ባንክ በዚሁ እርምጃው ይህንንም 18 በመቶ የሚለውን የብድር ጣሪያ ቶሎ ቢያነሳው ጥሩ ነበር፡፡
የብድር ጣሪያው በባንኮች አሰራር ላይ ችግር እየፈጠረ ነው ያለው፡፡ ለምን ብትል ተበዳሪዎች ብድራቸውን ከመለሱ በኋላ በባንኮች ላይ በተጣለው የብድር ጣሪያ ምክንያት መልሰው እንደማይበደሩ ስለሚያውቁ የመጀመሪያውንም ብድራቸውን አይከፍሉም፡፡ ለባንክ የሚከፍሉትን እዳ ለሌላ አገልግሎት ያውሉታል፡፡
ይልቁንም ለባንክ መክፈል የነበረባቸውን ገንዘብ ለሌላ ንግድ እያገላበጡ ይጠቀሙበታል፡፡ ለዚህ ነው እዳ ውስጥ የሚገቡት፡፡ ባንኮቹ በተቀመጠው የ 18 በመቶ የብድር ጣሪያ ምክንያት ተጨማሪ ብድር መስጠት አይችሉም ብቻ ሳይሆን ቀድመው ያበደሩትን ገንዘብ ማስመለስ አልቻሉም፡፡
ብሔራዊ ባንክ ይህንን የብድር ጣሪያ የሚያነሳበትን ጊዜ በጉጉት ነው የምንጠብቀው፡፡ እርምጃው ለኢንቨስትመንትና ለስራ ፈጠራም አስተዋፅኦ ያደርጋል፡፡ የግሉ ዘርፍ ከባንኮች እየተበደረ ኢንቨስት ካላደረገ ኢኮኖሚው አይንቀሳቀስም፣ የስራ እድል ሊፈጠር አይችልም፣ ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖው ብዙ ነው፡፡ " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
አስገዳጅ የቦንድ ግዢ መመሪያው መነሳቱ ለባንኮች ምን ትርጉም አለው ?
ሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ባካሔደው ሶስተኛ ስብሰባ፣ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ ከውሳኔዎቹ አንዱም የንግድ ባንኮች ሲገዙት ከነበረው የግምጃ ቤት ቦንድ ጋር የሚያያዝ ነው፡፡
ኮሚቴው፣ የንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ እንዲገዙ የሚያስገድደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ እንዲነሳ መወሰኑን አስታውቋል፡፡
ይህም የሆነው በአሁኑ ወቅት የመንግስት ገቢ የማሰባሰብ አቅም በእጅጉ በመሻሻሉና መንግስት የበጀት ጉድለቱን ለማሟላት የውጭና ገበያ መር ከሆኑ የሀገር ውስጥ የመበደሪያ አማራጮችን እየተጠቀመ በመሆኑ ነው ብሏል፡፡
የንግድ ባንኮች ቦንድ እንዲገዙ ሲደርግ የነበረው አስገዳጅ መመሪያ በመነሳቱ፣ ለባንኮቹ ምን ፋይዳ አለው ? በማለት ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቃቸው አንድ ከፍተኛ የባንክ ባለሙያ፣ " አሰራሩ በባንኮች ዘንድ የገንዘብ እጥረት እንዲፈጠር አስተዋፅኦ ስለነበረው፣ ይህ ውሳኔ በጣም ጠቃሚ ነው " ሲሉ ገልፀዋል፡፡
የባንክ ባለሙያው በዝርዝር ምን አሉ ?
