TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ት.ዲ.ት.ፓ.‼️

መንግስት የራያ ህዝብ እያቀረበ ያለውን የማንነት ጥያቄ ህገመንግስቱን ማዕከል በማድረግ #አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጥ የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር ፓርቲ ጠየቀ፡፡ የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር ኢንጅነር ግደይ ዘርዓፅዮን እንደተናገሩት፤ በትግራይና በአማራ ክልል ውስጥ ያሉ አንዳንድ የፖለቲካ አመራሮች ለግል ጥቅማቸው ሲሉ በሚነዙት የጥላቻ ፕሮፖጋንዳ ምክንያት የራያ ህዝብ የማንነት ጥያቄ ምላሽ አጥቷል፡፡

በዚህም የህዝቡ ደህንነት አደጋ ላይ የወደቀ በመሆኑ መንግስት አፋጣኝ መፍትሄ ሊሰጠው ይገባል፡፡ በህዝቡ የተነሳውን ጥያቄ ሁለቱ ክልሎች ተመካክረው ሊፈቱት ይገባ የነበረ ቢሆንም ለጉዳዩ በቂ ትኩረት ባለመስጠታቸው ምክንያት አንዱ ክልል በሌላው ላይ መንገድ እስከመዝጋት
የሚደርስ ተግባር የሚፈፀምበት ሁኔታ መኖሩን ምክትል ሊቀመንበሩ አመልክተዋል፡፡

"ፓርቲያችን በሁለቱም ክልሎች በየጎዳናው የሚደረገው ዛቻና ፉከራ ለማንም ይጠቅማል ብሎ አያምንም" ያሉት ምክትል ሊቀመንበሩ የራያ ህዝብ ጥያቄ በህገመንግስቱ መሰረት ወደ ፈዴሬሽን ምክር ቤት መጥቶ በህግ አግባብ ውሳኔ መሰጠት ይኖርበታል ብለዋል፡፡ "እኛ አሁን የምንጠይቀውና ጫና የምናደርገው የትግራይ ክልል መንግስትን ነው" ያሉት ምክትል ሊቀ መንበሩ ጉዳዩ በሌላ አካል ባይቀርብም እንኳ የክልሉ መንግስት ራሱ ለፌዴራል መንግስት ጥያቄ በማቅረብ እልባት እንዲያገኝ ማድረግ የሚጠበቅበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ምክትል ሊቀ መንበሩ የሁለቱም ክልል አመራሮች በህዝቦች መካከል ቅራኔ የሚፈጥሩ ትንኮሳዎችን በመከላከል የአገር ሰላምና ደህንነትን የማስጠበቅ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ኤጀንሲ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የተመራቂዎቹ ጥያቄ....

"ሰላም ፀግሽ ...ዶክተር ሳ__ እንባላለሁ ከመቀለ ዩኒቨርሲቲ የካቲት 16 ነበር የተመረቅኩት እስካሁን ስራ አልመደቡንም፤ ከዚህ በፊት ከሁለት ሳምንት በኃላ ነበር የሚመድቡት #FOMH አናግረን ነበር እናም ሁሉም ክልል ለሀኪም የሚሆን #በጀት_የለንም ብለዋል፤ ጠብቁ የሚል ምላሽ ነው የተሰጠን። 7 አመታትን በአድካሚ የትምህርት ስርዓት አልፈን ይህ መሆኑ አሳዝኖኛል።"

ይህን መሰሉ በርካታ ተመሳሳይ መልዕክቶች እየመጡ ናቸው፤ ተመራቂ ዶክተሮቹ መንግስት #አፋጣኝ_ምላሽ እና #መፍትሄ እንዲፈልግላቸው እየጠየቁ ናቸው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia