#ምርጫ2013
• ምርጫ ካርድ የጠፋባቸው መምረጥ ይችላሉ ?
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ካርድ የጠፋባቸው ዜጎች ድምፅ የሚሰጡበት አሰራር እንዳለ ገልጿል።
የቦርዱ የኮሚኒኬሽን ኃላፊ ወይዘሪት ሶሊያና ሽመልስ ዛሬ ለቲክቫህ አባላት ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ እና ማብራሪያ ተመዝግበው ምርጫ ካርድ ወስደው ነገር ግን ካርዱ የጠፋባቸው ዜጎች ምርጫ የሚመርጡበት መንገድ እንዳለ አስረድተዋል።
ሂደቱም እንደሚከተለው ነው ፦
- መራጮች የተመዘገቡበትን መታወቂያ ይዘው ይሄዳሉ፣
- ካርዳቸው እንደጠፋባቸው ያሳውቃሉ፣
- ስማቸው በመዝገብ ላይ ይፈለጋል በተመዘገቡበት መታወቂያ ላይ ባለው መሰረት በትክክል መዝገቡ ላይ ከተገኙ በቃለ ጉባኤ "ካርድ ጠፍቶባቸዋል እና ድምፃቸውን ይስጡ" ተብሎ ተይዞላቸው ድምፃቸውን ይሰጣሉ።
• በስራ ምክንያት ቀድሞ ከተመዘገቡበት ቦታ የተንቀሳቀሱ መራጮች ከተመዘገቡበት ምርጫ ጣቢያ ውጭ መምረጥ ይችላሉ ?
ወ/ሪት ሶሊያና ለዚህ ጥያቄ የሰጡት " #አይችሉም " የሚል አጭር ምላሽ ነው።
ምርጫው የሚካሄደው መራጮች በተመዘገቡበት የምርጫ ጣቢያ ላይ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል።
መራጮች ድምፃቸውን ለመስጠት በተቻላቸው አቅም በዕለቱ በተመዘገቡበት እና በሚኖሩበት አካባቢ ሊሆኑ ይገባል፤ ከዚህ ውጭ ግን ድምፃቸውን የሚሰጡበትም ምንም አይነት መንገድ እንደሌለ ገልፀዋል።
ወ/ሪት ሶሊያና ፥ "... አንዱ ጣቢያ ተመዝግቦ ፤ ሌላ ጣቢያ ላይ ድምፅ መስጠት አይቻልም፤ ይህ ሁኔታ በኃላ ውጤት ለመደመር አስቸጋሪ ያደርገዋል። ከዚህ በተጨማሪ አሰራሩ ዲጂታል ስላልሆነና የሚሰራው በወረቀት ስለሆነ ካርዱ ና መዝገቡ ተመሳክሮ ነው ድምፅ የሚሰጠው ስለዚህ ካርድ እና መዝገባቸው የተለያይ ሁለት ቦታ ስላሚሆን አይሆንም (ድምፅ መስጠት አይችሉም)" ብለዋል።
@tikvahethiopia
• ምርጫ ካርድ የጠፋባቸው መምረጥ ይችላሉ ?
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ካርድ የጠፋባቸው ዜጎች ድምፅ የሚሰጡበት አሰራር እንዳለ ገልጿል።
የቦርዱ የኮሚኒኬሽን ኃላፊ ወይዘሪት ሶሊያና ሽመልስ ዛሬ ለቲክቫህ አባላት ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ እና ማብራሪያ ተመዝግበው ምርጫ ካርድ ወስደው ነገር ግን ካርዱ የጠፋባቸው ዜጎች ምርጫ የሚመርጡበት መንገድ እንዳለ አስረድተዋል።
ሂደቱም እንደሚከተለው ነው ፦
- መራጮች የተመዘገቡበትን መታወቂያ ይዘው ይሄዳሉ፣
- ካርዳቸው እንደጠፋባቸው ያሳውቃሉ፣
- ስማቸው በመዝገብ ላይ ይፈለጋል በተመዘገቡበት መታወቂያ ላይ ባለው መሰረት በትክክል መዝገቡ ላይ ከተገኙ በቃለ ጉባኤ "ካርድ ጠፍቶባቸዋል እና ድምፃቸውን ይስጡ" ተብሎ ተይዞላቸው ድምፃቸውን ይሰጣሉ።
• በስራ ምክንያት ቀድሞ ከተመዘገቡበት ቦታ የተንቀሳቀሱ መራጮች ከተመዘገቡበት ምርጫ ጣቢያ ውጭ መምረጥ ይችላሉ ?