" ቦንዱ እንኳን ተነሳ፡፡ በቦንዱ ምክንያት ለአምስት አመት ታስሮ የሚቀመጥ ገንዘብ ነበር፡፡ ባንኮቹ ቦንድ የገዙበት ገንዘብ ከአምስት አመት በኋላ ነው የሚመለስላቸው፡፡
ይህ አስገዳጅ የቦንድ ግዢ መመሪያ፣ በባንኮች የገንዘብ እጥረት/የሊኩዲቲ ችግር እንዲመጣ አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡ ለሊኩዲቲ ችግር መከሰት አንዱ መንስኤ የነበረው እሱ ነው፡፡
የሆነ ብድር በሰጠህ ቁጥር የተወሰነ ፐርሰንት ቦንድ እድትገዛ ትገደድ ነበር፡፡ ብድር በሰጠህ ቁጥር የብድሩን 20 በመቶ ቦንድ ግዛ ትባላለህ፡፡ እስከ 20 በመቶ እንድተገዛ ትገደድ ነበር፡፡ ለአንድ ሰው አምስት ጊዜ ካበደርክ ያስቀመጥከውን ገንዘብ በሙሉ ወሰደው ማለት ነው የቦንድ ግዢው፡፡ በዚህ መልኩ ባንኮች ብድር በሰጡ ቁጥር ተደራራቢ የቦንድ ግዢ ስለሚፈፅሙ እና ገንዘቡም የሚመለሰው ከአምስት አመት በኋላ ስለነበረ ለገንዘብ እጥረት አጋልጧቸዋል።
አሁን ይኼ በመቆሙ ትልቅ እፎይታ ነው የሚሰጣቸው፡፡ ለችግራቸው መፍትሔ ይሆናል፡፡ ለገንዘብ እጥረቱ ማስተንፈሻ ነው፡፡ ብሔራዊ ባንክ የወሰደው እርምጃ በእጅጉ አጋዥ ነው፣ የሚያስመሰግነው ነው፡፡
በቦንድ ግዢ ከባንኮች ሲሔድ የነበረው የገንዘብ መጠን፣ ባንኮቹ በሚሰጡት የብድር መጠን ላይ የሚመሰረት ነበር፡፡ አሁን ይሔ አሰገዳጅ የቦንድ ግዢ መመሪያ በመቅረቱ፣ የባንኮቹን የገንዘብ እጥረት በምን ያህል መጠን ሊያቃልለው እንደሚችል ማወቅ ይከብዳል፣ ግን በእጅጉ ያቃልላል፡፡
ይሔ ጥሩ እርምጃ ሆኖ፣ የንግድ ባንኮች የሚሰጡት ዓመታዊ የብድር ዕድገት ጣሪያ ደግሞ አልተነሳም፡፡ ከ18 በመቶ እንዳይበልጥ የተቀመጠው የብድር ጣሪያ እስከ መስከረም ወር እንዲቀጥል ተወስኗል፡፡
ብሔራዊ ባንክ በዚሁ እርምጃው ይህንንም 18 በመቶ የሚለውን የብድር ጣሪያ ቶሎ ቢያነሳው ጥሩ ነበር፡፡
የብድር ጣሪያው በባንኮች አሰራር ላይ ችግር እየፈጠረ ነው ያለው፡፡ ለምን ብትል ተበዳሪዎች ብድራቸውን ከመለሱ በኋላ በባንኮች ላይ በተጣለው የብድር ጣሪያ ምክንያት መልሰው እንደማይበደሩ ስለሚያውቁ የመጀመሪያውንም ብድራቸውን አይከፍሉም፡፡ ለባንክ የሚከፍሉትን እዳ ለሌላ አገልግሎት ያውሉታል፡፡
ይልቁንም ለባንክ መክፈል የነበረባቸውን ገንዘብ ለሌላ ንግድ እያገላበጡ ይጠቀሙበታል፡፡ ለዚህ ነው እዳ ውስጥ የሚገቡት፡፡ ባንኮቹ በተቀመጠው የ 18 በመቶ የብድር ጣሪያ ምክንያት ተጨማሪ ብድር መስጠት አይችሉም ብቻ ሳይሆን ቀድመው ያበደሩትን ገንዘብ ማስመለስ አልቻሉም፡፡
ብሔራዊ ባንክ ይህንን የብድር ጣሪያ የሚያነሳበትን ጊዜ በጉጉት ነው የምንጠብቀው፡፡ እርምጃው ለኢንቨስትመንትና ለስራ ፈጠራም አስተዋፅኦ ያደርጋል፡፡ የግሉ ዘርፍ ከባንኮች እየተበደረ ኢንቨስት ካላደረገ ኢኮኖሚው አይንቀሳቀስም፣ የስራ እድል ሊፈጠር አይችልም፣ ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖው ብዙ ነው፡፡ " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤1.05K🙏67👏36🤔21😢17😭17😡15🕊13😱12🥰11
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tax ዩትዩብ ወይም ቲክቶክ የመሳሰሉ መተግበሪያዎችን በመጠቀም ገንዘብ የሚያገኙ ግለሰቦች እና ተቋማት ታክስ እንዲከፍሉ ሊደረግ ነው። በክፍያ የሚቀርቡ ወይም በሚያቀርቡት አገልግሎት ገንዘብ ከሚያገኙ የድረገጽ እና የመተግበሪያ ውጤቶች ላይ መንግሥት ታክስ ሊሰበስብ መዘጋጀቱን አሰራሩን ለመተግበር ከወጣው የመንግሥት ሰነድ መመልከቱን ዋዜማ ሬድዮ ዘግቧል። በድረገጽ የሚቀርቡ የሚዲያ አገልግሎቶች ፖድካስት፣…
#Ethiopia🇪🇹
ከዩቲዩብ ፣ ቲክቶክና ከሌሎች የዲጂታል ይዘት ፈጠራ የሚገኝ ገቢ ላይ 15 በመቶ ግብር ሊጣል ነው።
በኢትዮጵያ ለ9 ዓመታት ስራ ላይ የቆየውን የገቢ ግብር አዋጅ ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ፣ ከዲጂታል ይዘት ፈጠራ በሚገኝ ገቢ ላይ 15 በመቶ ግብር ለመጣል የሚያስችል ንዑስ አንቀጽ ተካቷል።
በታቀደው የአዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ መሰረት፣ ከማህበራዊ ሚዲያ የሚገኝ ገቢ ለምሳሌ ፦
- ከዩቲዩብ፣
- ፌስቡክ፣
- ኢንስታግራም፣
- ቲክቶክና ሌሎችም መድረኮች
- በኢንተርኔት ከሚሰራጩ መረጃዎች
- በኢንተርኔት ከሚፈፀሙ ግብይቶች፣
- ከስፖንሰርሺፕ ከመሳሰሉት የዲጂታል ይዘት ፈጠራ የሚገኝ ገቢ ላይ ግብር እንደሚጣልባቸው በዝርዝር ያስቀምጣል።
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዉይይት እየተደረገበት የሚገኘዉ ይህ ረቂቅ አዋጅ ፤ እነዚህ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች በመደበኛነት የሚከናወኑ ከሆነ፣ የሚገኘው ገቢ በንግድ ስራ ገቢ ስር የሚመደብ ሲሆን፣ የንግድ ስራ ገቢ ግብርም የሚከፈልበት መሆኑን ይገልጻል።
ሆኖም፣ በአዋጁ የተቀመጡትን መስፈርቶች የማያሟላ ከሆነ፣ ገቢው " ሌሎች ገቢዎች " በሚለው ስር ተመድቦ ከጠቅላላ ገቢው ላይ 15% (አስራ አምስት በመቶ) ግብር እንዲከፈልበት ይደረጋል ይላል።
ከዚህ በተጨማሪም፣ ለዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች ክፍያ የሚያመቻቹ መድረኮች ለእያንዳንዱ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪ የተከፈለውን ገንዘብ የሚያሳይ ሪፖርት ለታክስ ባለስልጣን የመላክ ግዴታ እንደሚኖርባቸው ያስቀምጣል።
ይህን ተከትሎም፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) የማውጣት ፣ ገቢያቸውን የማስታወቅ እና ሌሎች የታክስ ከፋይ ግዴታዎችን የመወጣት ሃላፊነት እንደሚጠበቅባቸው ያስገድዳል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የካፒታል ጋዜጣ ነው። #CAPITAL
@tikvahethiopia
ከዩቲዩብ ፣ ቲክቶክና ከሌሎች የዲጂታል ይዘት ፈጠራ የሚገኝ ገቢ ላይ 15 በመቶ ግብር ሊጣል ነው።
