#ሰበር_ዜና በደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መ በሚገኙ #ሁሉም ዞኖች፣ ከተማ አስተዳደሮች እና ልዩ ወረዳዎች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ #ታውጇል። #ETHIOPIA
#State_of_emergency
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#State_of_emergency
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#State_of_Emergency
ለ6 ወራት የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተፈፃሚነት ጊዜ እንዲያጥር የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ውሳኔ አሳልፋል።
ም/ቤቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ማውጣት የግድ አስፈላጊ እንዲሆን አድርጎ የነበረው ሁኔታ የተቀየረ መሆኑን ገልጿል።
አክሎም ስጋቱን በመደበኛ የሕግ ማስከበር ስራ መከላከልና መቆጣጠር የሚቻልበት ደረጃ ላይ መደረሱን በመግለፅ ለ6 ወራት የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተፈፃሚነት ጊዜ ማሳጠር አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን አሳውቋል።
በዚህም አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የ6 ወር ጊዜው ሳይጠናቀቅ ጊዜውን የማሳጠር ስልጣን ያለው ህ/ተ/ም/ቤት የአዋጁን ተፈጻሚነት ቀሪ እንዲያደርገው የሚጠይቅ የውሳኔ ሃሳብ ለምክር ቤቱ እንዲተላለፍ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ አሳልፏል።
@tikvahethiopia
ለ6 ወራት የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተፈፃሚነት ጊዜ እንዲያጥር የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ውሳኔ አሳልፋል።
ም/ቤቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ማውጣት የግድ አስፈላጊ እንዲሆን አድርጎ የነበረው ሁኔታ የተቀየረ መሆኑን ገልጿል።
አክሎም ስጋቱን በመደበኛ የሕግ ማስከበር ስራ መከላከልና መቆጣጠር የሚቻልበት ደረጃ ላይ መደረሱን በመግለፅ ለ6 ወራት የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተፈፃሚነት ጊዜ ማሳጠር አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን አሳውቋል።
በዚህም አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የ6 ወር ጊዜው ሳይጠናቀቅ ጊዜውን የማሳጠር ስልጣን ያለው ህ/ተ/ም/ቤት የአዋጁን ተፈጻሚነት ቀሪ እንዲያደርገው የሚጠይቅ የውሳኔ ሃሳብ ለምክር ቤቱ እንዲተላለፍ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ አሳልፏል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#State_of_Emergency
ከሳምንታት በፊት የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጊዜው ከመጠናቀቁ በፊት ቀሪ እንዲሆን ያቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ም/ ቤት ምርምሮ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ም/ ቤቱ ውሳኔውን መርምሮ የሚያፀድቀው ነገ በሚያካሂደው አስቸኳይ ስብሰባ ነው።
በውሳኔ ሃሳቡ ላይ ድምጽ ከመስጠቱ በፊት የም/ቤቱ የሕግ፣ ፍትህ እና ዲሞክራሲ ቋሚ ኮሚቴ በጉዳዩ ዙሪያ ማብራሪያ እንደሚሰጥ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር በድረገፁ ላይ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
ከሳምንታት በፊት የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጊዜው ከመጠናቀቁ በፊት ቀሪ እንዲሆን ያቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ም/ ቤት ምርምሮ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ም/ ቤቱ ውሳኔውን መርምሮ የሚያፀድቀው ነገ በሚያካሂደው አስቸኳይ ስብሰባ ነው።
በውሳኔ ሃሳቡ ላይ ድምጽ ከመስጠቱ በፊት የም/ቤቱ የሕግ፣ ፍትህ እና ዲሞክራሲ ቋሚ ኮሚቴ በጉዳዩ ዙሪያ ማብራሪያ እንደሚሰጥ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር በድረገፁ ላይ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert በአማራ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ አሳለፈ። የሚኒስትሮች ም/ቤት በዛሬው ዕለት 23ኛ መደበኛ ስብሰባ አካሂዶ ነበር። በዚህም ስብሰባ ፤ " የሕዝብን ሠላም እና ደህንነት ለማስጠበቅ " በቀረበው የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6 /2015 ላይ መመምከሩ ተነግሯል። ምክር ቤቱ ፤ " በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የሚታየውን…
#State_of_Emergency
ዛሬ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ " አማራ ክልል " የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲደነገግ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወቃል።
አመሻሹን ደግሞ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዴት ተግባራዊ እንደሚደረግ እንዲሁም የሚወሰዱ እርምጃዎች እና ተከለከሉ ተግባራት ዝርዝር ይፋ ተደርጓል።
በዚህም ፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የሚያስፈፅም በብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬከተር ጄነራል የሚመራ የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ መቋቋሙ ተገልጿል።
የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ አባላት፣ መዋቅር እና አደረጃጀት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚወሰን ይሆናል ተብሏል።
የአስቸኳይ ጊዜ መምሪያ ጠቅላይ ዕዙ ተጠሪነት ለኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እንደሚሆንም ተገልጿል።
በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የሚወሰዱ እርምጃዎችና የተከለከሉ ተግባራት ምንድናቸው ?
