TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
🌼 እንቁጣጣሽ የአዲስ ዓመት የንግድ ትርኢትና ባዛር በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ !

በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ የዐውደ ዓመት ገበያ ደርቷል፤ ለአዲስ ዓመት የሚያስፈልግዎትን ለመሸመት ጎራ ይበሉ!

በቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ወይም *127# የመግቢያ ትኬት ሲገዙ እንዲሁም ሲገበዩ እስከ 2500 ብር ድረስ ላለው 10% ተመላሽ ያገኛሉ።

🗓 እስከ ጳጉሜ 05/2016 ዓ.ም ይቆያል

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #SmartAfrica #RealizingDigitalEthiopia
#MesiratEthiopia

💼 ቢዝነሱን ማሳደግ ለሚፈልግ ⬇️
- በፋይናንስ፣
- በማርኬቲንግ፣
- ችሎታን በማዳበር፣
- በቴክኖሎጂ፣
- በኔትወርኪንግ፣
- የባለሙያ አማካሪዎችን በማግኘት፣
- በፖሊሲ፣
- በአገልግሎት ሰጪነት እና
- በአማካሪነት ድጋፍ ለማግኘት https://mesirat.acceleratorapp.co/application/new ላይ ተመዝገቡ።

የመስራት ስራ ፈጠራ ፕሮግራም አባል ይሁኑና ቢዝነስዎ እንዲያድግ አጠቃላይ ድጋፍን ያግኙ።

ሴቶች እና አካል ጉዳተኞች እንዲመዘገቡ ይበረታታሉ!
TIKVAH-ETHIOPIA
#Alert🚨 ኦሞ ወንዝ በከፍተኛ ሁኔታ በመሙላቱ የወንዙ ውሃ እና የቱርካና ሀይቅ ይዞታውን እያሰፋ በመሆኑ በኦሞራቴ ከተማ በ1.9 ኪ/ሜ ርቀት አከባቢ በተለያዩ ቦታዎች የመሬት መሰንጠቅ እዲሁም ውሃው ውስጥ ለውስጥ እየሄደ በመሆኑ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር ጥሪ አቅርቧል። @tikvahethiopia
#ትኩረት🚨

ኦሞራቴ ዙሪያ 500 ሜትር እርዝመትና ሁለት ሜትር ጥልቀት ያለዉ የመሬት መሰንጠቅ ተከስቷል።

የከተማዉ ነዋሪዎች " የመሬት መሰንጠቁ ውሀዉ መድረሱን ያሳያልና ድረሱልን " እያሉ ነው።

ከሰሞኑን የኦሞ ወንዝ መሙላቱን ተከትሎ በርካታ አርብቶ አደሮች መፈናቀላቸውንና አካባቢው በውሀው ከመጥለቅለቁ ባለፈ የወረዳው ዋና ከተማ ኦሞራቴ መቅረቡ የከተማውን ማህበረሰብ ስጋት ውስጥ እንዳስገባው ነግረናችሁ ነበር።

አሁን ደግሞ የተፈጠረዉ የመሬት መሰንጠቅ ሌላ የድንጋጤ ምክኒያት ሆኗል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች " ውሀው ከመቅረቡ ባለፈ በአካባቢው የመሬት መሰንጠቅ መፈጠሩ በነዋሪው ላይ ከፍተኛ ድንጋጤ ፈጥሯል " ብለዋል።

ውሀው ወደ ከተማው መጠጋቱን ለመከላከል እና አቅጣጫውን ለማስቀየር በሰው ሀይል ጥረት ቢደረግም ውሀው ውስጥ ለውስጥ መጠጋቱን የፈጠረዉ የመሬት መሰንጠቅ ይጠቁማል ብለዋል።

በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸዉን የሰጡን የወረዳዉ አስተዳዳሪ አሁን ላይ ህዝቡን ያሰጋዉ አምስት መቶ ሜትር ርዝመትና ሁለት ሜትር ጥልቀት ያለው የመሬት መሰንጠቅ በመፈጠሩ ነው ብለዋል።

አንድ ዶዘር መድረሱንና ስካቫተር እየመጣ መሆኑን ጠቁመው ይህም የውሀዉን አቅጣጫ ለመቀየርና ለማፍሰስ ይረዳል በማለት ይህም እየተከሰተ ያለውን የመሬት መሰንጠቅ አስቁሞ ማህበረሰቡን ያረጋጋል ብለዋል።