በኢትዮጵያ ለ9 ዓመታት ስራ ላይ የቆየውን የገቢ ግብር አዋጅ ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ፣ ከዲጂታል ይዘት ፈጠራ በሚገኝ ገቢ ላይ 15 በመቶ ግብር ለመጣል የሚያስችል ንዑስ አንቀጽ ተካቷል።
በታቀደው የአዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ መሰረት፣ ከማህበራዊ ሚዲያ የሚገኝ ገቢ ለምሳሌ ፦
- ከዩቲዩብ፣
- ፌስቡክ፣
- ኢንስታግራም፣
- ቲክቶክና ሌሎችም መድረኮች
- በኢንተርኔት ከሚሰራጩ መረጃዎች
- በኢንተርኔት ከሚፈፀሙ ግብይቶች፣
- ከስፖንሰርሺፕ ከመሳሰሉት የዲጂታል ይዘት ፈጠራ የሚገኝ ገቢ ላይ ግብር እንደሚጣልባቸው በዝርዝር ያስቀምጣል።
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዉይይት እየተደረገበት የሚገኘዉ ይህ ረቂቅ አዋጅ ፤ እነዚህ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች በመደበኛነት የሚከናወኑ ከሆነ፣ የሚገኘው ገቢ በንግድ ስራ ገቢ ስር የሚመደብ ሲሆን፣ የንግድ ስራ ገቢ ግብርም የሚከፈልበት መሆኑን ይገልጻል።
ሆኖም፣ በአዋጁ የተቀመጡትን መስፈርቶች የማያሟላ ከሆነ፣ ገቢው " ሌሎች ገቢዎች " በሚለው ስር ተመድቦ ከጠቅላላ ገቢው ላይ 15% (አስራ አምስት በመቶ) ግብር እንዲከፈልበት ይደረጋል ይላል።
ከዚህ በተጨማሪም፣ ለዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች ክፍያ የሚያመቻቹ መድረኮች ለእያንዳንዱ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪ የተከፈለውን ገንዘብ የሚያሳይ ሪፖርት ለታክስ ባለስልጣን የመላክ ግዴታ እንደሚኖርባቸው ያስቀምጣል።
ይህን ተከትሎም፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) የማውጣት ፣ ገቢያቸውን የማስታወቅ እና ሌሎች የታክስ ከፋይ ግዴታዎችን የመወጣት ሃላፊነት እንደሚጠበቅባቸው ያስገድዳል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የካፒታል ጋዜጣ ነው። #CAPITAL
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤1.19K😭449😡312👏111🤔73🕊30😱23🙏21💔15🥰13😢11
Calling all #Ethiopian Innovators!
The second round of the Immunisation Innovation Accelerator is now open - offering up to $100,000 in grants to solutions that improve #vaccine access.
📅 Application deadline: July 27
🔗 https://www.stc-accelerator.org/
#ChildHealth #InnovationInAction #HealthInnovation #Ethiopia
The second round of the Immunisation Innovation Accelerator is now open - offering up to $100,000 in grants to solutions that improve #vaccine access.