- ማንኛውም ሰው በአዋጁ መሰረት የሚወጡ መመሪያዎችን፣ የሚሰጡ ትዕዛዞች እና የሚተላለፉ ውሳኔዎችን የመተግበር እና የማከበር ግዴታ አለበት ተብሏል።
- የአስቸኳይ ጊዜ ጠ/መምሪያ ዕዙን እንቅስቃሴና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አላማ #የሚቃረን ፣ #የሚቃወም እና በክልሉ የአመጽ እንቅስቃሴን የሚያበረታታ ፣ ሰላማዊ ዜጎችን የሚያሸብር፣ እንዲሁም የፀጥታ መደፍረሱን የሚያባብስ ንግግር፣ የቀጥታም ሆነ የተዘዋዋሪ ቅስቀሳ በማንኛውም መንገድ ማድረግ ወይም ማሰራጭት የተከለከለ መሆኑ ተመላክቷል።
- በየትኛውም መንገድ፣ በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ ለታጣቂ ቡድኖች የገንዝብ፣ የመረጃ፣ የቁስም ሆነ የሞራል ድጋፍ ማድረግ የተከለከለ መሆኑ ተገልጿል።
- ከአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ ፈቃድ ውጪ ማንኛውንም የአደባባይ ስብሰባ ወይም ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ እንዲሁ ተከልክሏል።
- ከአስቸኳይ ጊዜ ጠ/መምሪያ ዕዙ ፈቃድ ውጭ ማናቸውንም የጦር መሳርያ ይዞ መንቀሳቀስ እንደማይቻል ተመላክቷል።
(ተጨማሪ ዝርዝር ጉዳዮችን ከላይ ያንብቡ)
@tikvahethiopia
ዛሬ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ " አማራ ክልል " የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲደነገግ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወቃል።
አመሻሹን ደግሞ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዴት ተግባራዊ እንደሚደረግ እንዲሁም የሚወሰዱ እርምጃዎች እና ተከለከሉ ተግባራት ዝርዝር ይፋ ተደርጓል።
በዚህም ፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የሚያስፈፅም በብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬከተር ጄነራል የሚመራ የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ መቋቋሙ ተገልጿል።
የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ አባላት፣ መዋቅር እና አደረጃጀት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚወሰን ይሆናል ተብሏል።
የአስቸኳይ ጊዜ መምሪያ ጠቅላይ ዕዙ ተጠሪነት ለኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እንደሚሆንም ተገልጿል።
በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የሚወሰዱ እርምጃዎችና የተከለከሉ ተግባራት ምንድናቸው ?
- ማንኛውም ሰው በአዋጁ መሰረት የሚወጡ መመሪያዎችን፣ የሚሰጡ ትዕዛዞች እና የሚተላለፉ ውሳኔዎችን የመተግበር እና የማከበር ግዴታ አለበት ተብሏል።
- የአስቸኳይ ጊዜ ጠ/መምሪያ ዕዙን እንቅስቃሴና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አላማ #የሚቃረን ፣ #የሚቃወም እና በክልሉ የአመጽ እንቅስቃሴን የሚያበረታታ ፣ ሰላማዊ ዜጎችን የሚያሸብር፣ እንዲሁም የፀጥታ መደፍረሱን የሚያባብስ ንግግር፣ የቀጥታም ሆነ የተዘዋዋሪ ቅስቀሳ በማንኛውም መንገድ ማድረግ ወይም ማሰራጭት የተከለከለ መሆኑ ተመላክቷል።
- በየትኛውም መንገድ፣ በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ ለታጣቂ ቡድኖች የገንዝብ፣ የመረጃ፣ የቁስም ሆነ የሞራል ድጋፍ ማድረግ የተከለከለ መሆኑ ተገልጿል።
- ከአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ ፈቃድ ውጪ ማንኛውንም የአደባባይ ስብሰባ ወይም ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ እንዲሁ ተከልክሏል።
- ከአስቸኳይ ጊዜ ጠ/መምሪያ ዕዙ ፈቃድ ውጭ ማናቸውንም የጦር መሳርያ ይዞ መንቀሳቀስ እንደማይቻል ተመላክቷል።
(ተጨማሪ ዝርዝር ጉዳዮችን ከላይ ያንብቡ)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#State_of_Emergency ዛሬ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ " አማራ ክልል " የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲደነገግ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወቃል። አመሻሹን ደግሞ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዴት ተግባራዊ እንደሚደረግ እንዲሁም የሚወሰዱ እርምጃዎች እና ተከለከሉ ተግባራት ዝርዝር ይፋ ተደርጓል። በዚህም ፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የሚያስፈፅም በብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬከተር ጄነራል የሚመራ…
#State_of_Emergency
የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ባወጣው መግለጫ ፤ በ " መጀመሪያ ምዕራፍ " ዕቅድ በትልልቆቹ የአማራ ክልል ከተሞች ፦
- ባሕር ዳር፣
- ደብረ ማርቆስ፣
- ደብረ ብርሃን፣
- ላሊበላ፣
- ጎንደር
- ሸዋ ሮቢት ላይ አስፈላጊውን እርምጃ በመውሰድ " የሕግ የበላይነት እንዲከበር አስደርጌያለሁ " ብሏል።
በእነዚህ ከተሞች " በዘረፋ እና በጥፋት የተሰማራ ቡድንን በመምታት በከተሞቹ ላይ የሕግ የበላይነትን ማስከበር ተችሏል " ሲል ገልጿል።
በአሁኑ ሰዓት ከተሞቹ ከስጋት ነጻ መሆናቸውን የገለፀው ዕዙ ፤ የመከላከያ ሠራዊቱ እና የክልሉ ህግ አስከባሪ አካላት የማጥራት ስራ እየሰሩ ነው ብሏል።
የመጨረሻውን የማጽዳት እና የመልቀም ተግባር በማከናወን ከተሞቹ በአጭር ጊዜ ወደ ተሟላ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲመለሱ ይደረጋል ሲልም አሳውቋል።
የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ ፦
- ከነገ ሐሙስ ነሐሴ 4 ጀምሮ ከላይ በተጠቀሱት ከተሞች መደበኛ የአውሮፕላን በረራ እንደሚጀምር፤
- ከባጃጅና ከሞተር ሳይክል በስተቀር ሁሉም ዓይነት የከተማ የትራንስፖርት አገልግሎቶች ወደ አገልግሎት እንደሚገቡ፤
- የመንግሥት ፣ የማኅበረሰብ አገልግሎት ፣ የንግድ፣ የጤና፣ የፋይናንስ፣ ወዘተ. ተቋማት አገልግሎት እንዲሰጡ እንደሚደረግ አሳውቋል።
በሌላ በኩል ፤ እስካሁን 14 ተጠርጣሪዎችን በአዲስ አበባ ከተማ በቁጥጥር ሥር ማዋሉንና ወደፊትም እንደሁኔታው በቁጥጥር ሥር የሚያውላቸውን ግለሰቦች አስመልክቶ አስፈላጊውን መረጃ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ገልጿል።
@tikvahethiopia
የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ባወጣው መግለጫ ፤ በ " መጀመሪያ ምዕራፍ " ዕቅድ በትልልቆቹ የአማራ ክልል ከተሞች ፦
- ባሕር ዳር፣
- ደብረ ማርቆስ፣
- ደብረ ብርሃን፣
- ላሊበላ፣
- ጎንደር
- ሸዋ ሮቢት ላይ አስፈላጊውን እርምጃ በመውሰድ " የሕግ የበላይነት እንዲከበር አስደርጌያለሁ " ብሏል።
በእነዚህ ከተሞች " በዘረፋ እና በጥፋት የተሰማራ ቡድንን በመምታት በከተሞቹ ላይ የሕግ የበላይነትን ማስከበር ተችሏል " ሲል ገልጿል።
በአሁኑ ሰዓት ከተሞቹ ከስጋት ነጻ መሆናቸውን የገለፀው ዕዙ ፤ የመከላከያ ሠራዊቱ እና የክልሉ ህግ አስከባሪ አካላት የማጥራት ስራ እየሰሩ ነው ብሏል።
የመጨረሻውን የማጽዳት እና የመልቀም ተግባር በማከናወን ከተሞቹ በአጭር ጊዜ ወደ ተሟላ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲመለሱ ይደረጋል ሲልም አሳውቋል።
የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ ፦
- ከነገ ሐሙስ ነሐሴ 4 ጀምሮ ከላይ በተጠቀሱት ከተሞች መደበኛ የአውሮፕላን በረራ እንደሚጀምር፤
- ከባጃጅና ከሞተር ሳይክል በስተቀር ሁሉም ዓይነት የከተማ የትራንስፖርት አገልግሎቶች ወደ አገልግሎት እንደሚገቡ፤
- የመንግሥት ፣ የማኅበረሰብ አገልግሎት ፣ የንግድ፣ የጤና፣ የፋይናንስ፣ ወዘተ. ተቋማት አገልግሎት እንዲሰጡ እንደሚደረግ አሳውቋል።
በሌላ በኩል ፤ እስካሁን 14 ተጠርጣሪዎችን በአዲስ አበባ ከተማ በቁጥጥር ሥር ማዋሉንና ወደፊትም እንደሁኔታው በቁጥጥር ሥር የሚያውላቸውን ግለሰቦች አስመልክቶ አስፈላጊውን መረጃ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ገልጿል።
@tikvahethiopia