የህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ዛሬ ዋና እምባ ጠባቂ ተሹሞለታል።
በተሿሚዎቹ ላይ ከፖለቲካ ገለልተኛ ስለመሆናቸው ጥያቄ ቢቀርብም ሹመታቸው ፀድቋል፡፡
የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት ወ/ሮ ስመኝ ውቤ ዋና እምባ ጠባቂ ሆነው በህ/ተ/ም/ቤት ተሹመዋል፡፡
የኔነህ ስመኝ (ዶ/ር) ምክትል ዋና እምባ ጠባቂ፣ አቶ አባይነህ አዴቶ ደግሞ የዘርፉ እምባ ጠባቂ ሆነው ተሹመዋል፡፡
ዶ/ር የኔነህ ስመኝ በአማራ ክልል የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት ሆነው እንዳገለገሉ ተነግሯል፡፡
አቶ አባይነህ አዴቶ ደግሞ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፍህና ህግ ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ሰርተዋል።
እጩዎቹ " ከሁሉም ክልል በህዝብ ይፋዊ ጥቆማ ከተሰጠ በኋላ ከም/ቤቱ በተመረጡ የእጩ አቅራቢ ኮሚቴ በተለያዩ መመዘኛዎች መሰረት በተሰጣቸው ነጥብ የተመረጡ ናቸው " ተብሏል፡፡
ከመመዘኛዎቹ መካከል ከፖለቲካ ፓርቲ ነፃ የሆኑ የሚለው አንዱ ቢሆንም ሁሉም እምባ ጠባቂ ሆነው የቀረቡ እጩዎች የመንግስት ከፍተኛ ተሿሚዎች የነበሩ እንደመሆናቸው ገለልተኝነታቸው አጠራጣሪ ነው የሚል ጥያቄ ከምክር ቤት ተነስቶ ነበር፡፡
በተጨማሪም በሰብአዊ መብቶች ላይ የሰሩ የህግ ሰዎች ጠፍተው ነው ወይ ? የሚል ጥያቄም ቀርቧል፡፡
ለዚህ ጥያቄ አፈ ጉባኤው ዝርዝሩን የእጩ አቅራቢ ኮሚቴው ፈትሿል ከማለት ውጭ ቀጥተኛ ምላሽ አልሰጡም፡፡
በምክር ቤቱ የመንግስት ረዳት ተጠሪ ሚኒስተር የሆኑት ተስፋዬ ቤልጅጌ (ዶ/ር) ፤ " የፖለቲካ ፓርቲ አባል ሆነው የነበረ ቢሆንም ከፓርቲው እንዲወጡ ይደረጋል እንጂ እንዳይሾሙ የሚከለክል ህግ የለም " ሲሉ በአጭሩ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
ያም ሆኖ ሹመታቸው በምክር ቤት የፀደቀላቸው የኢትዮጵያ እምባ ጠባቂ ተቋም ተሿሚዎች በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ መሐላ በመፈፀም ሀላፊነታቸውን ተረክበዋል፡፡
የዲሞክራሲ ተቋማት የስራ ሀላፊዎች ከፖለቲካ ገለልተኛ እንዲሆኑ ኢትዮጵያ እውቅና የሰጠችውና የብሔራዊ ሰብአዊ መብቶች ተቋማት አሰራርን በተመለከተ እ.አ.አ በ1993 የወጣው የፓሪስ መርሆች ያስገድዳል።
በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ እምባ ጠባቂ ተቋምን ጨምሮ የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽንና ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስራ ሀላፊዎች ከፖለቲካ ገለልተኛ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
መረጃው የሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
በተሿሚዎቹ ላይ ከፖለቲካ ገለልተኛ ስለመሆናቸው ጥያቄ ቢቀርብም ሹመታቸው ፀድቋል፡፡
የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት ወ/ሮ ስመኝ ውቤ ዋና እምባ ጠባቂ ሆነው በህ/ተ/ም/ቤት ተሹመዋል፡፡
የኔነህ ስመኝ (ዶ/ር) ምክትል ዋና እምባ ጠባቂ፣ አቶ አባይነህ አዴቶ ደግሞ የዘርፉ እምባ ጠባቂ ሆነው ተሹመዋል፡፡
ዶ/ር የኔነህ ስመኝ በአማራ ክልል የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት ሆነው እንዳገለገሉ ተነግሯል፡፡
አቶ አባይነህ አዴቶ ደግሞ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፍህና ህግ ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ሰርተዋል።
እጩዎቹ " ከሁሉም ክልል በህዝብ ይፋዊ ጥቆማ ከተሰጠ በኋላ ከም/ቤቱ በተመረጡ የእጩ አቅራቢ ኮሚቴ በተለያዩ መመዘኛዎች መሰረት በተሰጣቸው ነጥብ የተመረጡ ናቸው " ተብሏል፡፡
ከመመዘኛዎቹ መካከል ከፖለቲካ ፓርቲ ነፃ የሆኑ የሚለው አንዱ ቢሆንም ሁሉም እምባ ጠባቂ ሆነው የቀረቡ እጩዎች የመንግስት ከፍተኛ ተሿሚዎች የነበሩ እንደመሆናቸው ገለልተኝነታቸው አጠራጣሪ ነው የሚል ጥያቄ ከምክር ቤት ተነስቶ ነበር፡፡
በተጨማሪም በሰብአዊ መብቶች ላይ የሰሩ የህግ ሰዎች ጠፍተው ነው ወይ ? የሚል ጥያቄም ቀርቧል፡፡