አሁን ላይ ምንም እንኳን ዶዘር መድረሱና ስካቫተር እየመጣ መሆኑ ተስፋ ቢሰጠንም የነዳጅ የሰዉ ሀይልና አጠቃላይ ኦፕሬሽን ኮስት ስለሚያስፈልገን የክልሉና የፌደራሉ መንግስት ሊያግዘን ይገባል ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
#USA

አሜሪካ በአስገድዶ መድፈር ጥፋተኛ የተባለን ወንጀለኛ በመርዝ ገደለች፡፡

አሜሪካ በአስገድዶ ደፋሪዎች ላይ ከባድ ቅጣት ከሚያስተላልፉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት፡፡

ሎራን ኮል የተባለው አሜሪካዊ የ57 ዓመት እድሜ ያለው ሲሆን በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ተከሶ በፍርድ ቤት ጥፋተኛ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

ይህ ወንጀለኛ የሞት ፍርድ የተላለፈበት ሲሆን በዛሬው ዕለት ታስሮ በነበረበት ፍሎሪዳ ማረሚያ ቤት ገዳይ መርዝ በመርፌ ከተወጋ በኋላ ህይወቱ አልፏል።

ግለሰቡ የገዛ እህቱን በመድፈር ወንጀል ከተመሰረተበት ክስ በተጨማሪም የፍሎሪዳ ዩንቨርሲቲ የሆነ የ18 ዓመት ወጣት ግድያም ተከሶ ጥፋተኛ ተብሏል፡፡

አሜሪካ የተያዘው 2024 ዓመት ከገባ ጊዜ ጀምሮ 13 ሰዎች ላይ የሞት ፍርድ የፈጸመች ሲሆን ይህም ሀገሪቱ የሞት ፍርድ በብዛት ከሚፈጸምባቸው የዓለማችን ሀገራት መካከል ከፍተኛዋ አድርጓታል፡፡

አሜሪካ ካሏትግዛቶች ውስጥ 23ቱ የሞት ፍርድን የሚፈጽሙ ሲሆን ቀሪዎቹ 7 ግዛቶች ደግሞ የሞት ፍርዶችን ወደ እድሜ ልክ እስር ይቀይራሉ፡፡

እንደ ዓለም አቀፉ የስነ ህዝብ ፖፑሌሽን ሪቪው ጥናት ከሆነ በዓለም ላይ ካሉ ጠቅላላ ሴቶች መካከል 35 በመቶ ያህሉ ለጾታዊ ጥቃት የተጋለጡ ናቸው፡፡

ይሁንና ጥቃቱን ከሚፈጽሙት ውስጥ 10 በመቶዎቹ ብቻ ህግ ፊት ቀርበው ውሳኔ ሲሰጣቸው ቀሪዎቹ በብዙ ምክንያቶች ተገቢውን ፍትህ አያገኙም፡፡

ከአሜሪካ በተጨማሪም ጥብቅ ህግ ያላቸው ሀገራት ፦
- ሳውዲ አረቢያ፣
-  ቻይና፣
- ደቡብ ኮሪያ፣
- ቸክ ሪፐብሊክ፣
- ሰሜን ኮሪያ እና ፓኪስታን ዋነኞቹ ናቸው።

መረጃውን ሮይተርስን ዋቢ በማድረግ ያጋራው አል አይን ኒውስ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሪልስቴት #አዲስአበባ ° “ ብራችንን እኔ አውጥተን ተሰቃየን ” - የኖህ ሪልስቴት ቤት ገዥዎች ° “ የመብራት፣ የውሃ፣ የውሃ ታንከር ጥያቄ አለ ትክክል ነው ” - ኖህ ሪልስቴት በአዲስ አበባ ከተማ ፤ በኖህ ሪልስቴት ' የኖህ አያት ግሪን ፖርክ ቤት ' ገዢዎች ኖህ የገባውን ውል በመዘንጋት የቤት መሠረተ ልማቶችን እያሟላ እንዳልሆነ እና በጠበቃቸው በኩል ምላሽ እንዲሰጣቸው ቢጠይቁም መፍትሄ እንዳላገኙ…
#ሪልስቴት #Update

" ቤት ገብተው የሚኖሩ ሰዎች አሉ በጣም ነው የሚያሳዝኑት መብራትና ውሃ ስለሌለ እንጀራ ጋግረው አያውቁም እሱን እያየን ለመግባት ተቸግረል " - የኖህ ሪልስቴት ቤት ገዢዎች

