" አብዛኛዎቹ ከአፍሪካ ናቸው !! "
በመጠናቀቅ ላይ ባለው የፈረንጆች 2024 ባሕር አቋርጠው ወደ ስፔን ለመግባት የሞከሩ ቢያንስ 10 ሺሕ 457 ስደተኞች መሞታቸውን ' ካሚናንዶ ፍሮንቴራስ ' የተባለ መንግሥታዊ ያልሆነ ተቋም አስታውቋል።
ካለፈው ዓመት ጋራ ሲነጻጸር በ58 በመቶ ጭማሪ እንዳሳየም ድርጅቱ ጠቁሟል።
በአሐዙ መሠረት በቀን 30 ፍልሰተኞች ወደ ስፔን ለመሻገር ሲሞክሩ ሕይወታቸውን ያጣሉ። ይህም ከ2023 ጋራ ሲነጻጸር በ18 ጨምሯል።
ከሟቾቹ ውስጥ 1 ሺሕ 538 ሕጻናትና 421 ሴቶች እንደሚገኙበት ተገልጿል።
ድርጅቱ መረጃ መሰብሰብ ከጀመረበት ከእ.አ.አ. አቆጣጠር 2007 ወዲህ ከፍተኛው የሟቾች ቁጥር የተመዘገበበት ዓመት መሆኑም ተነግሯል።
በወጉ ያልተሠሩ ጀልባዎች፣ አደገኛ የባሕር ላይ ሁኔታዎች እንዲሁም የነፍስ አድን አገልግሎት ሰጪዎች በቂ አቅም ስለሌላቸው ችግሩ ሊባባስ መቻሉንም ድርጅቱ ጠቁሟል።
ተጎጂዎቹ ከ28 ሀገራት ሲሆኑ በዋነኝነት ግን ከአፍሪካ ናቸው።
በዓመቱ 60 ሺሕ 216 ፍልሰተኞች ስፔን መግባታቸው መታወቁን ቪኦኤ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
በመጠናቀቅ ላይ ባለው የፈረንጆች 2024 ባሕር አቋርጠው ወደ ስፔን ለመግባት የሞከሩ ቢያንስ 10 ሺሕ 457 ስደተኞች መሞታቸውን ' ካሚናንዶ ፍሮንቴራስ ' የተባለ መንግሥታዊ ያልሆነ ተቋም አስታውቋል።
ካለፈው ዓመት ጋራ ሲነጻጸር በ58 በመቶ ጭማሪ እንዳሳየም ድርጅቱ ጠቁሟል።
በአሐዙ መሠረት በቀን 30 ፍልሰተኞች ወደ ስፔን ለመሻገር ሲሞክሩ ሕይወታቸውን ያጣሉ። ይህም ከ2023 ጋራ ሲነጻጸር በ18 ጨምሯል።
ከሟቾቹ ውስጥ 1 ሺሕ 538 ሕጻናትና 421 ሴቶች እንደሚገኙበት ተገልጿል።
ድርጅቱ መረጃ መሰብሰብ ከጀመረበት ከእ.አ.አ. አቆጣጠር 2007 ወዲህ ከፍተኛው የሟቾች ቁጥር የተመዘገበበት ዓመት መሆኑም ተነግሯል።
በወጉ ያልተሠሩ ጀልባዎች፣ አደገኛ የባሕር ላይ ሁኔታዎች እንዲሁም የነፍስ አድን አገልግሎት ሰጪዎች በቂ አቅም ስለሌላቸው ችግሩ ሊባባስ መቻሉንም ድርጅቱ ጠቁሟል።
ተጎጂዎቹ ከ28 ሀገራት ሲሆኑ በዋነኝነት ግን ከአፍሪካ ናቸው።
በዓመቱ 60 ሺሕ 216 ፍልሰተኞች ስፔን መግባታቸው መታወቁን ቪኦኤ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
#አዲስአበባ #አሶሳ
➡️ " በስራ ዘመን ቆይታዬ ይህን ያህል ክብደት የሚመዝን ልጅ ሲወለድ የመጀመሪያው ነው " - ዶ/ር ረታ ትዕዛዙ (ዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል
👉 " የ3 ቀን ጨቅላ ህፃን አንገቷ ላይ በአፈጣጠር ትልቅ እብጠት ይዛ የተወለደች ቢሆንም የተሳካ ቀዶ ህክምና ተደርጎላታል አሁን በተሻለ የጤና ሁኔታ ላይ ናት " - አሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል
በአዲስ አበባ ዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል ቤቴልሄም አመኑ የተባለች እናት 6 ኪሎ ግራም የሚመዝን ወንድ ልጅ በተደረገላት የቀዶ ህክምና በሰላም ተገላገለች።
የሆስፒታሉ የማህፀን ስፔሻሊስት እና የዲፓርትመንት ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ረታ ትዕዛዙ ለኢቢሲ በሰጡት ቃል " በስራ ዘመን ቆይታዬ ይህን ያህል ክብደት የሚመዝን ልጅ ሲወለድ የመጀመሪያው ነው " ብለዋል።
ልጆች ከ5 ኪሎ በላይ ሆነው ሲወለዱ የሚደረግላቸው ህክምና መኖሩን የገለጹት ዶ/ር " ለልጁ የህክምና ክትትል እየተደረገለት ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
በሌላ መረጃ በአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል የተሳካ ቀዶ ህክምና ተደርጓል።
የ3 ቀን ጨቅላ ህፃን አንገቷ ላይ በአፈጣጠር ትልቅ እብጠት (Bilateral huge cystic hygroma) ይዛ የተወለደች ስትሆን በእብጠቱ ምክንያት ጡት መጥባትም ሆነ እንደ ልቧዋ መተንፈስ አትችልም ነበር።
በ13/4/17 ዓ/ም በሆስፒታሉ የተሳካ ቀዶ ህክምና ተደርጎላት አሁን በተሻለ የጤና ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ ተገልጿል።
አሁን እንደልቧ መተንፈስ ጡት መጥባትም ጀምራለች ተብኳል።
በህክምናው ላይ የተሳተፉ ባለሞያዎች ፦
🙏 Surgeons ፦ ዶ/ር ሮቤራ ተሾመ እና ዶ/ር መብራቴ ወ/መድህን
🙏 Anaesthesiologist ፦ ዶ/ር ሲሳይ እብስቱ
🙏 Anesthesia team: ደመቀ ወ/ኪዳን፣ ተሰፋዬ አሰፋ እና ሰለሞን አዳሙ
🙏 Scrub Nurse ፦ሲ/ር ሳይሽልዋል ወርቁ (ቹቹ)
🙏 Circulator Nrs ፦ አልሃጅ ሀሰን እንደሆኑ ሆስፒታሉ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
➡️ " በስራ ዘመን ቆይታዬ ይህን ያህል ክብደት የሚመዝን ልጅ ሲወለድ የመጀመሪያው ነው " - ዶ/ር ረታ ትዕዛዙ (ዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል
👉 " የ3 ቀን ጨቅላ ህፃን አንገቷ ላይ በአፈጣጠር ትልቅ እብጠት ይዛ የተወለደች ቢሆንም የተሳካ ቀዶ ህክምና ተደርጎላታል አሁን በተሻለ የጤና ሁኔታ ላይ ናት " - አሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል
በአዲስ አበባ ዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል ቤቴልሄም አመኑ የተባለች እናት 6 ኪሎ ግራም የሚመዝን ወንድ ልጅ በተደረገላት የቀዶ ህክምና በሰላም ተገላገለች።
የሆስፒታሉ የማህፀን ስፔሻሊስት እና የዲፓርትመንት ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ረታ ትዕዛዙ ለኢቢሲ በሰጡት ቃል " በስራ ዘመን ቆይታዬ ይህን ያህል ክብደት የሚመዝን ልጅ ሲወለድ የመጀመሪያው ነው " ብለዋል።
ልጆች ከ5 ኪሎ በላይ ሆነው ሲወለዱ የሚደረግላቸው ህክምና መኖሩን የገለጹት ዶ/ር " ለልጁ የህክምና ክትትል እየተደረገለት ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
በሌላ መረጃ በአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል የተሳካ ቀዶ ህክምና ተደርጓል።
የ3 ቀን ጨቅላ ህፃን አንገቷ ላይ በአፈጣጠር ትልቅ እብጠት (Bilateral huge cystic hygroma) ይዛ የተወለደች ስትሆን በእብጠቱ ምክንያት ጡት መጥባትም ሆነ እንደ ልቧዋ መተንፈስ አትችልም ነበር።
በ13/4/17 ዓ/ም በሆስፒታሉ የተሳካ ቀዶ ህክምና ተደርጎላት አሁን በተሻለ የጤና ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ ተገልጿል።
አሁን እንደልቧ መተንፈስ ጡት መጥባትም ጀምራለች ተብኳል።
በህክምናው ላይ የተሳተፉ ባለሞያዎች ፦
🙏 Surgeons ፦ ዶ/ር ሮቤራ ተሾመ እና ዶ/ር መብራቴ ወ/መድህን
🙏 Anaesthesiologist ፦ ዶ/ር ሲሳይ እብስቱ
🙏 Anesthesia team: ደመቀ ወ/ኪዳን፣ ተሰፋዬ አሰፋ እና ሰለሞን አዳሙ
🙏 Scrub Nurse ፦ሲ/ር ሳይሽልዋል ወርቁ (ቹቹ)
🙏 Circulator Nrs ፦ አልሃጅ ሀሰን እንደሆኑ ሆስፒታሉ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
🔴“ 14 ተማሪዎች ታስረዋል ” - ድርጅቱ
🔵 “ ስማቸውን ካረጋገጡልኝ እኔ ነኝ የማስፈታቸው። ግን ስምና ዲፓርትመንት አምጡ ስንል ‘አናመጣም’ ነው የሚሉት ” - ኀብረቱ
🟢 “ የታሰሩት መፈታታቸውን እንጂ ያልተፈቱ እንዳሉ መረጃው የለኝም ” - መቐለ ዩኒቨርሲቲ
ከአዲሱ የዩኒቨርሲቲዎች የምግብ ሜኑ ትግበራ ጋር ተያይዞ ተማሪዎች ቅሬታ እያነሱ መሆናቸው የሚታወቅ ሲሆን፣ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም ከቀናት በፊት ከተግበራው ጋር በያያዘ ቅሬታ አድሮባቸው ግርግር ተፈጥሮ ነበር።
በግርግሩ ተማሪዎች ላይ ድብደባና እስር ፣ በንብረት ላይ ደግሞ ውድመት መድረሱን ፣ በኋላም 27 ተማሪዎች ከእስር እንደተፈቱ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ኅብረት ትላንት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጹ ይታወሳል።
ዛሬስ ምን እየተባለ ነው ?
' ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብት ኢትዮጵያ ' የተሰኘው ሀገር በቀል የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅት “ 14 ተማሪዎች ታመታሰራዋል ” የሚል ሪፓርት አውጥቷል።
ተማሪዎቹ ከተማሪ ተወካዮቻቸው ጋር ሲገናኙበት በነበረው የቴሌግራም ገጽ አማካኝነት ከሜኑ ጋር በተያያዘ ተቃውሞ አሰምተው ከቴሌግራም ገጹ እንደታገዱ፣ በዚህም ልላ ከፈቱ የተባሉ ሁለት ተማሪዎች ታኀሳስ 15 ቀን 2017 ዓ/ም በክልሉ የጸጥታ ኃይሎች እንደታሰሩ ሪፓርቱ ያወሳል።
ይህን ተከትሎ በተነሳው ተቃው ደግሞ 14 ተማሪዎች መታሰራቸውን የድርጅቱ ሪፓርት ያመለከተ ሲሆን፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያም ስለጉዳዩ መቐለ ዩኒቨርሲቲን ጠይቋል።
ዩኒቨርሲቲው ምን መለሰ ?
አሁንም ያልተፈቱ ተማሪዎች አሉ እንዴ ? ስንል የጠየቅናቸው አንድ የዩኒቨርቲው አካል፣ “ የታሰሩት መፈታታቸውን እንጂ ያልተፈቱ እንዳሉ መረጃው የለኝም ” ብለዋል።
እኝሁ የዩኒቨርሲቲው አካል፣ “ ምናልባት ቼክ እናድርገው ” በማለት ሁኔታውን አጣርተው ምላሽ እንደሚሰጡ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃል ገብተዋል።
ከዩኒቨርሲቲው በተጨማሪ ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ከተማሪ ተወካዮቻቸው ጋር በሚገናኙት የቴሌግራም ገጹ አማካኝነት ስለምግብ ሜኑው ተቃውሞ ያነሱ ተማሪዎች ታስረዋል ? ሲል ለኢትዮጵያ ተማሪዎች ኀብረት ጥያቄ አቀርቧል።
ኀብረቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ምን አለ ?