ለዚህ ጥያቄ አፈ ጉባኤው ዝርዝሩን የእጩ አቅራቢ ኮሚቴው ፈትሿል ከማለት ውጭ ቀጥተኛ ምላሽ አልሰጡም፡፡
በምክር ቤቱ የመንግስት ረዳት ተጠሪ ሚኒስተር የሆኑት ተስፋዬ ቤልጅጌ (ዶ/ር) ፤ " የፖለቲካ ፓርቲ አባል ሆነው የነበረ ቢሆንም ከፓርቲው እንዲወጡ ይደረጋል እንጂ እንዳይሾሙ የሚከለክል ህግ የለም " ሲሉ በአጭሩ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
ያም ሆኖ ሹመታቸው በምክር ቤት የፀደቀላቸው የኢትዮጵያ እምባ ጠባቂ ተቋም ተሿሚዎች በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ መሐላ በመፈፀም ሀላፊነታቸውን ተረክበዋል፡፡
የዲሞክራሲ ተቋማት የስራ ሀላፊዎች ከፖለቲካ ገለልተኛ እንዲሆኑ ኢትዮጵያ እውቅና የሰጠችውና የብሔራዊ ሰብአዊ መብቶች ተቋማት አሰራርን በተመለከተ እ.አ.አ በ1993 የወጣው የፓሪስ መርሆች ያስገድዳል።
በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ እምባ ጠባቂ ተቋምን ጨምሮ የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽንና ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስራ ሀላፊዎች ከፖለቲካ ገለልተኛ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
መረጃው የሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
#EthiopianAirlines🇪🇹
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ ቦይንግ 777F እቃ ጫኝ አውሮፕላን መረከቡን ገልጿል።
ይህ አውሮፕላን የካርጎ ጭነት አገልግሎት አድማስን ለማሳደግ የራሱ አስተዋፅዖ ከማበርከቱ በተጨማሪ እያደገ የመጣውን የካርጎ አገልግሎት ለማስተናገድ የራሱ አስተዋፅዖ ይኖረዋል ብሏል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የካርጎና ሎጂስቲክስ አገልግሎት እየሰጠ ያለውን የላቀ የአየር እቃ ጭነት አገልግሎት አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል።
አሁን የገባው አዲስ የካርጎ አውሮፕላን አየር መንገዱ ማህበራዊ ሀላፊነቱን በመወጣት ረገድ እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራትን የሚያግዙና የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ላይ ለተሰማሩ ተቋማት የሚለገሱ ቁሳቁሶችን ወደ ሀገር ውስጥ ይዞ መምጣቱ ተገልጿል።
#Ethiopia🇪🇹
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ ቦይንግ 777F እቃ ጫኝ አውሮፕላን መረከቡን ገልጿል።
ይህ አውሮፕላን የካርጎ ጭነት አገልግሎት አድማስን ለማሳደግ የራሱ አስተዋፅዖ ከማበርከቱ በተጨማሪ እያደገ የመጣውን የካርጎ አገልግሎት ለማስተናገድ የራሱ አስተዋፅዖ ይኖረዋል ብሏል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የካርጎና ሎጂስቲክስ አገልግሎት እየሰጠ ያለውን የላቀ የአየር እቃ ጭነት አገልግሎት አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል።
አሁን የገባው አዲስ የካርጎ አውሮፕላን አየር መንገዱ ማህበራዊ ሀላፊነቱን በመወጣት ረገድ እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራትን የሚያግዙና የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ላይ ለተሰማሩ ተቋማት የሚለገሱ ቁሳቁሶችን ወደ ሀገር ውስጥ ይዞ መምጣቱ ተገልጿል።
#Ethiopia🇪🇹
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
" በአደጋው የ25 ሰዎች ሲሞቱ፣ 14 ሰዎች ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል " - ፖሊስ
በአማራ ክልል ፤ በሰሜን ወሎ ዞን ፤ ዳውንት ወረዳ ኩርባ ከተማ መነሻውን ያደረገ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ የ25 ስዎች ሕይወት አልፏል።
ዛሬ ጥር 15 2017ዓ.ም ከጥዋቱ 12 :00 ከኩርባ ከተማ ተነስቶ ወደ ደሴ ከተማ ሲጓዝ ነው አደጋው የደረሰው።