"...ለፕሬስ መግለጫ አልሰጥም  " - ኖህ ሪልስቴት

የኖህ ሪልስቴት ሀያት ግሪን ቤት ገዢዎች ድርጅቱ በውሉ መሠረት የቤቱን መሠረተ ልማት እንዳላሟላላቸው በድጋሚ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ቅሬታ አቀረቡ፡፡

ቅሬታቸውን ያቀረቡ በርካታ ገዢዎች፣ ድርጅቱ በገባው ውል መሠረት መብራት፣ ውሃ፣ ጀነሬተር መሠረተ ልማቶች ባለሟሟላቱ ችግር ላይ እንደወደቁ ገልጸዋል።

መሠረተ ልማቱ ሳይጠናቀቅ የቤት ኪራይ ሽሽት ቤታቸው የገቡ ገዢዎች ያለ መሠረተ ልማት ከ1 ዓመት በላይ እንተቀመጡ በምሬት ተናግረዋል፡፡

መሠረተ ልማቱ እስከሚጠናቀቅ በኪራይ ቤት ሆነው እየጠበቁ ያሉ ገዢዎችም፣ ቤቱን ለመግዛት እስከ 4 ሚሊዮን ብር አውጥተው ሳለ መሠረተ ልማቱ ባለመጠናቀቁ አሁንም በቤት ኪራይ ወጪ እየተበዘበዙ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ወደ ቤታቸው ያልገቡበትን ምክንያት ሲያስረዱም፣ " ቤት ገብተው የሚኖሩ ሰዎች አሉ በጣም ነው የሚያሳዝኑት መብራትና ውሃ ስለሌለ እንጀራ ጋግረው አያውቁም እሱን እያየን ለመግባት ተቸግረል " ነው ያሉት።

ከዚህ ቀደም መሠረተ ልማቱን በወር ከ15 ቀን ውስጥ እንደሚያጠናቅቅ በሚዲያ በኩል ቃል ገብቶላቸው እንደነበር አስታውሰው፣ ግን ምንም ሳይሰራ ወራቶች እንደጠቆጠሩ ተናግረዋል።

ውሃው ግቢ ውስጥ ገብቷል ከተባለ ብዙ ጊዜ እንዳስቆጠረ፣ ነገር ግን አገልግሎት ላይ እንዳልዋለ፣ በዚህም የከፋ ችግር ለማሳለፍ እንደተገደዱ ነው የገለጹት፡፡

ድርጅቱ ይባስ ብሎ ቤቱ ሳያጠናቅቅ ጥበቃዎችን እያስወጣ መሆኑን፣ የከተማዋ ከንቲባ ሳይቱን የመረቁት ሳይጠናቀቅ መሆኑንም ተናግረዋል።

ላደረባቸው ቅሬታ ምላሽ ቢሮ ድረስ ሂደው ቢጠይቁም አጥጋቢ ምላሽ እንዳልተሰጣቸው አስረድተው፣ አሁንም መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅናቸው የኖህ የህግ አማካሪና ጠበቃ አቶ የሴፍ ደስታ፣ አጭር የመከላከያ ሀሳብ ከመስጠት ውጪ በቀጥታ ለቅሬታው ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

" በጠበቃቸው አማካኝነት እየተከታተሉ ስለሆነና ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት የመሄድ ዕድል ስላለው የድርጅቱን የመከራከር መብት የሚያጣብብ ስለሚሆን ለፕሬስ መግለጫ አልሰጥም " ነው ያሉት።

ድርጅቱ ከዚህ ቀደም ስለቅሬታው ጠይቀነው በሰጠን ምላሽ፣ " ትክክል ነው የመብራት፣ የውሃ፣ ታንከር ጥያቄ አለ " ብሎ ይህ የገጠመው በተለያዩ ችግሮች እንደሆነ ገልጾ ነበር።

በወቅቱ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤቱን መቼ አጠናቃችሁ ታስረክቧቸዋላችሁ? ስንል ጠይቀናቸው በሰጡት ምሌሽ፣ " ነገ ቢሆን ደስ ይለኛል፡፡ 654 ቤቶችን ሰርተን መብራት ለማስገባት የምንዘገይበት ምክንያት እኔ ራሱ አልገባኝም " ነበር ያሉት።

" ስለዚህ በጣም በጣም ባጠረ ጊዜ ውስጥ ለመስራት እየሞከርን ነው " ማለታቸው ይታወሳል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#ትኩረት🚨