“ ‘አንድ ዳቦ፣ ሁለት ዳቦ፣ አሸዋ አለው’ በሚለው ጉዳይ ቅሬታ ተነስቶ ነበር። 120 ግራም ነበር አንድ ዳቦ የሚጋገረው አሁን 60፣ 60 ተደርጎ ወደ ሁለት ሆኗል። ግራሙ ላይ የተጨመረ፣ የቀነሰ ነገር የለም።
ሌላው ደግሞ ትላንት 5 ሰዓት ተኩል አካባቢ እኔ ራሴ አስወጥታቸው ታስረው የነበሩ 27 ተማሪዎችን ሌሊት ላይ ግን ‘ሲቀጠቀጡ ከነበሩ የመለቐ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መካከል አንዱ ሞቷል’ ብለው ፓስት አደረጉ።
ሌሊት ሄደን አይደር ግቢ አረጋጋግጥን ምንም እንደሌለ ሪፓርት አደረግን። ከዛ ደግሞ 8 ሰዓት ፓስት ተደረገ። ግን በእነዚህ ሦስትና አራት ቀናት በአይደር ግቢ ውስጥ የሞተ ተማሪ የለም።
ይሄ አሉባልታ ወሬ መሆኑ መታወቅ አለበት። እሱን ሀንድል ካደረግን በኋላ ደግሞ ተመልሰው ‘የታፈኑ ተማሪዎች’ አሉ ወደሚል መጡ። የታሰሩ እንኳ አላሉም። የታሰሩ ቢሉማ ወደ ህግ ነው። ‘ታፍነዋል’ ነው እየተባለ ያለው።
ይህም አይደለም። እርግጠኛ ከሆኑ የታፈኑ ተማሪዎችን እነማን ናቸው ? የት ዲፓርትመንት ናቸው ? መቼ ተወሰዱ ? ማንስ ወሰዳቸው። የሚለውን ማጣራት ግድ ነው።
ታስረው የነበሩ ተማሪዎችን ስማቸውንና ዲፓርትመንታቸውን ስላወቅን ነው ያስፈታናቸው። አሁን ግን ' ይባላል ' ነው እየተባለ ያለው። በይባላል ስለተባለ ይሆናል ማለት አይደለም። እስር ቤት ተኪዶ ቼክ የሚደረግ ነው።
የታፈኑትን ተማሪዎች ስም ዝርዝር ስጡን ስንልም ‘አንሰጥም’ በማለት ዝም ብለው ‘ታፍነዋል’ ይላሉ። ስም ለማስጠቆር የሚሄዱት ዘዴ ነው ሌላ ምንም የተደረገ ነገር የለም።
‘ተማሪዎች ተደብድበዋል፣ ንብረት ወድሟል፣ ተማሪዎች ተፈትተዋል። ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ነው ” ብሏል ኅብረቱ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብት ኢትዮጵያ የተሰኘው ድርጅት ያወጣውን ሪፓርት አይታችሁት ነበር ? ሲል ለኅብረቱ ተጨማሪ ጥያቄ አቅርቧል።
ኅብረቱ በምላሹ፣ “ አይቸዋለሁ። ይሄ ዝም ብሎ የለቃቀመው ነው እንጂ ትክክል አይደለም ” ብሎ፣ “ መሬት ላይ የሌለ ነገር ሆነ የሚባል ከሆነ ለቀጣይ ትውልድ ምንድን ነው የምናስተላልፈው? ” ሲል ጠይቋል።
አክሎ፣ “ እነዚህ 14 ተማሪዎች ማን ማን ይባላሉ ? ምን ድፓርትመንት ናቸው ? የስንተኛ ዓመት ናቸው ? የሚመውን ይናጋገሩ ” ሲል ገልጿል።
“ ኣዲ ሓቂ ከተማ ፓሊስ ጣቢያ ታስረዋል ” ነው የተባለውና ቼክ አድርጋችሁ ነበር ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ፣ “ ኣዲ ሓቂ ታስረው የነበሩን አስፈትተናቸዋል ” የሚል ምላሽ ሰጥቷል።
“ ስማቸውን ካረጋገጡልኝ (አሁን ታስረው ያሉ) እኔ ነኝ የማስፈታቸው። ግን ስምና ዲፓርትመንት አምጡ ስንል ‘አናመጣም’ ነው የሚሉት ” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ከቴሌግራም ገጹ ተነስተዋል መባሉን በተመለከተ ማብራሪያ እንደሰጥ ስንጠይቀውም፣ ከስድስቱ ግቢዎት የተማሪዎች መገናኛ የቴሌግራም ገጽ ተነስተው ከሆነ እንዳላወቀ፣ ከዋናው ከተማሪዎች ኀብረት ግን የተቀነሰ ተማሪ እንደሌለ ገልጿል። (ጉዳዩን የምንከታተለው ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴“ 14 ተማሪዎች ታስረዋል ” - ድርጅቱ
🔵 “ ስማቸውን ካረጋገጡልኝ እኔ ነኝ የማስፈታቸው። ግን ስምና ዲፓርትመንት አምጡ ስንል ‘አናመጣም’ ነው የሚሉት ” - ኀብረቱ
🟢 “ የታሰሩት መፈታታቸውን እንጂ ያልተፈቱ እንዳሉ መረጃው የለኝም ” - መቐለ ዩኒቨርሲቲ
ከአዲሱ የዩኒቨርሲቲዎች የምግብ ሜኑ ትግበራ ጋር ተያይዞ ተማሪዎች ቅሬታ እያነሱ መሆናቸው የሚታወቅ ሲሆን፣ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም ከቀናት በፊት ከተግበራው ጋር በያያዘ ቅሬታ አድሮባቸው ግርግር ተፈጥሮ ነበር።
በግርግሩ ተማሪዎች ላይ ድብደባና እስር ፣ በንብረት ላይ ደግሞ ውድመት መድረሱን ፣ በኋላም 27 ተማሪዎች ከእስር እንደተፈቱ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ኅብረት ትላንት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጹ ይታወሳል።
ዛሬስ ምን እየተባለ ነው ?
' ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብት ኢትዮጵያ ' የተሰኘው ሀገር በቀል የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅት “ 14 ተማሪዎች ታመታሰራዋል ” የሚል ሪፓርት አውጥቷል።
ተማሪዎቹ ከተማሪ ተወካዮቻቸው ጋር ሲገናኙበት በነበረው የቴሌግራም ገጽ አማካኝነት ከሜኑ ጋር በተያያዘ ተቃውሞ አሰምተው ከቴሌግራም ገጹ እንደታገዱ፣ በዚህም ልላ ከፈቱ የተባሉ ሁለት ተማሪዎች ታኀሳስ 15 ቀን 2017 ዓ/ም በክልሉ የጸጥታ ኃይሎች እንደታሰሩ ሪፓርቱ ያወሳል።
ይህን ተከትሎ በተነሳው ተቃው ደግሞ 14 ተማሪዎች መታሰራቸውን የድርጅቱ ሪፓርት ያመለከተ ሲሆን፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያም ስለጉዳዩ መቐለ ዩኒቨርሲቲን ጠይቋል።
ዩኒቨርሲቲው ምን መለሰ ?
አሁንም ያልተፈቱ ተማሪዎች አሉ እንዴ ? ስንል የጠየቅናቸው አንድ የዩኒቨርቲው አካል፣ “ የታሰሩት መፈታታቸውን እንጂ ያልተፈቱ እንዳሉ መረጃው የለኝም ” ብለዋል።
እኝሁ የዩኒቨርሲቲው አካል፣ “ ምናልባት ቼክ እናድርገው ” በማለት ሁኔታውን አጣርተው ምላሽ እንደሚሰጡ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃል ገብተዋል።
ከዩኒቨርሲቲው በተጨማሪ ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ከተማሪ ተወካዮቻቸው ጋር በሚገናኙት የቴሌግራም ገጹ አማካኝነት ስለምግብ ሜኑው ተቃውሞ ያነሱ ተማሪዎች ታስረዋል ? ሲል ለኢትዮጵያ ተማሪዎች ኀብረት ጥያቄ አቀርቧል።
ኀብረቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ምን አለ ?