የዳውንት ወረዳ ፖሊስ ፅሕፈት ቤት ታርጋ ቁጥሩ ኮድ 3-32917 የሆነ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ከኩርባ ከተማ በግምት 9 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ልዩ ቦታው 04 ቀበሌ ሰጎራ ከተባለ አካባቢ የመገልበጥ አደጋ እንደደረሰበት ገልጿል።
በአደጋውም የ25 ሰዎች ሲሞቱ፣ 14 ሰዎች ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል ብሏል።
በ15 ሰዎች ላይ ቀላል ጉዳት መደረሱ ተገልጿል።
ከባድና ቀላል ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች በደላንታ እና ደሴ ሆስፒታሎች ተወስደዋል።
መረጃው የሰሜን ወሎ ዞን ኮሚኒኬሽን ነው።
@tikvahethiopia
በአማራ ክልል ፤ በሰሜን ወሎ ዞን ፤ ዳውንት ወረዳ ኩርባ ከተማ መነሻውን ያደረገ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ የ25 ስዎች ሕይወት አልፏል።
ዛሬ ጥር 15 2017ዓ.ም ከጥዋቱ 12 :00 ከኩርባ ከተማ ተነስቶ ወደ ደሴ ከተማ ሲጓዝ ነው አደጋው የደረሰው።
የዳውንት ወረዳ ፖሊስ ፅሕፈት ቤት ታርጋ ቁጥሩ ኮድ 3-32917 የሆነ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ከኩርባ ከተማ በግምት 9 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ልዩ ቦታው 04 ቀበሌ ሰጎራ ከተባለ አካባቢ የመገልበጥ አደጋ እንደደረሰበት ገልጿል።
በአደጋውም የ25 ሰዎች ሲሞቱ፣ 14 ሰዎች ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል ብሏል።
በ15 ሰዎች ላይ ቀላል ጉዳት መደረሱ ተገልጿል።
ከባድና ቀላል ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች በደላንታ እና ደሴ ሆስፒታሎች ተወስደዋል።
መረጃው የሰሜን ወሎ ዞን ኮሚኒኬሽን ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray " በየመዋቅሩ ያሉ ም/ቤቶች ጊዚያቸው ያለፈ እና ህጋዊ መሰረታቸው ያበቃ በመሆኑ መሾምና መሻር አይችሉም " ብሎ የነበረው የትግራይ ክልልጊዚያዊ አስተዳደር ምክር ቤቶቹ ህጋዊ መሰረት እንዲኖራቸው የሚያደርግ ደንብ አፅድቀዋል።
የጊዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ የወረዳ ምክር ቤቶች የሚያጠናክር እና ህጋዊ መሰረት እንዲኖራቸው የሚያደርግ ነው ያለውን ደንብ ከሰሞኑን አፅድቋል።
" የፀደቀው ደንብ የወረዳ ም/ቤቶች ተጠናክረው የህዝቡ ተሳትፎ እና ውክልና በሚያረጋግጥ መልኩ እንዲንቀሳቀሱ የሚያስችል የተፈጠረው አለመግባባት የሚቀርፍ ሁሉን በሚያግባባ መልኩ ስራቸው እንዲፈፅሙ የሚያስችላቸው ነው " ብሏል።
ደንቡ ተፈፃሚነት እንዲኖረው ሁሉም የበኩሉ እንዲወጣ ያሳሰበው የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደሩ ፤ አስከታች ድረስ ያለው መንግስታዊ እና አስተዳዳራዊ መዋቅር ተጠናክሮ ህዝቡ የሚገባውን አገልግሎት ማግኘት አለበት ብሏል።
@tikvahethiopia
የጊዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ የወረዳ ምክር ቤቶች የሚያጠናክር እና ህጋዊ መሰረት እንዲኖራቸው የሚያደርግ ነው ያለውን ደንብ ከሰሞኑን አፅድቋል።
" የፀደቀው ደንብ የወረዳ ም/ቤቶች ተጠናክረው የህዝቡ ተሳትፎ እና ውክልና በሚያረጋግጥ መልኩ እንዲንቀሳቀሱ የሚያስችል የተፈጠረው አለመግባባት የሚቀርፍ ሁሉን በሚያግባባ መልኩ ስራቸው እንዲፈፅሙ የሚያስችላቸው ነው " ብሏል።
ደንቡ ተፈፃሚነት እንዲኖረው ሁሉም የበኩሉ እንዲወጣ ያሳሰበው የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደሩ ፤ አስከታች ድረስ ያለው መንግስታዊ እና አስተዳዳራዊ መዋቅር ተጠናክሮ ህዝቡ የሚገባውን አገልግሎት ማግኘት አለበት ብሏል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray " በየመዋቅሩ ያሉ ም/ቤቶች ጊዚያቸው ያለፈ እና ህጋዊ መሰረታቸው ያበቃ በመሆኑ መሾምና መሻር አይችሉም " ብሎ የነበረው የትግራይ ክልልጊዚያዊ አስተዳደር ምክር ቤቶቹ ህጋዊ መሰረት እንዲኖራቸው የሚያደርግ ደንብ አፅድቀዋል። የጊዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ የወረዳ ምክር ቤቶች የሚያጠናክር እና ህጋዊ መሰረት እንዲኖራቸው የሚያደርግ ነው ያለውን ደንብ ከሰሞኑን አፅድቋል። " የፀደቀው ደንብ…
የትግራይ ጉዳይ ወዴት ?