ዛሬም ድረስ የሰው ህይወት የሚቀጠፍባቸው የመስቃን እና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች ነዋሪዎች " በፈጣሪ ስም መፍትሄ ይፈለግልን ፤ ተሰቃየን ህይወታችን በሰቀቀን መግፋት ደከመን " ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጥሪ አቅርበዋል።

" ተደጋጋሚ እርቅ ይፈጸማል ግን ሳይቆይ ያገረሽና ደም ይፈሳል፣ ሰው ይገደላል የምንገባበት አጣን ድምጻችን ይሰማ " ብለዋል።

ከሰሞኑን በመስቃን እና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች የ9 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተከትሎ የአካባቢዉ ባለስልጣናት መታሰራቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።

ባለፉት ጊዜያት የነበረዉ የንጹሀን ግድያ  ለተወሰነ ጊዜ ረገብ ቢልም ከሰሞኑ እንደገና ባገረሸ ግጭት የ9 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 4 ሰዎች ደግም ቆስለዋል።

ይህን ተከትሎ አካባቢዉ ውጥረት ዉስጥ በመግባቱ አሁን ላይ በአካባቢዉ የሚኖሩ ንጹሀን በፍርሀት ውስጥ ናቸው።

" ኢንሴኖ ከተማና አካባቢው በየጊዜው በሚነሳው ግጭት ገጠራማው ቀበሌ የሚኖረው ምስኪን ግድያ ሲፈጸምበት ቆይቷል " የሚሉት ነዋሪዎቹ " በአካባቢው ሲስተዋል የነበረዉ የበቀል መጠፋፋት አሁንም በከፋ ሁኔታ ተመልሶ ይመጣል በሚል ተጨንቀናል " ሲሉ ገልጸዋል።

ከሰሞኑ በማረቆ ልዩ ወረዳ በሌሊት በተፈጸመ ጥቃት የ7 ሰዎች ህይወት (4ቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት) እንዲሁም በመስቃን ደግሞ 2 ሰዎች ህይወታቸው መቀጠፉን የሚናገሩት ነዋሪዎቹ ሁኔታውን የመንግስት አካላት ቶሎ ካልተቆጣጠሩት ግጭቱ ከፍ ሊል ይችላል ሲሉ ፍርሀታቸውን አስረድተዋል።

ስለሁኔታዉ የጠየቅናቸዉ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ጸጥታ ኃላፊዉ አቶ ተካልኝ ንጉሴ ስለሁኔታው መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ይሁንና በልዩ ወረዳዎቹ ግድያ መፈጸሙን ተከትሎ አካባቢውን ለማረጋጋት ወደቦታው ያቀናው የጸጥታ ኃይል ጥቂት የአካባቢው ግለሰቦችን ጨምሮ ግጭት በተፈጠረባቸዉ አካባቢዎች ለጊዜዉ ስማቸዉ አይጠቀስ የተባሉ የወረዳ ከፍተኛ ባለስልጣናትን በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉን ለማወቅ ተችሏል።

አሁን ላይ ኢንሴኖን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች የፌደራልና የክልል የጸጥታ አካላት ተሰማርተው ህዝቡን እያረጋጉ ሲሆን የህዝቡ እንቅስቃሴ ግን በጅጉ መቀዛቀዝ ይስተዋልበታል።

ይህ አካባቢ በተደጋጋሚ የሰዎች ህይወት የሚቀጠፍበት ፣ ዜጎች የሚፈናቀሉበት ሲሆን ዘላቂና አስተማማኝ መፍትሄ ሳይገኘ ዛሬም በዛው ቀጥሏል።

#Update : ከመሸ ስልክ ያነሱልን የምስራቅ ጉራጌ ወንጀል መከላከል ዲቪዥን ኃላፊ ኮማንደር መሀመድ ሀሰን " አሁን ላይ ሁሉም አካባቢ ሰላም " መሆኑን ጠቅሰው ስለሁኔታው አሁን ላይ መረጃ መስጠት ከባድ መሆኑን ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
#AddisAbaba #ባጃጅ

በአዲስ አበባ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት በሂደት ሙሉ በሙሉ መቋረጡ አይቀሬ እንደሆነ ተሰምቷል።

በአዲስ አበባ ከተማ የባለሶስት እና አራት እግር ተሽከርካሪ ወይም ባጃጅ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች  የአሰራር ፣ የአጀረጃጀት፣ የአገልግሎት አሰጣጥና የዲሲፒሊን ቁጥጥር አፈጻጸም መመሪያ ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጎ ነበር።
                              