📅 Application deadline: July 27
🔗 https://www.stc-accelerator.org/
#ChildHealth #InnovationInAction #HealthInnovation #Ethiopia
❤109🙏6😱5🤔4😢2🥰1👏1
TIKVAH-ETHIOPIA
" በተማሪነትም ሆነ በቱሪስት ቪዛ ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ዜጎቻችን ከተፈቀደላቸው የቪዛ ቆይታ ጊዜ በላይ በአሜሪካ መቆየት በአሁኑ ወቅት ተቀባይነት የሌለውና ከፍተኛ ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑን መገንዘብ ያሻል " - አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የአሜሪካ ቪዛ የያዙ ኢትዮጵያውያና የሌላ አገር ዜግነት ያላቸው ዜጎች ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ከቆዩ ቅጣት እንደሚከተላቸው…
#Ethiopia🇪🇹
" ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ የሚያደርጉ የአሜሪካ ፓስፓርት የያዙ ትውልደ ኢትዮጵያውያን፣ የሌሎች ሃገራት ዜግነት ያላቸው ግለሰቦች የኢትዮጵያን ቪዛ ለማግኘት ወደ አገራችን ሲመጡ ከተፈቀደላቸው የቆይታ ጊዜ በላይ መቆየት በሀገራችን ሕግ መሠረት ቅጣት የሚያስከትል በመሆኑ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደረግ ለማሳሰብ እንወዳለን " - አምባሳደር ነብያት ጌታቸው
@tikvahethiopia
" ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ የሚያደርጉ የአሜሪካ ፓስፓርት የያዙ ትውልደ ኢትዮጵያውያን፣ የሌሎች ሃገራት ዜግነት ያላቸው ግለሰቦች የኢትዮጵያን ቪዛ ለማግኘት ወደ አገራችን ሲመጡ ከተፈቀደላቸው የቆይታ ጊዜ በላይ መቆየት በሀገራችን ሕግ መሠረት ቅጣት የሚያስከትል በመሆኑ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደረግ ለማሳሰብ እንወዳለን " - አምባሳደር ነብያት ጌታቸው
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👏407❤196🤔125😡87😭45🙏23💔6😱3🥰2
" ስያሜያችሁ ከብሔር ስም ጋር የተገናኘ ከሆነ መቀየር ይኖርባችኋል " - የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በሀገሪቱ በሁሉም የሊግ እርከን የሚገኙ ክለቦች በ2018 የውድድር ዓመት ምዝገባ ወቅት የክለብ ስያሜያቸው ከብሔር ስም ጋር የተገናኘ ከሆነ በመቀየር ማስመዝገብ እንደሚኖርባቸው አዟል።
ከዚህም በተጨማሪ ክለቦች በኦፊሴላዊ መለያ (አርማ) ላይ ፖለቲካዊ እና የብሔር ይዘት ያላቸው መልዕክቶች እና ምስሎችን መጠቀም የተከለከለ መሆኑን ፌዴሬሽኑ አስገንዝቧል።
#Ethiopia🇪🇹
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በሀገሪቱ በሁሉም የሊግ እርከን የሚገኙ ክለቦች በ2018 የውድድር ዓመት ምዝገባ ወቅት የክለብ ስያሜያቸው ከብሔር ስም ጋር የተገናኘ ከሆነ በመቀየር ማስመዝገብ እንደሚኖርባቸው አዟል።
ከዚህም በተጨማሪ ክለቦች በኦፊሴላዊ መለያ (አርማ) ላይ ፖለቲካዊ እና የብሔር ይዘት ያላቸው መልዕክቶች እና ምስሎችን መጠቀም የተከለከለ መሆኑን ፌዴሬሽኑ አስገንዝቧል።
#Ethiopia
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👏1.76K❤289😡66🙏65🤔24🕊15😭10🥰8😱6💔1
#Save_the_Children #GSK
Calling all #Ethiopian Innovators!
The second round of the Immunisation Innovation Accelerator is now open - offering up to $100,000 in grants to solutions that improve #vaccine access.
📅 Application deadline: July 27
🔗 https://www.stc-accelerator.org/
#ChildHealth #InnovationInAction #HealthInnovation #Ethiopia
Calling all #Ethiopian Innovators!
The second round of the Immunisation Innovation Accelerator is now open - offering up to $100,000 in grants to solutions that improve #vaccine access.