በትግራይ ክልል ያሉ የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች እንደሆኑ የገለጹ መኮንኖች ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
በዚህም ' የተዳከመ ' ያሉት በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ተነስቶ በሌላ እንዲዋቀር መወሰናቸውን ገልጸዋል።
" የጊዜያዊ አስተዳደሩ እንደ አዲስ እንዲዋቀር ውሳኔ አሳልፈናል " ብለዋል።
" በፕሪቶሪያ ስምምነት መሠረት የተቋቋመው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ኃላፊነቱን በአግባቡ አልተወጣም የሌሎች መጠቀሚያ ሆኗል " የሚል ክስም አቅርበዋል።
" በጊዜያዊ አስተዳደሩ ቁልፍ ሥልጣን የነበራቸው አመራር እና አባላት ከተሰጣቸው ተልዕኮ ውጪ የሕዝብን ጥቅም ወደ ጎን በመተው ክህደት በመፈጸም የውጭ ኃይል መሣሪያ ሆነዋል" ብሏል።
በሕዝብ ጥቅም ላይ ስለደረሰው ጉዳትም ሆነ " የውጭ ኃይል " ያሉት አካል ማንነትን በተመለከተ በግልጽ የተናገሩት ነገር የለም።
የወታደራዊ አመራሮቹ በሰጡት መግለጫ በስፋት ስለ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ድክመት ሲናገሩ የነበረ ሲሆን " የስልጣን ዘመኑን ለማራዘም እየሞከረ ነው " የሚል ክስም አቅርበዋል።
ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ለተካሄደው (በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ቡድን) የህወሓት 14ኛ ጉባኤ እውቅና በመስጠት በጉባኤው ውሳኔ መሠረት የጊዜያዊ አስተዳደር የአመራሮች ለውጥ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።
ይህንን ጉባኤ የምርጫ ቦርድ እንዲሁም ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳና ሌሎች የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች እውቅና እንደነፈጉት ይታወሳል።
ወታደራዊ አመራሮቹ " ህወሓት የትግራይን ጊዜያዊ አስተዳደር ለማሻሻል ያሳለፈው ውሳኔ በአስቸኳይ ተግባራዊ እንዲሆን " ያሉ ሲሆን " ሠራዊቱን ወክለው በጊዜያዊ አስተዳደሩ የካቢኔ አባላት የሆኑትን ግለሰቦች በመገምገም እምነት የሚጣልባቸው ያልሆኑትን በሌሎች እንዲተኩ ወስነናል " ብለዋል።
" ጊዜያዊ አስተዳደሩን በሠራዊቱ ላይ የሚካሄደውን የስም ማጥፋት ዘመቻን መከላከል አልቻለም " በሚል ' በክህደት ' ወንጅለውታል።
በአሁኑ ወቅት በትግራይ ውስጥ ያለው ችግር " ፖለቲካዊ መፍትሄ የሚሻ ነው " ያሉት አመራሮቹ " ማንኛውም ነገር ከትግራይ ሠራዊት አቅም በላይ አይደለም ይህንን ሰበብ በማድረግ የሚደረግ ጣልቃ ገብነትን አንቀበልም " ብለዋል።
አመራሮቹ በደብረፅዮን (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ቡድን በግዚያዊ አስተዳደር ያለው 50+1 ድርሻ እንዲረከብ እንደሚፈልጉ ተናግረዋን።
ከዚህ በተጨማሪ በትግራይ ያሉ ታጣቂዎች በትግራይ ሰላም እና ፀጥታ ሴክሬታሪያት ስር እንዲሆኑ፥ ከዚህ ውጪ በሆነ ላይ ግን እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል።
ዛሬ መግለጫ የሰጡት የትግራይ ኃይሎች ከፍተኛ ወታደራዊ አመራር እንደሆኑ የገለጹት መኮንኖቹ በግልጽ ለደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ቡድን ያደላ አቋም ይዘዋል ፤ ይህ ደግሞ አሁን ላይ በክልሉ ያለውን ሁኔታ አስፍሪ አድርጎታል የሚሉ አስተያየቶች ሲሰጡ መመልከት ችለናል።
ህወሓት በአቶ ጌታቸው ረዳ እና ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ለሁለት ተከፍሎ ላለፉት ወራት እጅግ በጣም በከረረ የመግለጫ እና የሚዲያ ምልልስ ላይ ሲሆን የታጣቂ ኃይሎች እስካሁን በክልሉ ጉዳይ በይፋ አቋማቸውን ሲገልጹ አልታዩም ፤ የዛሬው ለደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት ያደላ የድጋፍ መግለጫ ጉዳዩ ወዴት ያመራ ይሆን ? የሚል ስጋት ደቅኗል።
ትግራይ በርካቶች ያለቁበትን እጅግ አስከፊ የሆነ ጦርነት አስተናግዳ ከህመሟ ገና ያላገገማች ሲሆን አሁን በክልሉ ያለው መካረር መፍትሄ አለማግኘቱ ብዙዎችን እያሳዘነ ይገኛል።
#BBCTigrigna
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
በትግራይ ክልል ያሉ የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች እንደሆኑ የገለጹ መኮንኖች ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
በዚህም ' የተዳከመ ' ያሉት በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ተነስቶ በሌላ እንዲዋቀር መወሰናቸውን ገልጸዋል።
" የጊዜያዊ አስተዳደሩ እንደ አዲስ እንዲዋቀር ውሳኔ አሳልፈናል " ብለዋል።
" በፕሪቶሪያ ስምምነት መሠረት የተቋቋመው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ኃላፊነቱን በአግባቡ አልተወጣም የሌሎች መጠቀሚያ ሆኗል " የሚል ክስም አቅርበዋል።
" በጊዜያዊ አስተዳደሩ ቁልፍ ሥልጣን የነበራቸው አመራር እና አባላት ከተሰጣቸው ተልዕኮ ውጪ የሕዝብን ጥቅም ወደ ጎን በመተው ክህደት በመፈጸም የውጭ ኃይል መሣሪያ ሆነዋል" ብሏል።
በሕዝብ ጥቅም ላይ ስለደረሰው ጉዳትም ሆነ " የውጭ ኃይል " ያሉት አካል ማንነትን በተመለከተ በግልጽ የተናገሩት ነገር የለም።
የወታደራዊ አመራሮቹ በሰጡት መግለጫ በስፋት ስለ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ድክመት ሲናገሩ የነበረ ሲሆን " የስልጣን ዘመኑን ለማራዘም እየሞከረ ነው " የሚል ክስም አቅርበዋል።
ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ለተካሄደው (በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ቡድን) የህወሓት 14ኛ ጉባኤ እውቅና በመስጠት በጉባኤው ውሳኔ መሠረት የጊዜያዊ አስተዳደር የአመራሮች ለውጥ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።
ይህንን ጉባኤ የምርጫ ቦርድ እንዲሁም ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳና ሌሎች የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች እውቅና እንደነፈጉት ይታወሳል።
ወታደራዊ አመራሮቹ " ህወሓት የትግራይን ጊዜያዊ አስተዳደር ለማሻሻል ያሳለፈው ውሳኔ በአስቸኳይ ተግባራዊ እንዲሆን " ያሉ ሲሆን " ሠራዊቱን ወክለው በጊዜያዊ አስተዳደሩ የካቢኔ አባላት የሆኑትን ግለሰቦች በመገምገም እምነት የሚጣልባቸው ያልሆኑትን በሌሎች እንዲተኩ ወስነናል " ብለዋል።
" ጊዜያዊ አስተዳደሩን በሠራዊቱ ላይ የሚካሄደውን የስም ማጥፋት ዘመቻን መከላከል አልቻለም " በሚል ' በክህደት ' ወንጅለውታል።
በአሁኑ ወቅት በትግራይ ውስጥ ያለው ችግር " ፖለቲካዊ መፍትሄ የሚሻ ነው " ያሉት አመራሮቹ " ማንኛውም ነገር ከትግራይ ሠራዊት አቅም በላይ አይደለም ይህንን ሰበብ በማድረግ የሚደረግ ጣልቃ ገብነትን አንቀበልም " ብለዋል።
አመራሮቹ በደብረፅዮን (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ቡድን በግዚያዊ አስተዳደር ያለው 50+1 ድርሻ እንዲረከብ እንደሚፈልጉ ተናግረዋን።
ከዚህ በተጨማሪ በትግራይ ያሉ ታጣቂዎች በትግራይ ሰላም እና ፀጥታ ሴክሬታሪያት ስር እንዲሆኑ፥ ከዚህ ውጪ በሆነ ላይ ግን እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል።
ዛሬ መግለጫ የሰጡት የትግራይ ኃይሎች ከፍተኛ ወታደራዊ አመራር እንደሆኑ የገለጹት መኮንኖቹ በግልጽ ለደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ቡድን ያደላ አቋም ይዘዋል ፤ ይህ ደግሞ አሁን ላይ በክልሉ ያለውን ሁኔታ አስፍሪ አድርጎታል የሚሉ አስተያየቶች ሲሰጡ መመልከት ችለናል።
ህወሓት በአቶ ጌታቸው ረዳ እና ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ለሁለት ተከፍሎ ላለፉት ወራት እጅግ በጣም በከረረ የመግለጫ እና የሚዲያ ምልልስ ላይ ሲሆን የታጣቂ ኃይሎች እስካሁን በክልሉ ጉዳይ በይፋ አቋማቸውን ሲገልጹ አልታዩም ፤ የዛሬው ለደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት ያደላ የድጋፍ መግለጫ ጉዳዩ ወዴት ያመራ ይሆን ? የሚል ስጋት ደቅኗል።
ትግራይ በርካቶች ያለቁበትን እጅግ አስከፊ የሆነ ጦርነት አስተናግዳ ከህመሟ ገና ያላገገማች ሲሆን አሁን በክልሉ ያለው መካረር መፍትሄ አለማግኘቱ ብዙዎችን እያሳዘነ ይገኛል።
#BBCTigrigna
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" በአደጋው የ25 ሰዎች ሲሞቱ፣ 14 ሰዎች ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል " - ፖሊስ በአማራ ክልል ፤ በሰሜን ወሎ ዞን ፤ ዳውንት ወረዳ ኩርባ ከተማ መነሻውን ያደረገ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ የ25 ስዎች ሕይወት አልፏል። ዛሬ ጥር 15 2017ዓ.ም ከጥዋቱ 12 :00 ከኩርባ ከተማ ተነስቶ ወደ ደሴ ከተማ ሲጓዝ ነው አደጋው የደረሰው። የዳውንት ወረዳ ፖሊስ ፅሕፈት…