በውይይቱ ላይ ፦
- የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ
- የትራፊክ ማናጅመንት ፣
- የትራንስፖርት ቢሮ
- የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የማዕከልና የክ/ከተሞች ኃላፊዎች ተገኝተው ነበር።

በአፈፃፀም መመሪያው የባለ ሶስትና አራት እግር ተሽከርካሪ ወይም ባጃጅ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ካሁን ቀደም ሲያጋጥሙ የነበሩ የሕግ ጥሰቶችንና የደንብ መተላለፎችን ለመከላከል ሲባል አገልግሎት ሰጪዎቹ ፦

የአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪነት መታወቂያ ፣

የአዲስ አበባ የሠሌዳ ቁጥር

በማህበር መደራጀት እንደሚኖርባቸው ተገልጿል።

" በአዲስ አበባ፣ የከተማ አስተዳደሩን ታርጋ ለጥፈውና የአዲስ አበባ መታወቂያ ይዘው ከሚሰሩት ይልቅ ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ አሽከርካሪዎች መበራከት የፀጥታ ችግር ሆነው ቆይተዋል " ተብሏል።

ይህ ደግሞ በተለይ በወንጀል ድርጊት ላይ ተሳትፈው በሚገኙ አሽከርካሪዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ አዳጋች እንደነበር ተገልጿል።

በዚሁ መድረክ ላይ " የባጃጅ ትራንስፖርት የከተማዋን ዘመናዊ እሳቤ የሚመጥን ስላልሆነ በሂደት ሙሉ በሙሉ አገልግሎቱ የሚቋረጥ ይሆናል " ተብሏል።

" እስከዚያ ጊዜ ድረስ የባለሶስት እግር አሽከርካሪዎች የአዲስ አበባ መታወቂያ፣ ታርጋ እና በማህበር መደራጀት ይኖርባቸዋል " ነው የተባለው።

አሁን ላይ በተለይ በጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ ሰፊ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት ፍላጎት በመኖሩ በነዚህ አካባቢ ያለው ፍላጎት በሌላ አማራጮች እስኪተካ ድረስ አገልግሎቱ እንደሚቀጥል ተመላክቷል።

በአዲስ አበባ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ባሉባቸው እንዲሁም በውስጥ ለውስጥ ሰፈሮች ዜጎች ባለ 3 እግር ተሽከርካሪዎችን / ባጃጅ ለትራንስፖርት ይጠቀማሉ።

እጅግ በርካታ ዜጎችም በተለይ በተለይ ወጣቶች በዚሁ የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጡ ገቢ ያገኛሉ ቤተሰባቸውንም ያስተዳድራሉ።

ከዚህ ቀደም ባጃጆች በተለይ በከተማው ዳርዳር ከዋና ዋና የሚባሉ መንገዶች ወጥተው ውስጥ ለውስጥ ብቻ እንዲሰሩ መደረጉ የሚዘነጋ አይደለም።

#AddisAbaba
#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#MPESASafaricom

በM-PESA ቅናሽ እና ስጦታ እንደልብ ነዉ ፤ የሀገር ዉስጥ በረራችንን በM-PESA ስንከፍል 5% ተመላሻችን ይጠብቀናል ፤ አሁኑኑ ለሀገር ዉስጥ በረራችን በM-PESA እንክፈል 5%ተመላሽ እንቀበል ፤ መልካም ጉዞ !

የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

  #FurtherAheadTogether
#flyethiopian
@heyonlinemarket

•PlayStation 5, 73,000 Birr
•Playstaion 5 Slim, 78,000 Birr

•PlayStation 4 Slim, 37,000 Birr
•PlayStation 4 Pro, 43,000 Birr

•Playstaion portal, 25,000 Birr
•Meta Quest 2, 45,000 Birr
•Meta Quest 3, 73,000 Birr

Contact
0953964175 @heymobile

@heyonlinemarket
#ጥቆማ #ጥንቃቄ 🚨

ይህ የተንጋደደና ለመውደቅ ጫፍ የደረሰ የመንገድ መብራት ምሰሶ ወድቆ በአስፓልቱ ላይ በሚተላለፍ ተሽከርካሪ እና በሰው ላይ ጉዳት ከማድረሱ በፊት መፍትሄ ይፈለግለት።

ይነሳ አልያም በአግባቡ ይጠገን።

ቦታው አዲስ አበባ ፣ ከአትላስ ወደ ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን መሄጃ የትራፊክ መብራቱ ጋር ነው።