📅 Application deadline: July 27
🔗 https://www.stc-accelerator.org/
#ChildHealth #InnovationInAction #HealthInnovation #Ethiopia
❤91🙏8🕊2😭2
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ETHIOPIA🇪🇹
#GERD
" ግብፅ ግድቡን ታፈነዳዋለች " ሲሉ የነበሩት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት አሁን ግድቡ ሊመረቅ ሲቃረብ " ግድቡ የተሰራው በኛ ገንዘብ ነው " ማለት ጀምረዋል።
ከዚህ ቀደም በነበራቸው የመጀመሪያው የአሜሪካ ፕሬዚዳንትነት የስልጣን ዘመን ኢትዮጵያውያንን " ውሃ ወደ ናይል ወንዝ እንዳይፈስ የሚያቆም ግድብ ገነቡ (ታላቁ የሕዳሴ ግድብን ማለታቸው ነው) ፤ ግብጽ በዚህ ብትበሳጭ መኮነን የለባትም። ግብጽ ግድቡን ታፈነዳዋለች " በሚለው ንግግራቸው የሚታወቁት ዶናልድ ትራምፕ አሁን ደግሞ " ግድቡን በአብዛኛው የገነባነው እኛ ነን " እያሉ ደጋግመው እየተናገሩ ናቸው።
ዶናልድ ትራምፕ በዋይት ሐውስ ለሪፐብሊካን ሴናተሮች የእራት ፕሮግራም ባደረጉበት ምሽት የታላቁ ሕዳሴ ግድብን የሚመለከት ነገር ተናግረዋል።
በዓለም ላይ ያሉ ጦርነቶችን ሰላማዊ እልባት ለመስጠት አሜሪካ እያደረገችው ስላለው ጥረት ተናግረው " ግብፅ እና ኢትዮጵያ በሕዳሴ ግድብ እየተጣሉ መሆኑን ታውቃላችሁ " ብለዋል።
" ኢትዮጵያ ግድቡን የገነባችው በአሜሪካ ገንዘብ ነው፤ በአብዛኛው " ሲሉ ተደምጠዋል።
ትራምፕ አገራቸው መቼ ገንዘቡን እንደሰጠች ወይም በምን መልኩ እንደሆነ ምንም አልተናገሩም።
ፕሬዝደንቱ ዳግም ተመርጠው ስልጣን ላይ ከወጡ በኃላ በተደጋጋሚ አገራቸው ለሕዳሴ ግድብ የገንዘብ ድጋፍ መስጠቷን ሲናገሩ ነበር። በቅርብ ጊዜ ውስጥ እንኳን ሁለት ጊዜ ተናግረዋል፤ የአሁኑ ሶስተኛቸው ነው።
ኢትዮጵያ እስካሁን ለፕሬዚዳንቱ ንግግር ይፋዊ ምላሽ አልሰጠቻቸውም።
ትራምፕ በመጀመሪያው የስልጣን ዘመናቸው " ውሃ ወደ ናይል ወንዝ እንዳይፈስ የሚያቆም ግድብ ገነቡ ፤ ግብጽ በዚህ ብትበሳጭ መኮነን የለባትም። ግብጽ ግድቡን ታፈነዳዋለች፤ ግብጽ እና ኢትዮጵያ ስምምነት ላይ እንዲደርሱ አድርጌ ነበር ኢትዮጵያ ግን ጥላ ወጣች " ብለው ነበር።
ኢትዮጵያ አስገዳጅ ስምምነቱን ጥላ በመውጣቷ ብዙ ድጋፎች እንደተቋረጠባትም ገልጸው ነበር።
ፕሬዜዳንቱ አሁን ዳግም ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ በግልጽ ለግብጽ ወገንተኛ የሆኑ አስተያየቶችን ከመስጠት ባለፈ ከ " ታፈነዳዋለች " አስተያየት " እኛ ነን የገነባነው " ወደማለት መጥተዋል።