ወ/ሪት ሶሊያና ለዚህ ጥያቄ የሰጡት " #አይችሉም " የሚል አጭር ምላሽ ነው።
ምርጫው የሚካሄደው መራጮች በተመዘገቡበት የምርጫ ጣቢያ ላይ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል።
መራጮች ድምፃቸውን ለመስጠት በተቻላቸው አቅም በዕለቱ በተመዘገቡበት እና በሚኖሩበት አካባቢ ሊሆኑ ይገባል፤ ከዚህ ውጭ ግን ድምፃቸውን የሚሰጡበትም ምንም አይነት መንገድ እንደሌለ ገልፀዋል።
ወ/ሪት ሶሊያና ፥ "... አንዱ ጣቢያ ተመዝግቦ ፤ ሌላ ጣቢያ ላይ ድምፅ መስጠት አይቻልም፤ ይህ ሁኔታ በኃላ ውጤት ለመደመር አስቸጋሪ ያደርገዋል። ከዚህ በተጨማሪ አሰራሩ ዲጂታል ስላልሆነና የሚሰራው በወረቀት ስለሆነ ካርዱ ና መዝገቡ ተመሳክሮ ነው ድምፅ የሚሰጠው ስለዚህ ካርድ እና መዝገባቸው የተለያይ ሁለት ቦታ ስላሚሆን አይሆንም (ድምፅ መስጠት አይችሉም)" ብለዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1320/2016 @tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ
የኢዴፌሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ የመንግሥት ተቆጣጣሪ አካል በሚወስነው መሠረት በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ እንዲተገበር የሚያደርግ አዋጅ አፅድቋል።
አዋጁ የቤት አከራይ ከ2 ወር የቤቱ ኪራይ በላይ ቅድመ ክፍያ መጠየቅ እንደማይችልም ያስገድዳል።
አዋጁ ምን ይላል ?
➡ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋን የተመለከተው የአዋጁ አንቀጽ የመኖሪያ ቤት አከራዮች በዘፈቀድ የኪራይ ዋጋ እንዳይጨምሩ ይከለክላል።
➡ አከራይ የኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ የሚችለው ተቆጣጣሪው አካል በዓመት አንድ ጊዜ ነባራዊ የኢኮኖሚውን ሁኔታ እና ሌሎች አግባብነት ያላቸውን ጉዳዮች ከግምት በማስገባት ሊወስን የሚችለውን የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ መሠረት በማድረግ ነው።
➡ በአዋጁ መሠረት የሚደረገው የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ፤ በተቆጣጣሪው አካል በሰኔ አንድ ለሕዝብ ይፋ ተደርጎ ከሰኔ 30 ጀምሮ ለአንድ አመት የፀና ይሆናል።
➡ የቤት ኪራይ ውል ዘመን ሳይጠናቀቅ ተከራይን ከቤት ማስወጣት ወይም በዚህ አዋጅ ከተፈቀደው ሁኔታ ውጪ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ አይቻልም። ይህም አስገዳጅ ድንጋጌ ነው።
➡ አከራዮች ከሁለት ወር የቤቱ ኪራይ በላይ ቅድመ ክፍያ መጠየቅ #አይችሉም።
➡ የቤት ኪራይ ክፍያዎች በባንክ ወይም በሌላ ሕጋዊ የኤሌክትሮኒክ ዘዴ መፈፀም አለባቸው። አከራይ እና ተከራይ የቤት ኪራይ ክፍያ ሰነዶችን አደራጅተው የመያዝ ግዴታ አለባቸው።
➡ ማንኛውም የቤት ኪራይ ውል በጽሁፍ የሚደረግ ሆኖ በተቆጣጣሪው አካል መረጋገጥ እና መመዝገብ አለበት። ሁለቱም ወገኖች የቤት ኪራይ ውሉ በተፈረመ ሰላሳ ቀናት ውስጥ ውሉን አቅርበው እንዲረጋገጥ እና እንዲመዘገብ የማድረግ ግዴታ አለባቸው። ያልተረጋገጠ እና ያልተመዘገበ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል እንዳልተደረገ ይቆጠራል። አዋጁን ተከትሎ የሚደረግ መኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ከሁለት ዓመት ሊያንስ አይችልም።
NB. በአዋጁ መሠረት ተቆጣጣሪ አካል ማለት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውልን እና ዋጋን እንዲቆጣጠር በክልሎች ወይም በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የሚሰየም አካል ነው፡፡ #HoPR #ቢቢሲ
@tikvahethiopia
የኢዴፌሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ የመንግሥት ተቆጣጣሪ አካል በሚወስነው መሠረት በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ እንዲተገበር የሚያደርግ አዋጅ አፅድቋል።
አዋጁ የቤት አከራይ ከ2 ወር የቤቱ ኪራይ በላይ ቅድመ ክፍያ መጠየቅ እንደማይችልም ያስገድዳል።
አዋጁ ምን ይላል ?