“ ‘አንድ ዳቦ፣ ሁለት ዳቦ፣ አሸዋ አለው’ በሚለው ጉዳይ ቅሬታ ተነስቶ ነበር። 120 ግራም ነበር አንድ ዳቦ የሚጋገረው አሁን 60፣ 60 ተደርጎ ወደ ሁለት ሆኗል። ግራሙ ላይ የተጨመረ፣ የቀነሰ ነገር የለም።
ሌላው ደግሞ ትላንት 5 ሰዓት ተኩል አካባቢ እኔ ራሴ አስወጥታቸው ታስረው የነበሩ 27 ተማሪዎችን ሌሊት ላይ ግን ‘ሲቀጠቀጡ ከነበሩ የመለቐ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መካከል አንዱ ሞቷል’ ብለው ፓስት አደረጉ።
ሌሊት ሄደን አይደር ግቢ አረጋጋግጥን ምንም እንደሌለ ሪፓርት አደረግን። ከዛ ደግሞ 8 ሰዓት ፓስት ተደረገ። ግን በእነዚህ ሦስትና አራት ቀናት በአይደር ግቢ ውስጥ የሞተ ተማሪ የለም።
ይሄ አሉባልታ ወሬ መሆኑ መታወቅ አለበት። እሱን ሀንድል ካደረግን በኋላ ደግሞ ተመልሰው ‘የታፈኑ ተማሪዎች’ አሉ ወደሚል መጡ። የታሰሩ እንኳ አላሉም። የታሰሩ ቢሉማ ወደ ህግ ነው። ‘ታፍነዋል’ ነው እየተባለ ያለው።
ይህም አይደለም። እርግጠኛ ከሆኑ የታፈኑ ተማሪዎችን እነማን ናቸው ? የት ዲፓርትመንት ናቸው ? መቼ ተወሰዱ ? ማንስ ወሰዳቸው። የሚለውን ማጣራት ግድ ነው።
ታስረው የነበሩ ተማሪዎችን ስማቸውንና ዲፓርትመንታቸውን ስላወቅን ነው ያስፈታናቸው። አሁን ግን ' ይባላል ' ነው እየተባለ ያለው። በይባላል ስለተባለ ይሆናል ማለት አይደለም። እስር ቤት ተኪዶ ቼክ የሚደረግ ነው።
የታፈኑትን ተማሪዎች ስም ዝርዝር ስጡን ስንልም ‘አንሰጥም’ በማለት ዝም ብለው ‘ታፍነዋል’ ይላሉ። ስም ለማስጠቆር የሚሄዱት ዘዴ ነው ሌላ ምንም የተደረገ ነገር የለም።
‘ተማሪዎች ተደብድበዋል፣ ንብረት ወድሟል፣ ተማሪዎች ተፈትተዋል። ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ነው ” ብሏል ኅብረቱ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብት ኢትዮጵያ የተሰኘው ድርጅት ያወጣውን ሪፓርት አይታችሁት ነበር ? ሲል ለኅብረቱ ተጨማሪ ጥያቄ አቅርቧል።
ኅብረቱ በምላሹ፣ “ አይቸዋለሁ። ይሄ ዝም ብሎ የለቃቀመው ነው እንጂ ትክክል አይደለም ” ብሎ፣ “ መሬት ላይ የሌለ ነገር ሆነ የሚባል ከሆነ ለቀጣይ ትውልድ ምንድን ነው የምናስተላልፈው? ” ሲል ጠይቋል።
አክሎ፣ “ እነዚህ 14 ተማሪዎች ማን ማን ይባላሉ ? ምን ድፓርትመንት ናቸው ? የስንተኛ ዓመት ናቸው ? የሚመውን ይናጋገሩ ” ሲል ገልጿል።
“ ኣዲ ሓቂ ከተማ ፓሊስ ጣቢያ ታስረዋል ” ነው የተባለውና ቼክ አድርጋችሁ ነበር ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ፣ “ ኣዲ ሓቂ ታስረው የነበሩን አስፈትተናቸዋል ” የሚል ምላሽ ሰጥቷል።
“ ስማቸውን ካረጋገጡልኝ (አሁን ታስረው ያሉ) እኔ ነኝ የማስፈታቸው። ግን ስምና ዲፓርትመንት አምጡ ስንል ‘አናመጣም’ ነው የሚሉት ” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ከቴሌግራም ገጹ ተነስተዋል መባሉን በተመለከተ ማብራሪያ እንደሰጥ ስንጠይቀውም፣ ከስድስቱ ግቢዎት የተማሪዎች መገናኛ የቴሌግራም ገጽ ተነስተው ከሆነ እንዳላወቀ፣ ከዋናው ከተማሪዎች ኀብረት ግን የተቀነሰ ተማሪ እንደሌለ ገልጿል። (ጉዳዩን የምንከታተለው ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ሕብር የወጣቶች የቁጠባ ሒሳብ
ከመደበኛ የቁጠባ አይነት የተሻለ ወለድ የሚያስገኝ እንዲሁም ሌሎች ተጨማሪ ጥቅሞችን የያዘ ልዩ የወጣቶች የቁጠባ ሒሳብ ነው፡፡
ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!
📞 ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡
🤳 በቀላሉ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገፃችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡፡ https://t.iss.one/HibretBanket
🌐 ሌሎች የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን linktr.ee/Hibret.Bank ይጎብኙ፡፡
#Youthsaving #hibirYouth #Startsaving
ከመደበኛ የቁጠባ አይነት የተሻለ ወለድ የሚያስገኝ እንዲሁም ሌሎች ተጨማሪ ጥቅሞችን የያዘ ልዩ የወጣቶች የቁጠባ ሒሳብ ነው፡፡
ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!