" ሁለት ሰዎች ወዲያው ሲሞቱ አንድ ሰው ከባድ አንድ ሰው ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል " - ፖሊስ
ዛሬ ከቀኑ 7:00 ሠዐት በአማራ ክልል፣ ሰሜን ሸዋ ዞን በሞጃና ወደራ ወረዳ ዙብአንባ ቀበሌ ልዩ ቦታው ሞፈር ውሀ ጅረት አካባቢ ከአበባ ወደ መሀልሜዳ ሲጓዝ የነበረ ተሽከርካሪ መንገድ ስቶ በመገልበጡ 2 ሠወች ወዲያው ሲሞቱ አንድ ሠው ከባድና አንድ ሠው ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱን የአማራ ፖሊስ አሳውቋል።
ተጎጅዎች በደብረብረሀን ሪፈራል ሆስፒታል እየታከሙ ናቸው።
ዛሬ በዚሁ በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ፤ ዳውንት ወረዳ ኩርባ ከተማ መነሻውን ያደረገና ወደ ደሴ ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ የ25 ስዎች ሕይወት ማለፉ ይታወቃል።
@tikvahethiopia
ዛሬ ከቀኑ 7:00 ሠዐት በአማራ ክልል፣ ሰሜን ሸዋ ዞን በሞጃና ወደራ ወረዳ ዙብአንባ ቀበሌ ልዩ ቦታው ሞፈር ውሀ ጅረት አካባቢ ከአበባ ወደ መሀልሜዳ ሲጓዝ የነበረ ተሽከርካሪ መንገድ ስቶ በመገልበጡ 2 ሠወች ወዲያው ሲሞቱ አንድ ሠው ከባድና አንድ ሠው ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱን የአማራ ፖሊስ አሳውቋል።
ተጎጅዎች በደብረብረሀን ሪፈራል ሆስፒታል እየታከሙ ናቸው።
ዛሬ በዚሁ በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ፤ ዳውንት ወረዳ ኩርባ ከተማ መነሻውን ያደረገና ወደ ደሴ ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ የ25 ስዎች ሕይወት ማለፉ ይታወቃል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የትግራይ ጉዳይ ወዴት ? በትግራይ ክልል ያሉ የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች እንደሆኑ የገለጹ መኮንኖች ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር። በዚህም ' የተዳከመ ' ያሉት በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ተነስቶ በሌላ እንዲዋቀር መወሰናቸውን ገልጸዋል። " የጊዜያዊ አስተዳደሩ እንደ አዲስ እንዲዋቀር ውሳኔ አሳልፈናል " ብለዋል። " በፕሪቶሪያ ስምምነት መሠረት የተቋቋመው የትግራይ…
🚨#Alert
" የወጣው መግለጫ ግልፅ የሆነ መፈንቀለ መንግስት ያወጀ እና የፕሪቶሪያውን ውል ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው ! " - የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር
" ህጋዊ ያልሆነ ቡድን ደግፎ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ለማፍረስ ፤ ስርዓት አልበኝነት ለማስፈን እና ሰራዊቱን ለመበተን መንቀሳቀስ ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ " የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አስታወቀ።
ጊዚያዊ አስተዳደሩ ዛሬ ጥር 15/2017 ዓ.ም በትግራይ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮች ስም የወጣው መግለጫ አላማውን የሳተ እና ሰራዊቱ ከተሰጠው ተልእኮ ውጭ ነው ብሏል።
ጊዚያዊ አስተዳደሩ ፤ " በሰራዊት ከፍተኛ አዣዦች ስም የወጣው መግለጫ እንደማያውቀው በማንኛውም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለው ያልተለመደ ተግባር ነው " ብሎታል።
የጊዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ " ያልተለመደ ተግባር " ሲል የገለፀውን ውሳኔ አስመልክቶ ለመወያየት አስቸኳይ ስብሰባ መጥራቱን እና ሁኔታውን መርምሮ ዝርዝር ማብራርያ እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።
" በከፍተኛ የሰራዊት አዛዦች ስም የወጣው መግለጫ ግልፅ የሆነ መፈንቀለ መንግስት ያወጀ እና የፕሪቶሪያውን ውል ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው " ብሏል ጊዚያዊ አስተዳደሩ።