#TikvahEthiopiaFamliyAA
@tikvahethiopia
#GERD
" ግብፅ ግድቡን ታፈነዳዋለች " ሲሉ የነበሩት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት አሁን ግድቡ ሊመረቅ ሲቃረብ " ግድቡ የተሰራው በኛ ገንዘብ ነው " ማለት ጀምረዋል።
ከዚህ ቀደም በነበራቸው የመጀመሪያው የአሜሪካ ፕሬዚዳንትነት የስልጣን ዘመን ኢትዮጵያውያንን " ውሃ ወደ ናይል ወንዝ እንዳይፈስ የሚያቆም ግድብ ገነቡ (ታላቁ የሕዳሴ ግድብን ማለታቸው ነው) ፤ ግብጽ በዚህ ብትበሳጭ መኮነን የለባትም። ግብጽ ግድቡን ታፈነዳዋለች " በሚለው ንግግራቸው የሚታወቁት ዶናልድ ትራምፕ አሁን ደግሞ " ግድቡን በአብዛኛው የገነባነው እኛ ነን " እያሉ ደጋግመው እየተናገሩ ናቸው።
ዶናልድ ትራምፕ በዋይት ሐውስ ለሪፐብሊካን ሴናተሮች የእራት ፕሮግራም ባደረጉበት ምሽት የታላቁ ሕዳሴ ግድብን የሚመለከት ነገር ተናግረዋል።
በዓለም ላይ ያሉ ጦርነቶችን ሰላማዊ እልባት ለመስጠት አሜሪካ እያደረገችው ስላለው ጥረት ተናግረው " ግብፅ እና ኢትዮጵያ በሕዳሴ ግድብ እየተጣሉ መሆኑን ታውቃላችሁ " ብለዋል።
" ኢትዮጵያ ግድቡን የገነባችው በአሜሪካ ገንዘብ ነው፤ በአብዛኛው " ሲሉ ተደምጠዋል።
ትራምፕ አገራቸው መቼ ገንዘቡን እንደሰጠች ወይም በምን መልኩ እንደሆነ ምንም አልተናገሩም።
ፕሬዝደንቱ ዳግም ተመርጠው ስልጣን ላይ ከወጡ በኃላ በተደጋጋሚ አገራቸው ለሕዳሴ ግድብ የገንዘብ ድጋፍ መስጠቷን ሲናገሩ ነበር። በቅርብ ጊዜ ውስጥ እንኳን ሁለት ጊዜ ተናግረዋል፤ የአሁኑ ሶስተኛቸው ነው።
ኢትዮጵያ እስካሁን ለፕሬዚዳንቱ ንግግር ይፋዊ ምላሽ አልሰጠቻቸውም።
ትራምፕ በመጀመሪያው የስልጣን ዘመናቸው " ውሃ ወደ ናይል ወንዝ እንዳይፈስ የሚያቆም ግድብ ገነቡ ፤ ግብጽ በዚህ ብትበሳጭ መኮነን የለባትም። ግብጽ ግድቡን ታፈነዳዋለች፤ ግብጽ እና ኢትዮጵያ ስምምነት ላይ እንዲደርሱ አድርጌ ነበር ኢትዮጵያ ግን ጥላ ወጣች " ብለው ነበር።
ኢትዮጵያ አስገዳጅ ስምምነቱን ጥላ በመውጣቷ ብዙ ድጋፎች እንደተቋረጠባትም ገልጸው ነበር።
ፕሬዜዳንቱ አሁን ዳግም ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ በግልጽ ለግብጽ ወገንተኛ የሆኑ አስተያየቶችን ከመስጠት ባለፈ ከ " ታፈነዳዋለች " አስተያየት " እኛ ነን የገነባነው " ወደማለት መጥተዋል።
#TikvahEthiopiaFamliyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤1.2K😡538🤔180😭52💔49🕊31👏26🙏25😱18😢12🥰9