#NBE
በባንኮች እና በማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ገንዘብ አስቀማጮች ዋስትና ለመስጠት የተቋቋመው የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ እስከ 200 ሺሕ ብር ተቀማጭ ገንዘብ ላላቸው ዋስትና እንደሚሰጥ ተገለጸ፡፡
ባንኮች እና የማክሮ ፋይናንስ ተቋማት በየዓመቱ ከተቀማጭ ገንዘባቸው 0.2 በመቶ ለፈንዱ ገቢ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ አቶ ሰለሞን ደስታ ለሪፖርተር ጋዜጣ ተከታዩን ብለዋል ፦
" በየባንኩ ለእያንዳንዱ አስቀማጭ እስከ 200 ሺሕ ብር ለሚሆን ተቀማጭ ገንዘብ የዋስትና ሽፋን ይሰጣል፡፡
የመድን ሽፋኑ መጠን እስከ 200 ሺሕ ብር ለሚሆነው ተቀማጭ ገንዘብ የዋስትና ሽፋኑ እንዲሰጥ የተወሰነው፣ 96 በመቶ ያህል አስቀማጮች የተቀማጭ ገንዘባቸው መጠን የተጠቀሰውን ያህል ስለሆነ ነው።
በዚህ መሠረት የመድን ሽፋኑ ይሰጣል። ይህ ውሳኔ አብዛኞቹን አስቀማጮች የሚሸፍን ነው።
ባንኮች ለዚህ ዋስትና ሽፋን ተቀማጭ የሚያደርጉት በየዓመቱ ከጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘባቸው 0.2 በመቶ የሚሆነውን በማስላት ለፈንዱ ገቢ በማድረግ ተፈጻሚ ይሆናል።
የተቀማጭ ገንዘብ ዋስትና ፈንድ አገልግሎት ሲጀመር ባንኮቹ የሚከፍሉት ክፍያ ይኖራል። የገንዘቡ መጠን ግን ገና አልተወሰነም ። "
More : https://telegra.ph/Reporter-Newspaper-05-07
#ሪፖርተር
@tikvahethiopia
በባንኮች እና በማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ገንዘብ አስቀማጮች ዋስትና ለመስጠት የተቋቋመው የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ እስከ 200 ሺሕ ብር ተቀማጭ ገንዘብ ላላቸው ዋስትና እንደሚሰጥ ተገለጸ፡፡
ባንኮች እና የማክሮ ፋይናንስ ተቋማት በየዓመቱ ከተቀማጭ ገንዘባቸው 0.2 በመቶ ለፈንዱ ገቢ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ አቶ ሰለሞን ደስታ ለሪፖርተር ጋዜጣ ተከታዩን ብለዋል ፦
" በየባንኩ ለእያንዳንዱ አስቀማጭ እስከ 200 ሺሕ ብር ለሚሆን ተቀማጭ ገንዘብ የዋስትና ሽፋን ይሰጣል፡፡
የመድን ሽፋኑ መጠን እስከ 200 ሺሕ ብር ለሚሆነው ተቀማጭ ገንዘብ የዋስትና ሽፋኑ እንዲሰጥ የተወሰነው፣ 96 በመቶ ያህል አስቀማጮች የተቀማጭ ገንዘባቸው መጠን የተጠቀሰውን ያህል ስለሆነ ነው።
በዚህ መሠረት የመድን ሽፋኑ ይሰጣል። ይህ ውሳኔ አብዛኞቹን አስቀማጮች የሚሸፍን ነው።
ባንኮች ለዚህ ዋስትና ሽፋን ተቀማጭ የሚያደርጉት በየዓመቱ ከጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘባቸው 0.2 በመቶ የሚሆነውን በማስላት ለፈንዱ ገቢ በማድረግ ተፈጻሚ ይሆናል።
የተቀማጭ ገንዘብ ዋስትና ፈንድ አገልግሎት ሲጀመር ባንኮቹ የሚከፍሉት ክፍያ ይኖራል። የገንዘቡ መጠን ግን ገና አልተወሰነም ። "
More : https://telegra.ph/Reporter-Newspaper-05-07
#ሪፖርተር
@tikvahethiopia
#NBE
የኢንሹራንስ ዘርፉ ፤ ከ " ብሔራዊ ባንክ " ውጪ በሆነ ተቆጣጣሪ ተቋም እንዲመራ ለማስቻል ተፈላጊ የሆነው ጥናት በዓለም ባንክ አማካይነት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡
በዓለም ባንክ በኩል የሚደረገው ጥናት በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቅ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን ሰፊ የሆኑ ተግባራትን እንደሚሸፍን ተጠቅሷል።
የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ አቶ ሰለሞን ደስታ ይህ በተመለከተ ለሪፖርተር ቃላቸውን ሰጥተው ነበር።
ምን አሉ ?
አቶ ሰለሞን ደስታ ፦
" የኢንሹራንስ ዘርፉን የሚቆጣጠር ከብሔራዊ ባንክ ውጪ የሆነ ተቆጣጣሪ እንዲቋቋም ጥናት ተጀምሯል።
Terms of Reference እና ሌሎችም ጉዳዮች እየተሠሩ ነው።
በጥናቱ የመጀመርያ ሥራ ተብሎ የተያዘው ጉዳይ ገለልተኛ ተቋም ‹እንዴት ይዋቀር ? የሚለው ሲሆን ከዚያም ተጠሪነቱ ለማን ይሁን ? ለጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ነው ? ለፓርላማው ነው ? የሚለውን ጨምሮ ሌሎችም ጉዳዮች ናቸው።
ይህ ብቻም ሳይሆን የኢንሹራንስ ዘርፉን ለውጭ ክፍት ለማድረግ ሪፎርም መደረግ እንዳለበትና ብዙ የሕግ ማዕቀፎች ጎን ለጎን መሠራት ስላለበት ሥራው በአሁኑ ወቅት ተጀምሯል። "
በሌላ በኩል ፦
የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ " ለውጭ ተወዳዳሪዎች " ክፍት እንዲሆን ከተወሰነ በኋላ በ2009 ዓ/ም የወጣው የባንክ ሥራ ረቂቅ አዋጅ የማሻሻል ሥራ እየተጠናቀቀ እንደሆነ ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል፡፡
የብሔራዊ ምክትል ገዥ አቶ ሰለሞን ደስታ ፦
" ከአንዳንድ የድጋፍ ሰጪዎች ግብዓቶች ካሉ እየጠየቅን ነው፡፡
የብሔራዊ ባንክ ገዥው ከዚህ በፊት ባሉት መሠረት በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ለፓርላማ እናቀርባለን ተብሏል፡፡ ስለዚህ እየተፋጠነ ነው።
አዋጁ እንደወጣ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ከሦስት እስከ አምስት ለሚጠጉ የውጭ ባንኮች ፈቃድ ይሰጣል ተብሎ ታቅዷል።
ቁጥሩ ከዚያ በላይ ከፍ የማድረግ ዕቅድ የለም፤ ይህም ከአቅም በላይ እንዳይሆን ከሚል ዕሳቤ ነው። " ሲሉ ተናግረዋል።
Credit - Ethiopian Reporter
@tikvahethiopia
የኢንሹራንስ ዘርፉ ፤ ከ " ብሔራዊ ባንክ " ውጪ በሆነ ተቆጣጣሪ ተቋም እንዲመራ ለማስቻል ተፈላጊ የሆነው ጥናት በዓለም ባንክ አማካይነት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡
በዓለም ባንክ በኩል የሚደረገው ጥናት በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቅ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን ሰፊ የሆኑ ተግባራትን እንደሚሸፍን ተጠቅሷል።
የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ አቶ ሰለሞን ደስታ ይህ በተመለከተ ለሪፖርተር ቃላቸውን ሰጥተው ነበር።
ምን አሉ ?
አቶ ሰለሞን ደስታ ፦
" የኢንሹራንስ ዘርፉን የሚቆጣጠር ከብሔራዊ ባንክ ውጪ የሆነ ተቆጣጣሪ እንዲቋቋም ጥናት ተጀምሯል።
Terms of Reference እና ሌሎችም ጉዳዮች እየተሠሩ ነው።
በጥናቱ የመጀመርያ ሥራ ተብሎ የተያዘው ጉዳይ ገለልተኛ ተቋም ‹እንዴት ይዋቀር ? የሚለው ሲሆን ከዚያም ተጠሪነቱ ለማን ይሁን ? ለጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ነው ? ለፓርላማው ነው ? የሚለውን ጨምሮ ሌሎችም ጉዳዮች ናቸው።
ይህ ብቻም ሳይሆን የኢንሹራንስ ዘርፉን ለውጭ ክፍት ለማድረግ ሪፎርም መደረግ እንዳለበትና ብዙ የሕግ ማዕቀፎች ጎን ለጎን መሠራት ስላለበት ሥራው በአሁኑ ወቅት ተጀምሯል። "
በሌላ በኩል ፦
የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ " ለውጭ ተወዳዳሪዎች " ክፍት እንዲሆን ከተወሰነ በኋላ በ2009 ዓ/ም የወጣው የባንክ ሥራ ረቂቅ አዋጅ የማሻሻል ሥራ እየተጠናቀቀ እንደሆነ ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል፡፡
የብሔራዊ ምክትል ገዥ አቶ ሰለሞን ደስታ ፦
" ከአንዳንድ የድጋፍ ሰጪዎች ግብዓቶች ካሉ እየጠየቅን ነው፡፡
የብሔራዊ ባንክ ገዥው ከዚህ በፊት ባሉት መሠረት በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ለፓርላማ እናቀርባለን ተብሏል፡፡ ስለዚህ እየተፋጠነ ነው።
አዋጁ እንደወጣ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ከሦስት እስከ አምስት ለሚጠጉ የውጭ ባንኮች ፈቃድ ይሰጣል ተብሎ ታቅዷል።
ቁጥሩ ከዚያ በላይ ከፍ የማድረግ ዕቅድ የለም፤ ይህም ከአቅም በላይ እንዳይሆን ከሚል ዕሳቤ ነው። " ሲሉ ተናግረዋል።
Credit - Ethiopian Reporter
@tikvahethiopia