" ሃላፊነት የጎደለውን ውሳኔው ወደ ታች ለማውረድ ጥድፍያ የተሞላበት እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ መሆኑ ደርሼቤታለሁ " ያለው የጊዚያዊ አስተዳደሩ " የሚያስከትለው አደጋው እጅግ ከፍተኛ መሆኑ በመረዳት ተግባሩ በአስቸኳይ መቆም አለበት " ሲል አስጠንቅቋል።
" መላው የፀጥታ አካላት ህገ-ወጥ ውሳኔው የህዝቡን ችግር የሚያባብስ የጦርነት አዋጅ እና ስርዓት አልበኝነት የሚያስከትል መሆኑ በመገንዘብ በፅናት እንድትቃወሙት ትእዛዙን ተግባራዊ እንዳታደርጉ አስታውቃለሁ " ሲልም አክሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" የወጣው መግለጫ ግልፅ የሆነ መፈንቀለ መንግስት ያወጀ እና የፕሪቶሪያውን ውል ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው ! " - የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር
" ህጋዊ ያልሆነ ቡድን ደግፎ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ለማፍረስ ፤ ስርዓት አልበኝነት ለማስፈን እና ሰራዊቱን ለመበተን መንቀሳቀስ ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ " የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አስታወቀ።
ጊዚያዊ አስተዳደሩ ዛሬ ጥር 15/2017 ዓ.ም በትግራይ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮች ስም የወጣው መግለጫ አላማውን የሳተ እና ሰራዊቱ ከተሰጠው ተልእኮ ውጭ ነው ብሏል።
ጊዚያዊ አስተዳደሩ ፤ " በሰራዊት ከፍተኛ አዣዦች ስም የወጣው መግለጫ እንደማያውቀው በማንኛውም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለው ያልተለመደ ተግባር ነው " ብሎታል።
የጊዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ " ያልተለመደ ተግባር " ሲል የገለፀውን ውሳኔ አስመልክቶ ለመወያየት አስቸኳይ ስብሰባ መጥራቱን እና ሁኔታውን መርምሮ ዝርዝር ማብራርያ እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።
" በከፍተኛ የሰራዊት አዛዦች ስም የወጣው መግለጫ ግልፅ የሆነ መፈንቀለ መንግስት ያወጀ እና የፕሪቶሪያውን ውል ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው " ብሏል ጊዚያዊ አስተዳደሩ።
" ሃላፊነት የጎደለውን ውሳኔው ወደ ታች ለማውረድ ጥድፍያ የተሞላበት እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ መሆኑ ደርሼቤታለሁ " ያለው የጊዚያዊ አስተዳደሩ " የሚያስከትለው አደጋው እጅግ ከፍተኛ መሆኑ በመረዳት ተግባሩ በአስቸኳይ መቆም አለበት " ሲል አስጠንቅቋል።
" መላው የፀጥታ አካላት ህገ-ወጥ ውሳኔው የህዝቡን ችግር የሚያባብስ የጦርነት አዋጅ እና ስርዓት አልበኝነት የሚያስከትል መሆኑ በመገንዘብ በፅናት እንድትቃወሙት ትእዛዙን ተግባራዊ እንዳታደርጉ አስታውቃለሁ " ሲልም አክሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 🔴 “ በጥሩ ሁኔታ በመግባባት ጥያቄያቸው ተመልሷል ” - ማኀበሩ 🔵 “ 20% የደመወዝ ጭማሪ አድርገው በኋላ ደግሞ ሥራ ጀምረን ሌላውን ለማስተካከል ተስማምተናል ” - ሠራተኞቹ ✅ “ ከየካቲት 1/2017 ዓ/ም ጀምሮ 20% የደመወዝ ጭማሪ የሚደረግ መሆኑን ስምምነት ላይ ደርሰናል ” - ፌደሬሽኑ በአይሰን ኤክስፕሪያንስ መሠረታዊ መሠራተኞች ማኀበር ሥር የሚተዳደሩት የሳፋሪኮም ኮልሴንተርና…
#Update
“ ቃል በገባነው መሠረት ሁላችንም ሠራተኞች ወደ ሥራ ተመልሰናል። ግን ገና የሚስተካከሉ ነገሮች አሉ ” - ሠራተኞቹ
በርካታ ቅሬታዎች ያደሩባቸው ከ350 በላይ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኮልሴንተርና ሲምካርድ አፕሱቫል ሠራተኞች ለቅሬታቸው አጥጋቢ ምላሽ ባለማግኘታቸው የሥራ ማቆም አድማ መምታታቸውን መግለጻቸው አይዘነጋም።
“ የሳፋሪኮም ኮልሴንተርና ሲምካርድ አፕሩቫል ሰርቪሶች ተቋርጠዋል ” ብለው የነበረ ሲሆን፣ ሠራተኞቹን የሚያስተዳድረው አይሰን የተሰኘው ድርጅት ቅሬታውን በውይይት እንደፈታ ትላንት ምላሽ ሰጥቶን ነበር።
የትራንስፖርት መገናኛ ሠራተኛ ማኀበራት ኢንዱስትሪ ፌደሬሽን፣ ሠራተኞቹ ደመወዝ ሊጨመርላቸው ስምምነት ላይ እንደተደረሰ፣ ሌሎች ጥያቄዎቻቸው በሂደት እንዲፈቱ፣ ለዛሬ ሠራተኞቹ ወደ ሥራ እንደሚመለሱ ነግሮን ነበር።
ሠራተኞቹ አቋርጠውት ወደነበረው ሥራ ተመለሱ ?