እንዲሁ ሊወድቅ እንዳለና እንደተንጋደደ በርካታ ቀናት የተቆጠሩ ሲሆን የሚያነሳው እና የሚያስተካክለው አልመጣም።

ከከባዱ የክረምት ወቅት ጋር ተያይዞ ወድቆ ጉዳት ሳይደርስ በፊት አስቸኳይ መፍትሄ ይሰጠው።

👉 ለአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ
👉 ትራፊክ ማኔጅመንት

#TikvahEthiopiaAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray

" በችግር ላይ ሌላ ችግር  በህዝቡ ላይ የመጫን ፍላጎት የለንም ፤ አሁን የገጠመን ፈተና እናልፈዋለን። አባቶች በፀሎትና ምክር አግዙን !! " - ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር)

የህወሓት ሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር ) ነሃሴ 24 ቀን 2016 ዓ/ም ከአበው ጳጳሳት እና የአገር ሽማግሌዎች ጋር በኣክሱም ከተማ መወያየታቸውን የሚገልጽና አንድ ንግግር ሲያደርጉ የሚታይበት ቪድዮ ተሰራጭቷል።

ቪድዮው በትግራይ ፐብሊክ ሚዲያ (TPM) የማህበራዊ ትስስር ገጽ ላይ ነው የተሰራጨው።

ሊቀመንበሩ የ5 ደቂቃ ርዝማኔ ባለው ንግግራቸው  ፥ " እኔ ለድርጅትና ለህዝብ ደህንነት ስል ብዙ ታግሻለሁ ፤ ትዕግስትና ዝምታዬ ግን መልካም ነገር ሳይሆን አደጋ ነው ያስከተለው ፤ ስለሆነም ከአሁን በኋላ መታገስ ሳይሆን ተመጣጣኝ ሰላማዊ ትግል ነው የሚያዋጣው " ሲሉ ተደምጠዋል።

" እኛ የውጭ ጠላት አለብን የውስጥ ጉዳይ አናቆየው በማለታችን በውስጣችን ብዙ ችግሮች እንዲፈጠሩ ሆኗል " ያሉት ደብረፅዮን (ዶ/ር) ፥ " ከአሁን በኋላ የጎራ መደበላለቅ አይኖርም አቋማችን በግልፅ በማንፀባረቅ ሰላማዊ ትግል ማካሄዳችን እንቀጥላለን " ብለዋል።

" በሃይል ፍላጎቴን አሳካለሁ የሚል አካል ሃይ ሊባል ይገባዋል ፥ በትግራይ በጉልበት እሰራለሁ ማለት አያዋጣም " ሲሉ ገልጸዋል።

" ከአሁን በኋላ ከህዝብ የሚደበቅ ሚስጥር አይኖርም " በማለትም ተናግረዋል።

ሊቀመንበሩ ፤ " የተፈጠረውን ልዩነት በሰላም እንጨርሰው ፤ የማይሳካ ከሆነ ግን ሉአላዊነታችንን አሳልፈን አንሰጥም ፤ አቋማችን ግልፅ በማድረግ እንታገላለን " ብለዋል።

" አንድ በማያደርገን አንድ ሁኑ አትበሉን  በፓለቲካ አንድ በማያደርግህ አቋም አንድ መሆን አይቻልም ፤ ተከባብሮ በሰላም መስራት ግን ይቻላል ፤ ትግራይ ለሁሉም በቂ ናት " ሲሉም ደብረጽዮን (ዶ/ር) አክለዋል።

ህዝቡ ላይ በችግር ላይ ሌላ ችግር መጫን  እንደማይፈልጉ የተናገሩት ሊቀመንበሩ ፥ የተፈጠረው ሁኔታ ተስፋ የሚያስቆርጥ እንዳልሆነና በሰላማዊ አግባብ እንደሚፈታ በማመላከት የሃይማኖት አባቶች በፀሎትና በምክር እንዲረዱዋቸው ጠይቀዋል።

#ቲክቫህኢትዮጵያመቐለ #TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
Bethlehem Ghiday, a Jasiri fellow of the 5th cohort, says that Jasiri gave her the foundational skills needed to become entrepreneur. Through Jasiri, she was able to become the co-founder of Baobab Superfoods.

If you wish to establish your own venture like Bethlehem, Join the next cohort. Apply now!

👉🏾 https://bit.ly/3A8rxtV

For more information, Join our telegram channel 👉🏾 @Jasiri4africa