📞 ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡
🤳 በቀላሉ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገፃችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡፡ https://t.iss.one/HibretBanket
🌐 ሌሎች የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን linktr.ee/Hibret.Bank ይጎብኙ፡፡
#Youthsaving #hibirYouth #Startsaving
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
🔈 #የጤናባለሞያዎችድምጽ
🔴 " ከደመወዝ ጋር ይከፈለናል ብለን በተስፋ ስንጠብቅ አሁንም ሳይከፈለን ቀርቷል " -ቅሬታ አቅራቢ የጤና ባለሞያዎች
🔵 " ምን ያህል ይታገሱ የሚለውን አላውቅም " -የወረዳው አስተዳዳሪ
በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ በ9 ጤና ጣቢያ ውስጥ የሚሰሩ የጤና ባለሞያዎች ከግንቦት 2016 ዓ/ም ጀምሮ የተጠራቀመ የትርፍ ሰዓት ስራ (ዲዩቲ) ክፍያቸው እንዳልተከፈላቸው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ቅሬታ ማቅረባቸው ይታወሳል።
ባለሞያዎቹ ያልተከፈላቸው የ2016 ዓ/ም የግንቦት እና የሰኔ ወር እንዲሁም በ2017 ዓ/ም የ3 ወር በጠቅላላው የ5 ወር የዱዩቲ (የትርፍ ሰዓት) የሰሩበት ክፍያ ነው።
መረጃውን ባጋራንበት ወቅት ባለሞያዎቹ ያልተከፈላቸው የ4 ወር የትርፍ ሰአት ክፍያ የነበረ ሲሆን በወቅቱ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የቃሉ ወረዳ አስተዳዳሪ የሆኑትን አቶ ሙህዲን አህመድን በጉዳዩ ላይ አነጋግሮ ነበር።
አስተዳዳሪው " ክፍያው የዘገየው በየጤና ጣቢያዎቹ የሚሰጠው አገልግሎት እና የሥራ ጫና የሚለያይ በመሆኑ የሚያድረው የጤና ባለሞያ ቁጥርም ይለያያል በዛ ምክንያት ደረጃ ይውጣለትና በሚሰጡት አገልግሎት እና ባለባቸው የስራ ጫና ልክ ይከፈላቸው ተብሎ ይህንን የሚያጣራ ኮሚቴ ተቋቁሞ በወረዳው በሚገኙ በዘጠኙም ጤና ጣቢያዎች እያጣራ ነው ሪፖርቱን እንዳቀረበ ይከፈላቸዋል " ማለታቸው ይታወሳል።
አስተዳዳሪው ይህንን ምላሽ ይስጡ እንጂ የባለሞያዎቹ የትርፍ ሰአት ክፍያ ሳይከፈል 5 ወር ማለፉን የጤና ባለሞያዎች በድጋሚ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
ባለሞያዎቹ " የሰራንበትን ክፍያ እንዲከፈለን ደጋግመን ብንጠይቅም የሚሰማ አመራር በማጣታችን አሁንም ለችግር ተጋልጠናል " ብለዋል።
" በህዳር ወር መጨረሻ ከደመወዝ ጋር ይከፈለናል ብለን በተስፋ ስንጠብቅ አሁንም ሳይከፈለን ቀርቷል ለምን ? ብለን ስንጠይቅ እንደገና በወረዳው ጤና ጥበቃ ኦፊሰሮች ኮሚቴ ተዋቅሮ 9ኙም ጤና ጣቢያዎች ቼክ ይደረጉ ተብሎ ከወረዳ አስተዳደር አቅጣጫ ተቀምጧል በዚህ ወር የሰራችሁበት አይከፈላቹም " የሚል ምላሽ ተሰጥቶናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የወረዳውን አስተዳዳሪ የጤና ባለሞያዎቹ ምን ያህል ጊዜ ይታገሱ ሲል በድጋሚ ጠይቋል " ምን ያህል ይታገሱ የሚለውን አላውቅም በቴክኒክ ኮሚቴው ተጨማሪ ጥናት እየተደረገ ነው እሱ እንዳለቀ ይከፈላቸዋል " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ወረዳው ኮሚቴዎችን አዋቅሮ በዘጠኙም ጤና ጣቢያ ጀምሮት የነበረውን የማጣራት ስራ ካጠናቀቀ በኋላ በድጋሚ ጤና ጣቢያዎቹ በራሳቸው የማጣራት ስራ ጀምረዋል ይህ ለምን ሆነ ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ " ተቋማቱ (ጤና ጣቢያዎቹ) እኛም ቼክ እናድርግ አሉ እኛ ከሰራነው ጋር ያለውን mismatch (ልዩነት) እንየው ከቴክኒኩ ውጤት ጋር ይገጥማል ወይስ ልዩነት አለው የሚለውን ለማየት ፈልገው ስለሆነ እሱ እንዳለቀ ይከፈላል " ሲሉ መልሰዋል።
ሃላፊው በወረዳው ደረጃ የሰሩት የጥናት ውጤት ምን እንደሆነ ከመናገር የተቆጠቡ ሲሆን ተጨማሪ ምላሽ ለመስጠትም ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።
የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ዳንኤል ጋሻው ምን ምላሽ ሰጡ ?
ሃላፊው " የጤና ጣቢያዎቹ አሰራራቸውን ማየት ስላለብን በድጋሚ ጀምረናል የሚሰጡት አገልግሎት እና የባለሞያው ቁጥር ትንሽ ይጣረሳል " ብለዋል።
ጥናቱም በዚህ ሳምንት እንደሚያልቅ እና በውጤቱም መሰረት እንደሚከፈላቸው ተናግረዋል።
" ነገሩን ማስተካከል ስለሚቻል በዚህ ሳምንት ጨርሰን ያለውን ነገር ችግሮቹን ለይተን የሚከፈለው ካለ ይከፈላል ያልሰራበትንም የወሰደ ካለ በምርመራው መሰረት ያሰራውም አካል የወሰደውም አካል ተጠያቂ ይሆናል " ነው ያሉት።
" ጥናት ማድረግ የተለየ ነገር አይደለም አሰራርን መፈተሽ ያለ ነው ለሰራተኛውም ይጠቅማል የሚሰራውን እና የማይሰራውን ለመለየትም ያግዛል " ሲሉ አክለዋል።
ጥናቱን ከጨረሳችሁ በኋላ የቀረውን ክፍያ በሙሉ ትከፍላላቹ ወይስ እየቀነሳቹ ? ስንል ላነሳንላቸው ጥያቄ " እሱን ከጥናቱ በኋላ ነው የምናየው ግን የሰሩበት ይከፈላል " ብለዋል።
በውጤቱ መሰረትም በጣም ኬዝ ሎድ ኖሮባቸው ዝቅተኛ የሚከፈለው ካለ ክፍያውን ሊሻሻል እንደሚችል እና ምንም ሳይሰራ እንደ መርሐ ግብር የሚከፈለው ካለም ክፍያውን ሊያጣ እንደሚችል ጠቁመዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴 " ከደመወዝ ጋር ይከፈለናል ብለን በተስፋ ስንጠብቅ አሁንም ሳይከፈለን ቀርቷል " -ቅሬታ አቅራቢ የጤና ባለሞያዎች
🔵 " ምን ያህል ይታገሱ የሚለውን አላውቅም " -የወረዳው አስተዳዳሪ
በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ በ9 ጤና ጣቢያ ውስጥ የሚሰሩ የጤና ባለሞያዎች ከግንቦት 2016 ዓ/ም ጀምሮ የተጠራቀመ የትርፍ ሰዓት ስራ (ዲዩቲ) ክፍያቸው እንዳልተከፈላቸው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ቅሬታ ማቅረባቸው ይታወሳል።
ባለሞያዎቹ ያልተከፈላቸው የ2016 ዓ/ም የግንቦት እና የሰኔ ወር እንዲሁም በ2017 ዓ/ም የ3 ወር በጠቅላላው የ5 ወር የዱዩቲ (የትርፍ ሰዓት) የሰሩበት ክፍያ ነው።
መረጃውን ባጋራንበት ወቅት ባለሞያዎቹ ያልተከፈላቸው የ4 ወር የትርፍ ሰአት ክፍያ የነበረ ሲሆን በወቅቱ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የቃሉ ወረዳ አስተዳዳሪ የሆኑትን አቶ ሙህዲን አህመድን በጉዳዩ ላይ አነጋግሮ ነበር።
አስተዳዳሪው " ክፍያው የዘገየው በየጤና ጣቢያዎቹ የሚሰጠው አገልግሎት እና የሥራ ጫና የሚለያይ በመሆኑ የሚያድረው የጤና ባለሞያ ቁጥርም ይለያያል በዛ ምክንያት ደረጃ ይውጣለትና በሚሰጡት አገልግሎት እና ባለባቸው የስራ ጫና ልክ ይከፈላቸው ተብሎ ይህንን የሚያጣራ ኮሚቴ ተቋቁሞ በወረዳው በሚገኙ በዘጠኙም ጤና ጣቢያዎች እያጣራ ነው ሪፖርቱን እንዳቀረበ ይከፈላቸዋል " ማለታቸው ይታወሳል።
አስተዳዳሪው ይህንን ምላሽ ይስጡ እንጂ የባለሞያዎቹ የትርፍ ሰአት ክፍያ ሳይከፈል 5 ወር ማለፉን የጤና ባለሞያዎች በድጋሚ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
ባለሞያዎቹ " የሰራንበትን ክፍያ እንዲከፈለን ደጋግመን ብንጠይቅም የሚሰማ አመራር በማጣታችን አሁንም ለችግር ተጋልጠናል " ብለዋል።
" በህዳር ወር መጨረሻ ከደመወዝ ጋር ይከፈለናል ብለን በተስፋ ስንጠብቅ አሁንም ሳይከፈለን ቀርቷል ለምን ? ብለን ስንጠይቅ እንደገና በወረዳው ጤና ጥበቃ ኦፊሰሮች ኮሚቴ ተዋቅሮ 9ኙም ጤና ጣቢያዎች ቼክ ይደረጉ ተብሎ ከወረዳ አስተዳደር አቅጣጫ ተቀምጧል በዚህ ወር የሰራችሁበት አይከፈላቹም " የሚል ምላሽ ተሰጥቶናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የወረዳውን አስተዳዳሪ የጤና ባለሞያዎቹ ምን ያህል ጊዜ ይታገሱ ሲል በድጋሚ ጠይቋል " ምን ያህል ይታገሱ የሚለውን አላውቅም በቴክኒክ ኮሚቴው ተጨማሪ ጥናት እየተደረገ ነው እሱ እንዳለቀ ይከፈላቸዋል " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ወረዳው ኮሚቴዎችን አዋቅሮ በዘጠኙም ጤና ጣቢያ ጀምሮት የነበረውን የማጣራት ስራ ካጠናቀቀ በኋላ በድጋሚ ጤና ጣቢያዎቹ በራሳቸው የማጣራት ስራ ጀምረዋል ይህ ለምን ሆነ ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ " ተቋማቱ (ጤና ጣቢያዎቹ) እኛም ቼክ እናድርግ አሉ እኛ ከሰራነው ጋር ያለውን mismatch (ልዩነት) እንየው ከቴክኒኩ ውጤት ጋር ይገጥማል ወይስ ልዩነት አለው የሚለውን ለማየት ፈልገው ስለሆነ እሱ እንዳለቀ ይከፈላል " ሲሉ መልሰዋል።
ሃላፊው በወረዳው ደረጃ የሰሩት የጥናት ውጤት ምን እንደሆነ ከመናገር የተቆጠቡ ሲሆን ተጨማሪ ምላሽ ለመስጠትም ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።
የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ዳንኤል ጋሻው ምን ምላሽ ሰጡ ?
ሃላፊው " የጤና ጣቢያዎቹ አሰራራቸውን ማየት ስላለብን በድጋሚ ጀምረናል የሚሰጡት አገልግሎት እና የባለሞያው ቁጥር ትንሽ ይጣረሳል " ብለዋል።
ጥናቱም በዚህ ሳምንት እንደሚያልቅ እና በውጤቱም መሰረት እንደሚከፈላቸው ተናግረዋል።
" ነገሩን ማስተካከል ስለሚቻል በዚህ ሳምንት ጨርሰን ያለውን ነገር ችግሮቹን ለይተን የሚከፈለው ካለ ይከፈላል ያልሰራበትንም የወሰደ ካለ በምርመራው መሰረት ያሰራውም አካል የወሰደውም አካል ተጠያቂ ይሆናል " ነው ያሉት።
" ጥናት ማድረግ የተለየ ነገር አይደለም አሰራርን መፈተሽ ያለ ነው ለሰራተኛውም ይጠቅማል የሚሰራውን እና የማይሰራውን ለመለየትም ያግዛል " ሲሉ አክለዋል።
ጥናቱን ከጨረሳችሁ በኋላ የቀረውን ክፍያ በሙሉ ትከፍላላቹ ወይስ እየቀነሳቹ ? ስንል ላነሳንላቸው ጥያቄ " እሱን ከጥናቱ በኋላ ነው የምናየው ግን የሰሩበት ይከፈላል " ብለዋል።
በውጤቱ መሰረትም በጣም ኬዝ ሎድ ኖሮባቸው ዝቅተኛ የሚከፈለው ካለ ክፍያውን ሊሻሻል እንደሚችል እና ምንም ሳይሰራ እንደ መርሐ ግብር የሚከፈለው ካለም ክፍያውን ሊያጣ እንደሚችል ጠቁመዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት እስከምሽቱ 4:00 እንዲሰጥ ተወስኗል " - የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ
በአዲስ አበባ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ አካላት እስከምሽቱ 4:00 የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡ የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ ወስኗል።
በዚህ ውሳኔ መሠረት ማንኛውም የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ፦
- አውቶቡሶች፣
- ሚዲ ባስ
- ሚኒ ባሶች በመደበኛ ቀን በሚትሰሩበት መስመር እና ቀን ላይ በሚከፈለው ህጋዊ ታሪፍ መሠረት እስከምሽቱ 4:00 አገልግሎት እንዲሰጡ ማሳሰቢያ ተላልፏል።
ቢሮው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቃሚዎች እስከምሽት 4:00 አገልግሎት እንዲያገኙና እና የትራንስፖርት ቁጥጥር ሠራተኞች እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ ለተግባራዊነቱ ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርቧል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ቢሮው አገልግሎት ሰጪዎች እስከ ምሽት 4:00 አገልግሎት ባይሰጡስ ምን እንደሚጠብቃቸው በዝርዝር ያለው ነገር የለም።
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ አካላት እስከምሽቱ 4:00 የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡ የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ ወስኗል።
በዚህ ውሳኔ መሠረት ማንኛውም የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ፦
- አውቶቡሶች፣
- ሚዲ ባስ
- ሚኒ ባሶች በመደበኛ ቀን በሚትሰሩበት መስመር እና ቀን ላይ በሚከፈለው ህጋዊ ታሪፍ መሠረት እስከምሽቱ 4:00 አገልግሎት እንዲሰጡ ማሳሰቢያ ተላልፏል።
ቢሮው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቃሚዎች እስከምሽት 4:00 አገልግሎት እንዲያገኙና እና የትራንስፖርት ቁጥጥር ሠራተኞች እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ ለተግባራዊነቱ ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርቧል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ቢሮው አገልግሎት ሰጪዎች እስከ ምሽት 4:00 አገልግሎት ባይሰጡስ ምን እንደሚጠብቃቸው በዝርዝር ያለው ነገር የለም።
@tikvahethiopia
" የተሠረቀባችሁን ዕቃ በአካል ቀርባቹ በመለየት መረከብ ትችላላችሁ " - ፖሊስ
በልደታ ክ/ከተማ በተደረገ የሌባ ጥናት የተለያዩ የተሠረቁ የመኪና ዕቃዎችን ከአንድ ተጠርጣሪ ጋር መያዙን በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የልደታ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።
" የሌባ ተቀባዬች ከተለያዩ አካባቢዎች የተሰረቁ የመኪና ዕቃዎችን በማከማቸት ዕቃዎቹን ለማስመለስ ከፍተኛ ገንዘብ የሚጠየቅባቸው ሁኔታዎች እንዳሉ ተደጋግሞ ይገለፃል " ያለው ፖሊስ የተሰረቁ የተሽከርካሪ ዕቃዎችን በመኖሪያ ቤት ውስጥ በመደበቅና የተሽከርካሪዎቹ ባለቤቶች ሲመጡ የራሳቸውን ዕቃ በገንዘብ የሚሸጡ ግለሰቦች ላይ ጥናት ሲደረግ መቆየቱን አመልክቷል።
ታህሳስ 17 ቀን 2017 ዓ/ም በልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 7 ቀጠና አራት አካባቢ በጥናት በተለዩ አራት የመኖሪያ ቤቶች ውስጥ ከሌቦች እየተቀበሉ በመደበቅ የሚሸጡ ግለሰቦችን ላይ በተደረገ ኦፕሬሽን ፦
👉 152 የተለያዩ ስፖኬዎች፣
👉 08 ዓርማዎች ( ማርክ )፣
👉 08 የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጀር ክዳኖች፣
👉 01 የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጀር፣
👉 15 የስፖኪዮ ማቀፊያ፣
👉 01 የሞተር ሳይክል ፍሬቻ ከአንድ ተጠርጣሪ ጋር በቁጥጥር ስር መዋሉን ፖሊስ ገልጿል።
ፖሊስ አሁንም መሰል የወንጀል ድርጊት ውስጥ በመግባት የተጠረጠሩ ግለሰቦችን ተገቢውን የፍርድ ቤት የመያዣና የመበርበሪያ ትዕዛዝ በማውጣት ተጠርጣሪዎችን የመያዝና ብርበራዎችን የማድረግ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።
" ተመሳሳይ ወንጀል ተፈጽሞብኛል " የሚል ካለ ጎማ ቁጠባ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ በአካል በመቅረብ የተሠረቀበትን ዕቃ መለየትና መረከብ እንደሚችል ፖሊስ አስታውቋል።
በነገራችን ላይ ...
አዲስ አበባ ውስጥ የትም ቦታ የራሳችሁን የመኪና ዕቃ ብትሰረቁ ዕቃችሁን የት እንደሚገባ ይታወቃል።
የተሰረቁ ሰዎች ዕቃቸውን ፍለጋ ወደ እነዚህ ስፍራዎች ሲሄዱ ሌቦቹ እና ተቀባዮቹ ልክ እንደ ህጋዊ የራሳቸው እቃ ከፍተኛ ብር ይጠይቃሉ።
የራሳችሁ በሆነና በተሰረቃችሁት ዕቃ ላይ ይደራደራሉ " አያዋጣኝም ከቦታው አልመጣም " ይላሉ።
ከዛም በፈለጉት ዋጋ የራሳችሁን ዕቃ ሽጠውላችሁ ይሸኟችኃል።
ይህ ብቻ አይደለም የጠፋባችሁን የመኪና ዕቃ ፍለጋ ባሄዳችሁት " ቆዩ አንድ 40 ደቂቃ ጠብቁ " ትባሉና ተመሳሳዩ ይመጣላችኋል። ይህን የሚያደርጉት ሌቦችን አሰማርተው በማሰረቅ ነው።
ይህ ሁሉ የሚሆንባቸው የአዲስ አበባ ቦታዎች በግልጽ በይፋ ይታወቃሉ።
የተሰረቁ ሰዎች " ለፖሊስ አመልክተን እቃችንን የምናገኝበት እድል ጠባብ ነው ፤ የሚወስደው ጊዜም ብዙ ነው " በሚል የራሳቸውን እቃ በውድ ዋጋ ይገዛሉ።
የሚሰረቁ የመኪና እቃዎች የት እንደሚወስዱ እየታወቀ ፤ የሚሸጥባቸው እና ድርድር የሚደረግባቸው ቦታዎች በይፋ እየታወቀ ይህንን ተግባር ለምን በዘላቂነት ማስቆም እንዳልተቻለ የብዙ ሰዎች ጥያቄ ነው።
ማልባትም በዚህ ነገር እጃቸው የረዘመ እና የጥቅሙ ተካፋይ ፣ የሌቦችም ጠበቃ የሆኑ ብዙ ግለሰቦች ይኖራሉ።
በመኪና ስርቆት የተማረሩ በኃላም የራሳቸውን እቃ ሄደው በከፍተኛ ብር የገዙ ብዙ ሰዎች ይኖራሉ። እናተስ የምታውቁት ታሪክ ይኖር ይሆን ? አጋሩን @tikvahethiopiaBot
@tikvahethiopia
በልደታ ክ/ከተማ በተደረገ የሌባ ጥናት የተለያዩ የተሠረቁ የመኪና ዕቃዎችን ከአንድ ተጠርጣሪ ጋር መያዙን በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የልደታ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።
" የሌባ ተቀባዬች ከተለያዩ አካባቢዎች የተሰረቁ የመኪና ዕቃዎችን በማከማቸት ዕቃዎቹን ለማስመለስ ከፍተኛ ገንዘብ የሚጠየቅባቸው ሁኔታዎች እንዳሉ ተደጋግሞ ይገለፃል " ያለው ፖሊስ የተሰረቁ የተሽከርካሪ ዕቃዎችን በመኖሪያ ቤት ውስጥ በመደበቅና የተሽከርካሪዎቹ ባለቤቶች ሲመጡ የራሳቸውን ዕቃ በገንዘብ የሚሸጡ ግለሰቦች ላይ ጥናት ሲደረግ መቆየቱን አመልክቷል።
ታህሳስ 17 ቀን 2017 ዓ/ም በልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 7 ቀጠና አራት አካባቢ በጥናት በተለዩ አራት የመኖሪያ ቤቶች ውስጥ ከሌቦች እየተቀበሉ በመደበቅ የሚሸጡ ግለሰቦችን ላይ በተደረገ ኦፕሬሽን ፦
👉 152 የተለያዩ ስፖኬዎች፣
👉 08 ዓርማዎች ( ማርክ )፣
👉 08 የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጀር ክዳኖች፣
👉 01 የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጀር፣
👉 15 የስፖኪዮ ማቀፊያ፣
👉 01 የሞተር ሳይክል ፍሬቻ ከአንድ ተጠርጣሪ ጋር በቁጥጥር ስር መዋሉን ፖሊስ ገልጿል።
ፖሊስ አሁንም መሰል የወንጀል ድርጊት ውስጥ በመግባት የተጠረጠሩ ግለሰቦችን ተገቢውን የፍርድ ቤት የመያዣና የመበርበሪያ ትዕዛዝ በማውጣት ተጠርጣሪዎችን የመያዝና ብርበራዎችን የማድረግ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።
" ተመሳሳይ ወንጀል ተፈጽሞብኛል " የሚል ካለ ጎማ ቁጠባ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ በአካል በመቅረብ የተሠረቀበትን ዕቃ መለየትና መረከብ እንደሚችል ፖሊስ አስታውቋል።
በነገራችን ላይ ...