ለቅሬታዎቻችሁ " መፍትሄ አላገኘንም " በማለት መብታችሁን ለማስከበር ካደረጋችሁት የሥራ ማቆም አድማ በኋላ ዛሬስ ወደ ሥራ ተመለሳችሁ ? ስንል ጠይቀናቸዋል።
ሠራተኞቹም፣ “ ቃል በገባነው መሠረት ሁላችንም ሠራተኞች ወደ ሥራ ተመልሰናል። ግን ገና የሚስተካከሉ ነገሮች አሉ ” የሚል ምላሽ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።
ሠራተኞቹ ፦
“ ሥራ ጀምረናል። ግን ገና ብዙ የሚስተካከሉ ነገሮች አሉ። ሁሉም ቀስ እያሉ ይስተካከላሉ። የደመወዙ ጭማሪ ከየካቲት 1/2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል።
ሌሎቹን ጉዳዮች በተመለከተም ከቀጣይ ሳምንት ጀምረን ወደ ድርድር እንገባለን።
ሁሉም ሠራተኞች ወደ ስራ ተመልሰዋል። ምክንያቱም ማንም ሰው ባደረገው የሥራ አድማ ምክንያት አሉታዊ ነገር እንዳይደርስበት ተፈራርመን ነው የተመለስነው ” ብለዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ የሚፈጠር አዲስ ነገር ካለም የምንከታተልና መረጃም የምናደርሳችሁ ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ ቃል በገባነው መሠረት ሁላችንም ሠራተኞች ወደ ሥራ ተመልሰናል። ግን ገና የሚስተካከሉ ነገሮች አሉ ” - ሠራተኞቹ
በርካታ ቅሬታዎች ያደሩባቸው ከ350 በላይ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኮልሴንተርና ሲምካርድ አፕሱቫል ሠራተኞች ለቅሬታቸው አጥጋቢ ምላሽ ባለማግኘታቸው የሥራ ማቆም አድማ መምታታቸውን መግለጻቸው አይዘነጋም።
“ የሳፋሪኮም ኮልሴንተርና ሲምካርድ አፕሩቫል ሰርቪሶች ተቋርጠዋል ” ብለው የነበረ ሲሆን፣ ሠራተኞቹን የሚያስተዳድረው አይሰን የተሰኘው ድርጅት ቅሬታውን በውይይት እንደፈታ ትላንት ምላሽ ሰጥቶን ነበር።
የትራንስፖርት መገናኛ ሠራተኛ ማኀበራት ኢንዱስትሪ ፌደሬሽን፣ ሠራተኞቹ ደመወዝ ሊጨመርላቸው ስምምነት ላይ እንደተደረሰ፣ ሌሎች ጥያቄዎቻቸው በሂደት እንዲፈቱ፣ ለዛሬ ሠራተኞቹ ወደ ሥራ እንደሚመለሱ ነግሮን ነበር።
ሠራተኞቹ አቋርጠውት ወደነበረው ሥራ ተመለሱ ?
ለቅሬታዎቻችሁ " መፍትሄ አላገኘንም " በማለት መብታችሁን ለማስከበር ካደረጋችሁት የሥራ ማቆም አድማ በኋላ ዛሬስ ወደ ሥራ ተመለሳችሁ ? ስንል ጠይቀናቸዋል።
ሠራተኞቹም፣ “ ቃል በገባነው መሠረት ሁላችንም ሠራተኞች ወደ ሥራ ተመልሰናል። ግን ገና የሚስተካከሉ ነገሮች አሉ ” የሚል ምላሽ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።
ሠራተኞቹ ፦
“ ሥራ ጀምረናል። ግን ገና ብዙ የሚስተካከሉ ነገሮች አሉ። ሁሉም ቀስ እያሉ ይስተካከላሉ። የደመወዙ ጭማሪ ከየካቲት 1/2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል።
ሌሎቹን ጉዳዮች በተመለከተም ከቀጣይ ሳምንት ጀምረን ወደ ድርድር እንገባለን።
ሁሉም ሠራተኞች ወደ ስራ ተመልሰዋል። ምክንያቱም ማንም ሰው ባደረገው የሥራ አድማ ምክንያት አሉታዊ ነገር እንዳይደርስበት ተፈራርመን ነው የተመለስነው ” ብለዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ የሚፈጠር አዲስ ነገር ካለም የምንከታተልና መረጃም የምናደርሳችሁ ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Hibir Diaspora
For Ethiopians & Ethiopians with foreign nationalities who are living and working abroad.
For more information visit our website
https://www.hibretbank.com.et/diaspora/
Hibret Bank
United, We prosper!
📞Call us toll-free at 995.
🤳 Join our Telegram community and connect with us. https://t.iss.one/HibretBanket
🌐 Follow us across all our social media platforms and visit our website on linktr.ee/Hibret.Bank
For Ethiopians & Ethiopians with foreign nationalities who are living and working abroad.
For more information visit our website
https://www.hibretbank.com.et/diaspora/
Hibret Bank
United, We prosper!
📞Call us toll-free at 995.
🤳 Join our Telegram community and connect with us. https://t.iss.one/HibretBanket
🌐 Follow us across all our social media platforms and visit our website on linktr.ee/Hibret.Bank