TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#አቢሲንያ_ባንክ

አዲሱን የአቢሲንያ ሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ፣ ነባር የአቢሲንያ ሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚዎች በቀላሉ አክቲቬት ማድረግ የሚችሉበት ቀላል መመሪያ - እነሆ!
ለአንድሮይድ ስልኮች https://play.google.com/store/apps/details?id=com.boa.boaMobileBanking&hl=en&gl=US

ለአፕል ስልኮች  https://apps.apple.com/us/app/boamobile/id6463218765

ለሁዋዌ ስልኮች https://appgallery.huawei.com/app/C110106115
የአምስተኛ ዙር የባጃጅ ተረክ አድራጊ ወሳኞች ታውቀዋል።
እንኳን ደስ አላችሁ!
ሽልማቱ እንደቀጠለ ነዉ!
M-PESA ላይ እንመዝገብ፣ በM-PESA እንገበያይ፣ ቀጣይ እድለኛ አሸናፊዎች እንሁን።

🔗 የM-PESA ሳፋሪኮምን መተግበሪያ በዚህ ሊንክ ያውርዱ፡ https://bit.ly/M-PESA_SafaricomEthiopia


ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም የቻት ግሩፕ
https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC https://t.iss.one/SafaricomETForum እንዲሁም @SafaricomETCare
24/7 መጠየቅ ይቻላል!

#MPESASafaricom
#SafaricomET #TerekBeMPESA
#FurtherAheadTogether
#ዓድዋ

እንኳን ለ128ኛው የዓድዋ ድል በዓል ቀን አደረሳችሁ !

" ዓድዋ ዛሬ ናት አድዋ ትናንት
መቼ ተነሱና የወዳደቁት
ምስጋና ለእነርሱ ለአድዋ ጀግኖች
ለዛሬ ነፃነት ላበቁኝ ወገኖች
የጥቁር ድል አምባ ዓድዋ
አፍሪካ እምዬ #ኢትዮጵያ
ተናገሪ
የድል ታሪክሽን አውሪ !!  " - ጂጂ

መልካም የድል በዓል ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ !!

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ዓድዋ128 #ዓድዋ

ፕሬዝዳንት ሥህለወርቅ ዘውዴ በታሪካዊቷ ከተማ ዓድዋ ለሚከበረው የዓድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ላይ ለመገኘት ትግራይ ክልል ገብተዋል።

ፕሬዝዳንቷ መቐለ አሉላ አባነጋ ኤርፖርት ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

ከመቐለ በሄልኮፕተር ወደ ዓድዋ በመጓዝ ላይ መሆናቸው በስፋት እየተነገረ ነው።

የዓድዋ በዓል የፌደራል መንግስት ባካተተ መልኩ መከበር የቆመው ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ ነበር።

ከ4 ዓመት በኃላ ወደ ነበረው የበዓል አከባበር ለመመለስ እየተሞከረ መሆኑን በዛው በዓድዋ የሚገኘው የመቐለው የቲክቫህ ቤተሰብ አባል መረጃውን አጋርቷል።

የፎቶ ባለቤት ፦ ድምፂ ወያነ (መቐለ)

@tikvahethiopia
#ዓድዋ

" ኢትዮጵያ ምን ጊዜም አሸናፊ ናት " - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

128ኛው የዓድዋ ድል በዓል በአዲስ አበባ ከተማ በቅርቡ በተመረቀው " የዓድዋ ድል መታሰቢያ " እየተከበረ ይገኛል።

በዚሁ ዝግጅት ላይ የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት መሪዎች፣ የተለያዩ ባለልስጣናት ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች መገኘታቸውን ለመረዳት ተችሏል።

በዓሉ በሀገር መከላከያ ወታደራዊ ትርኢት እና በሌሎችም ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል።

የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፥ የዓድዋ ድል ደማቅ ታሪክ የተጻፈበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

" ቀደም ሲል #ለትውስታ ብቻ ይከበር ነበር " ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ " ዘንድሮ ግን ድሉን የሚመጥን መታሰቢያ በዚህ ትውልድ ተገንብቷል " ብለዋል።

" የጦር መሪዎችን ጨምሮ ብሔር ብሔረሰቦች በመታሰቢያው መካተታቸውን የሚደነቅ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

" የመከላከያ ሠራዊት የዓድዋ ጀግኖችን ሥራ ውርሱ አድርጎ ለሀገሩ በኩራት ዘብ ይቆማል " ብለዋል።

ፊልድማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፤ " ሀገራችን ጠንካራ የመከላከያ ኃይል እንዳላት ለኢትዮጵያውያን ማረጋገጥ እፈልጋለሁ " ነው ያሉ ሲሆን " የኢትዮጵያ መከላከያ ከሀገራችን አልፎ ለሌሎች ሀገራትም ኩራትና መከታ ነው ይህንንም የወደቀላቸው ይመሰክራሉ " ሲሉ ገልጸዋል፡፡

" ኢትዮጵያ ምን ጊዜም አሸናፊ ናት፤ ዛሬም የዓድዋ ጀግኖች ልጆች መሆናችንን እያስመሰከርን እንቀጥላለን " ማለታቸውን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

@tikvahethiopia