➡ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋን የተመለከተው የአዋጁ አንቀጽ የመኖሪያ ቤት አከራዮች በዘፈቀድ የኪራይ ዋጋ እንዳይጨምሩ ይከለክላል።
➡ አከራይ የኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ የሚችለው ተቆጣጣሪው አካል በዓመት አንድ ጊዜ ነባራዊ የኢኮኖሚውን ሁኔታ እና ሌሎች አግባብነት ያላቸውን ጉዳዮች ከግምት በማስገባት ሊወስን የሚችለውን የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ መሠረት በማድረግ ነው።
➡ በአዋጁ መሠረት የሚደረገው የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ፤ በተቆጣጣሪው አካል በሰኔ አንድ ለሕዝብ ይፋ ተደርጎ ከሰኔ 30 ጀምሮ ለአንድ አመት የፀና ይሆናል።
➡ የቤት ኪራይ ውል ዘመን ሳይጠናቀቅ ተከራይን ከቤት ማስወጣት ወይም በዚህ አዋጅ ከተፈቀደው ሁኔታ ውጪ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ አይቻልም። ይህም አስገዳጅ ድንጋጌ ነው።
➡ አከራዮች ከሁለት ወር የቤቱ ኪራይ በላይ ቅድመ ክፍያ መጠየቅ #አይችሉም።
➡ የቤት ኪራይ ክፍያዎች በባንክ ወይም በሌላ ሕጋዊ የኤሌክትሮኒክ ዘዴ መፈፀም አለባቸው። አከራይ እና ተከራይ የቤት ኪራይ ክፍያ ሰነዶችን አደራጅተው የመያዝ ግዴታ አለባቸው።
➡ ማንኛውም የቤት ኪራይ ውል በጽሁፍ የሚደረግ ሆኖ በተቆጣጣሪው አካል መረጋገጥ እና መመዝገብ አለበት። ሁለቱም ወገኖች የቤት ኪራይ ውሉ በተፈረመ ሰላሳ ቀናት ውስጥ ውሉን አቅርበው እንዲረጋገጥ እና እንዲመዘገብ የማድረግ ግዴታ አለባቸው። ያልተረጋገጠ እና ያልተመዘገበ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል እንዳልተደረገ ይቆጠራል። አዋጁን ተከትሎ የሚደረግ መኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ከሁለት ዓመት ሊያንስ አይችልም።
NB. በአዋጁ መሠረት ተቆጣጣሪ አካል ማለት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውልን እና ዋጋን እንዲቆጣጠር በክልሎች ወይም በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የሚሰየም አካል ነው፡፡ #HoPR #ቢቢሲ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba በአዲስ አበባ ከተማ የአከራይ እና ተከራይ ህጋዊ ውል ምዝገባ ሰኔ 1 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚጀመር የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል። የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ መጽደቁ ይታወቃል፡፡ በዚህም አስተዳደሩ አዋጁን በመመሪያ በማስደገፍ ወደ ስራ ለማስገባት ዝግጅቶቹን ማጠናቀቁ ተገልጿል። ከሰኔ 1 እስከ 30 ቀን 2016 ዓ.ም በከተማዋ ውስጥ የሚገኙ…
#ማስታወሻ
" የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1320/2016 " ምን ይዟል ?