አዲስ አበባ ውስጥ የትም ቦታ የራሳችሁን የመኪና ዕቃ ብትሰረቁ ዕቃችሁን የት እንደሚገባ ይታወቃል።
የተሰረቁ ሰዎች ዕቃቸውን ፍለጋ ወደ እነዚህ ስፍራዎች ሲሄዱ ሌቦቹ እና ተቀባዮቹ ልክ እንደ ህጋዊ የራሳቸው እቃ ከፍተኛ ብር ይጠይቃሉ።
የራሳችሁ በሆነና በተሰረቃችሁት ዕቃ ላይ ይደራደራሉ " አያዋጣኝም ከቦታው አልመጣም " ይላሉ።
ከዛም በፈለጉት ዋጋ የራሳችሁን ዕቃ ሽጠውላችሁ ይሸኟችኃል።
ይህ ብቻ አይደለም የጠፋባችሁን የመኪና ዕቃ ፍለጋ ባሄዳችሁት " ቆዩ አንድ 40 ደቂቃ ጠብቁ " ትባሉና ተመሳሳዩ ይመጣላችኋል። ይህን የሚያደርጉት ሌቦችን አሰማርተው በማሰረቅ ነው።
ይህ ሁሉ የሚሆንባቸው የአዲስ አበባ ቦታዎች በግልጽ በይፋ ይታወቃሉ።
የተሰረቁ ሰዎች " ለፖሊስ አመልክተን እቃችንን የምናገኝበት እድል ጠባብ ነው ፤ የሚወስደው ጊዜም ብዙ ነው " በሚል የራሳቸውን እቃ በውድ ዋጋ ይገዛሉ።
የሚሰረቁ የመኪና እቃዎች የት እንደሚወስዱ እየታወቀ ፤ የሚሸጥባቸው እና ድርድር የሚደረግባቸው ቦታዎች በይፋ እየታወቀ ይህንን ተግባር ለምን በዘላቂነት ማስቆም እንዳልተቻለ የብዙ ሰዎች ጥያቄ ነው።
ማልባትም በዚህ ነገር እጃቸው የረዘመ እና የጥቅሙ ተካፋይ ፣ የሌቦችም ጠበቃ የሆኑ ብዙ ግለሰቦች ይኖራሉ።
በመኪና ስርቆት የተማረሩ በኃላም የራሳቸውን እቃ ሄደው በከፍተኛ ብር የገዙ ብዙ ሰዎች ይኖራሉ። እናተስ የምታውቁት ታሪክ ይኖር ይሆን ? አጋሩን @tikvahethiopiaBot
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን በድጋሚ የሚፈተኑ ተፈታኞች በበየነ መረብ (ኦንላይን) መመዝገብ እንደሚችሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
ተፈታኞች በራሳቸው የሚመዘገቡበት አድራሻ https://register.eaes.et/Online እንደሆነ ተገልጿል።
ይህ የበይነ መረብ (አንላይን) ምዝገባ መተግበሪያ ራስ አገዝ (self services ) ሲሆን ተመዝጋቢዎች የሚፈልጉትን ድጋፍ በመጠየቅ ከማዕከል ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።
(እንዴት መመዝገብ እንደሚቻል ከላይ ይመልከቱ)
(የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት)
@tikvahethiopia
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን በድጋሚ የሚፈተኑ ተፈታኞች በበየነ መረብ (ኦንላይን) መመዝገብ እንደሚችሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
ተፈታኞች በራሳቸው የሚመዘገቡበት አድራሻ https://register.eaes.et/Online እንደሆነ ተገልጿል።
ይህ የበይነ መረብ (አንላይን) ምዝገባ መተግበሪያ ራስ አገዝ (self services ) ሲሆን ተመዝጋቢዎች የሚፈልጉትን ድጋፍ በመጠየቅ ከማዕከል ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።
(እንዴት መመዝገብ እንደሚቻል ከላይ ይመልከቱ)
(የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት)
@tikvahethiopia
#ethiotelecom #telebirr
✨🏑 ሁላችንም የምንሳተፍበት የዘንድሮ የገና ጨዋታ የሚደረግበት ሜዳ ቴሌብር ሱፐርአፕ ነው!! 😁
💁♂️ መተግበሪያው https://onelink.to/uecbbr ከሌለዎት ያውርዱ፤ በሞቀው የገና ጨዋታ ተሳታፊ ይሁኑ!
🤩 ከ15 ሚሊየኑ የዕድልዎን ለመውሰድ ታኅሣሥ 23 ይጠብቁን!!
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
✨🏑 ሁላችንም የምንሳተፍበት የዘንድሮ የገና ጨዋታ የሚደረግበት ሜዳ ቴሌብር ሱፐርአፕ ነው!! 😁
💁♂️ መተግበሪያው https://onelink.to/uecbbr ከሌለዎት ያውርዱ፤ በሞቀው የገና ጨዋታ ተሳታፊ ይሁኑ!
🤩 ከ15 ሚሊየኑ የዕድልዎን ለመውሰድ ታኅሣሥ 23 ይጠብቁን!!
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia