TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ኢትዮጵያ እና አሜሪካ ወታደራዊ ልምምድ ሊያደርጉ ነው። ወታደራዊ ልምምዱ የአሜሪካ መከላከያ አባላት ከኢትዮጵያ መከላከያ ሃይል ጋር በጥምረት የሚካሄድ መሆኑ ተገልጿል። ልምምዱ #በሶማሊያ በተሰማራው የአፍሪካ ህብረት ሰላም አስከባሪ ሃይል (አሚሶም) አባላትን አቅም ማሳደግ ላይ ያተኮረ ሲሆን፥ ወደ 1 ሺህ 100 የሚጠጉ ወታደራዊና የመንግስት ሃላፊዎች ይሳተፉበታል። ልምምዱ የመከላከያ አባላትን ዝግጁነትና አቅም በማሳደግ ሰላምን ለማስከበር የሚደረገውን ጥረት እንዲደግፉና በቀጠናው ሰላምን ለማስፈን እንደሚያግዝም ታምኖበታል። የፊታችን ሰኞ የሚጀመረው የ2019 ወታደራዊ ልምምድ ለ17 ቀናት እንደሚቆይ በኢትዮጵያ ከአሜሪካ ኤምባሲን ጠቅሶ ኤፍ ቢሲ ዘቧል።

በወታደራዊ ልምምዱ ላይ፦

•ከብራዚል
•ከብሩንዲ
•ከካናዳ
•ከጂቡቲ
•ከፈረንሳይ
•ከጀርመን
•ከጣሊያን
•ከኬንያ
•ከኔዘርላንድስ
•ከሩዋንዳ
•ከሶማሊያ
•ከኡጋንዳ እና ዩናይትድ ኪንግደም የተውጣጡ #ወታደሮች ይሳተፋሉ።

Via #EPA/fbc/
🗞ቀን ሃምሌ 3/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
" ሁላችሁም የውጭ አገራት ጣልቃ እንዳትገቡ " - ኮሎኔል ሜጀር አማዱ

በአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት መፈንቅለ መንግሥት ሲደረግ በተደጋጋሚ ተሰምቷል።

አሁን ደግሞ በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ኒጀር #ወታደሮች መፈንቅለ መንግሥት አውጀዋል።

ወታደሮሹ ሕገ-መንግሥቱን መበተናቸውን፤ ሁሉም የመንግሥት ተቋማት ለጊዜው ሥራ ማቆማቸውን እና የሃገሪቱ ድንበሮች መዘጋታቸውን ይፋ አድርገዋል።

ከረቡዕ ጀምሮ የኒጀር ፕሬዝደንት ሞሐመድ ባዙም በወታደሮች ቁጥጥር ሥር እንዳሉ ተነግሯል።

ተመድ እንዲሁም አሜሪካ ለፕሬዝደንቱ ድጋፍ እንደሚያደርጉ አሳውቀዋል።

ረቡዕ ዕለት ዘጠኝ የወታደር መለዮ በለበሱ ሰዎች ተከበው በቴሌቪዥን መስኮት መግለጫ የሰጡት ኮሎኔል ሜጀር አማዱ አብድራማኔ ፤ " እኛ የመከላከያና የፀጥታ ኃይሎች የምታውቁት መንግሥት ከሥልጣን አውርደናል " ብለዋል።

የሃገሪቱ ሁሉም ተቋማት ለጊዜ ሥራ እንደሚያቆሙ የገለጹት ኮሎኔሉ ሚኒስትሮች የቀን ተቀን ሥራውን እንደሚመሩ ገልጠዋል።

" ሁሉም የውጭ አገራት ጣልቃ እንዳይገቡ እንጠይቃለን። ሁኔታዎች እስኪረጋጉ በምድርም ሆነ በአየር ድንበራችንን ዘግተናል " ብለዋል።

አክለው ላልተወሰነ ጊዜ ከምሽት 4 ሰዓት እስከ ንጋት 11 የሚቆይ ሰዓት እላፊ መታወጁንም ማሳወቃቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

የኒጀር ጎረቤት የሆኑት ማሊ እና ቡርኪና ፋሶ በቅርብ ዓመታት በተመሳሳይ በመፈንቅለ መንግሥት ምክንያት ታምሰው እንደነበር አይዘነጋም። #ቢቢሲ

@tikvahethiopia
4.28K👍1.08K👎110🕊39😢27🥰18👏16😱12🙏7