➡ የመኖሪያ ቤት አከራዮች #በዘፈቀድ የኪራይ ዋጋ መጨመር #አይችሉም።
➡ አከራይ የኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ የሚችለው ተቆጣጣሪ አካል #በዓመት_አንድ_ጊዜ ነባራዊ የኢኮኖሚውን ሁኔታ እና ሌሎች አግባብነት ያላቸውን ጉዳዮች ከግምት በማስገባት ሊወስን የሚችለውን የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ መሠረት በማድረግ ነው።
➡ ማንኛውም የቤት ኪራይ ጭማሪ በተቆጣጣሪው አካል በሰኔ 1 ለሕዝብ ይፋ ተደርጎ ከሰኔ 30 ጀምሮ ለአንድ አመት የፀና ይሆናል።
➡ የቤት ኪራይ ውል ዘመን #ሳይጠናቀቅ ተከራይን ከቤት ማስወጣት ወይም በዚህ አዋጅ ከተፈቀደው ሁኔታ ውጪ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ አይቻልም። ይህም አስገዳጅ ድንጋጌ ነው።
➡ አከራዮች #ከ2_ወር_የቤቱ_ኪራይ_በላይ ቅድመ ክፍያ መጠየቅ #አይችሉም።
➡ የቤት ኪራይ ክፍያዎች በባንክ ወይም በሌላ ሕጋዊ የኤሌክትሮኒክ ዘዴ መፈፀም አለባቸው። አከራይ እና ተከራይ የቤት ኪራይ ክፍያ ሰነዶችን አደራጅተው #የመያዝ_ግዴታ አለባቸው።
➡ ማንኛውም የቤት ኪራይ ውል በጽሁፍ የሚደረግ ሆኖ በተቆጣጣሪው አካል መረጋገጥ እና መመዝገብ አለበት።
➡️ መኖሪያ ቤት ኪራይ ውል #ከሁለት_ዓመት ሊያንስ አይችልም።
NB. በአዋጁ መሠረት " ተቆጣጣሪው አካል ፣ ማለት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውልን እና ዋጋን እንዲቆጣጠር በክልሎች ወይም በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የሚሰየም አካል ነው፡፡
More : https://t.iss.one/tikvahethiopia/86580?single
#Ethiopia
#የመኖሪያ_ቤት_ኪራይ_ቁጥጥርና_አስተዳደር_አዋጅ
@tikvahethiopia
" የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1320/2016 " ምን ይዟል ?
➡ የመኖሪያ ቤት አከራዮች #በዘፈቀድ የኪራይ ዋጋ መጨመር #አይችሉም።
➡ አከራይ የኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ የሚችለው ተቆጣጣሪ አካል #በዓመት_አንድ_ጊዜ ነባራዊ የኢኮኖሚውን ሁኔታ እና ሌሎች አግባብነት ያላቸውን ጉዳዮች ከግምት በማስገባት ሊወስን የሚችለውን የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ መሠረት በማድረግ ነው።
➡ ማንኛውም የቤት ኪራይ ጭማሪ በተቆጣጣሪው አካል በሰኔ 1 ለሕዝብ ይፋ ተደርጎ ከሰኔ 30 ጀምሮ ለአንድ አመት የፀና ይሆናል።
➡ የቤት ኪራይ ውል ዘመን #ሳይጠናቀቅ ተከራይን ከቤት ማስወጣት ወይም በዚህ አዋጅ ከተፈቀደው ሁኔታ ውጪ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ አይቻልም። ይህም አስገዳጅ ድንጋጌ ነው።
➡ አከራዮች #ከ2_ወር_የቤቱ_ኪራይ_በላይ ቅድመ ክፍያ መጠየቅ #አይችሉም።
➡ የቤት ኪራይ ክፍያዎች በባንክ ወይም በሌላ ሕጋዊ የኤሌክትሮኒክ ዘዴ መፈፀም አለባቸው። አከራይ እና ተከራይ የቤት ኪራይ ክፍያ ሰነዶችን አደራጅተው #የመያዝ_ግዴታ አለባቸው።
➡ ማንኛውም የቤት ኪራይ ውል በጽሁፍ የሚደረግ ሆኖ በተቆጣጣሪው አካል መረጋገጥ እና መመዝገብ አለበት።
➡️ መኖሪያ ቤት ኪራይ ውል #ከሁለት_ዓመት ሊያንስ አይችልም።
NB. በአዋጁ መሠረት " ተቆጣጣሪው አካል ፣ ማለት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውልን እና ዋጋን እንዲቆጣጠር በክልሎች ወይም በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የሚሰየም አካል ነው፡፡
More : https://t.iss.one/tikvahethiopia/86580?single
#Ethiopia
#የመኖሪያ_ቤት_ኪራይ_ቁጥጥርና_አስተዳደር_አዋጅ
@tikvahethiopia