TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ጋር መወያየታቸውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቋል።
ሚኒስቴሩ ይፋ ባደረገው መረጃ ውይይቱን በተመለከተ ዝርዝር ጉዳዮችን ባያብራራም አቶ ደመቀ እና የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሊንከን በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ምክክር መደረጉን አመልክቷል።
@tikvahethiopia
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ጋር መወያየታቸውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቋል።
ሚኒስቴሩ ይፋ ባደረገው መረጃ ውይይቱን በተመለከተ ዝርዝር ጉዳዮችን ባያብራራም አቶ ደመቀ እና የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሊንከን በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ምክክር መደረጉን አመልክቷል።
@tikvahethiopia
የተማሪ ሊዲያ አበራ ጉዳይ ...
በደቡብ ክልል ሀላባ ቁሊቶ ከተማ በሚገኘው የሀለባ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ10ኛ ክፍል ተማሪዋ #ሊዲያ_አበራ የካቲት 22 ቀን 2015 ዓ/ም ከትምህርት ቤቷ ተወስዳ ከታሰረች በኋላ ጉዳዩ የማኅበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ሆኗል።
ሊዲያ ከታሰራች በኋላ ለ5 ቀናት ፍርድ ቤት ሳትቀርብ መቆየቷን እና በእስር ቤት ውስጥ የሰብአዊ መብት ጥሰት እንደተፈጸመባት አባቷ አቶ አበራ ሻሞሮ እንዲሁም ጠበቃዋ አቶ አበባየሁ ጌታ እንዳገለፁለት ቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት በድረገፁ አስነብቧል።
በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሕግ እና ፖሊስ ሥራ ክፍል ዳይሬክተር ወ/ሮ ታሪኳ ጌታቸው የ14 ዓመቷ ተማሪን ጉዳይ ኮሚሽኑ እየተከታተለ መሆኑን ገልፀዋል።
የሊዲያ እስር ምክንያት ምንድን ነው ?
በሀላባ ቁሊቶ 30 ዓመታት የኖሩት አቶ አበራ ሻሞሮ፣ ሁለት ሴት ልጆች የሃላባ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ10ኛ እና 11ኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸው።
ሊዲያ የካቲት 22/2015 ዓ.ም. በመደበኛ ትምህርቷ ላይ ተገኝታ ነበር።
በዚያን ዕለት ሊዲያ በምትማርበት ክፍል ውስጥ አንዲት ተማሪ መውደቋ የነገሮች ሁሉ መነሻ ነው።
👉 ጉዳዩን በተመለከት ሰሜ አይጠቀስ ያሉ የሀላባ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር የሰጡት ቃል ፦
" ተማሪዋ የወደቀችው ሊዲያ መተት አሰርታባት ነው በሚል በተፈጠረ ግርግር የትምህርት ቤቱ ሥራ በጊዜያዊነት ተስተጓግሎ ነበር።
ከጥቂት ጊዜ በኋላም ፖሊሶች ወደ ትምህርት ቤቱ መጡ።
ያለምንም መጥሪያ...ፖሊሶች መጥተው ከነዩኒፎርሟ፣ ከነደብተሯ እያለቀሰች” ከትምህርት ቤት ወሰዷል።
ይህ በጣም አሳሳቢ እና የሚያሳዝን ነው። "
👉 የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ ወንድሙ መርጋም የሰጡት ቃል ፦
" በዚያን ዕለት ሌላም ተማሪ መውደቋ ለሊዲያ እስር ምክንያት ሆኗል። ሆኖም ታዳጊዋ ላይ ቀደም ብሎ ተማሪዎች እና ወላጆቻቸው አቤቱታ ያቀርቡባት ነበር።
ከእሷ ጋር አብረን ምግብ በልተናል የሚሉ 8 ተማሪዎች ወላጆች ቅሬታ አቅርበዋል፤ ትምህርት ቤቱ እርምጃ ይውሰድ የሚል ጫናም እየበረታ መጥቶ ነበር።
በዚህ ሳቢያ ትምህርት ቤቱ የቅሬታ አቅራቢ ተማሪዎች ወላጆች ጉዳዩን ወደ ፖሊስ ጣቢያ እንዲወስዱ አድርጓል።
በትምህርት ቤት ውስጥ ከእሷ [ሊዲያ] ጋራ ግንኙነት ነበረን፣ ምግብ በልተናል ያሉ 8 ተማሪዎች ወድቀዋል ፤ ይሄ ነገር ከእሷ ጋር ግንኙነት አለው? ወይስ የለውም ? የሚለውን ለማጣራት ነው ክስ ተመስርቶ በዚያው እየታየ ያለው።
በዕለቱ ተማሪዎች ስለተረበሹ እና እርምጃ መውሰድ ስላለብን...ለፖሊስ ልጅቷን በአፋጣኝ ይዛችሁ ብትሄዱ የተሻለ ይሆናል ያልነው። "
ሆኖም ይህ በሊዲያ ላይ የቀረበው ቅሬታ በእህቷ ላይ አልተሰማም ተብሏል።
👉 የሊዲያ ጠበቃ አቶ አበባየሁ ጌታ ፦
" ሊዲያ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ከተወሰደች በኋላ ከሕግ ውጪ ለ5 ቀናት ፍርድ ቤት ሳትቀርብ ታስራ ቆይታለች።
ከአምስት (5) ቀናት በኋላ ሃላባ መጀመሪያ ፍርድ ቤት ካለ ጠበቃ ጋር ቀርባ የ14 ቀናት ቀጥሮ ለምርመራ ከተሰጠ በኋላ ወደ ሃላባ ቁሊቶ ማረሚያ ቤት ተወስዳለች።
ይህ ድርጊት ከሕግ ጋር የሚጻረር ነው። ለአካለ መጠን ያልደረሰ ሰው በወንጀል ሲጠረጠር ከቤተሰቦቹ ጋር ቆይቶ ለምርመራ ሲፈልግ እንደሚጠራ በሕግ ተደንግጓል።
በተጠረጠረችበት ወንጀል #ጥፋተኛ ሆና ብትገኝ እንኳን የማረሚያ ቤት እስር እንደማይፈረድባት የወንጀል ሕጉ ያስቀምጣል።
በተሰጠው የጊዜ ቀጠሮ ላይ ለሃላባ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ተጠይቋል። ይግባኙም የታዳጊዋ አያያዝ እንዲሁም ለቀናት በእስር ላይ እንድትቆይ መደረጉ ተገቢ አይደለም የሚል ነው።
የሊዲያ ከሳሾች ጉዳት ደርሶብናል ያሉት ተማሪዎች ወላጆች ሲሆኑ ልጆቻችንን ላይ ባደረገችባቸው መተት/ድግምት አፍዝዛ ጉዳት አድርሳባቸዋለች የሚል ማመልከቻ አቅርበው ነው የተከሰሰችው።
ክሱ ተሰራ በተባለው መተት / ድግምት ተጎድተው ሕክምና ላይ የሚገኙ ተማሪዎች አሉ ይላል።
ሊዲያም ባለፈው አርብ አግኝተናት አናግረናት ነበር። በወቅቱም ንቅሳት ካለብሽ እናይሻለን በሚል እርቃኗን እንደፈተሿት ተናግራለች።
ሊዲያ እስሩ በተፈጸመባቸው የመጀመሪያዎቹ ቀናት ታለቅስ ነበር። አሁን መምህራን፣ የትምህርት ቤት ጓደኞቿ እና ሌሎች ሰዎች እየጠየቋት በመሆኑ በጥሩ ሞራል ላይ ትገኛለች።
በኢትዮጵያ ሕግ ድግምት ፣ ጥንቆላ፣ እኔ አውቅልሃለሁ ባይነት፣ መንፈስ መጥራት እና መሰል ወንጀሎች የሚዳኙበት ድንጋጌ አለ።
ሆኖም እነዚህ ወንጀሎች ጥቅምን ለማግኘት በማሰብ እና የሌላን ሰው ገንዘብ ለማግኘት የሚፈጸም እንጂ የግል ጥቅም ምን እንደሆነ በማታውቅ ታዳጊ ልጅ፣ ገንዘብ ያለበትን እጠቁማቸኋለሁ ባላለችበት ሁኔታ. . . [ሕጉ] ይህንን ሁኔታ ሊቀበለው አይችለም።
ሰዎችን ለማፍዘዝ የተለያዩ ዱቄት መሰል ምርቶችን ማምረት፣ መሸጥ እና ማሰተላለፍ ወንጀል ነው ሊዲያ ግን ይህንን ሁሉ አላደረገችም።
በማኅበራዊ ሚዲያዎች ለሕይወቷ የሚያሰጉ ዛቻዎች እና ማስፈራሪያዎች እየተዘዋወሩ ነው። በደረሰባት የሥነ ልቦና ጫና ምክንያት ከሥነ ልቦና ጫናው ተላቃ ትምህርቷን ትቀጥላለች ማለት ይከብዳል። "
👉 የሊዲያ አባት አቶ አበራ ሻሞሮ ፦
" ... የልጄ እስር የተወረወረ ዱብ ዕዳ ነው። ልጆቼ በትምህርታቸው ከአጠቃላይ ተማሪ ተሸላሚ ናቸው። እያጠኑ የሚያድሩ ናቸው።
የተቀረውን የትምህርት ጊዜ ሌላ አካባቢ እንዲጨርሱ እየሞከርኩ ነው።
ልጄም በማረሚያ ቤት ባነጋገርኩበት ወቅት መቼ ነው ከዚህ የምወጣው? ብላ ጠይዋኛለች። "
👉 ጉዳዩን በተመለከተ የሀላባ ዞን የቁሊቶ ከተማ አሰተዳደር ሰላም እና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ከቀናት በፊት በፌስቡክ ገጹ ይህን ብሏል ፦
" ... በከተማችን በሙሰሊም ሴት ተማሪዎች ላይ ድግምት አሲራለች ተብላ በታሰረች ተማሪ ሊዲያ አበራ በተያያዥ ጉዳይ በአቶ ናስር በሀላባ በዚህም ጉዳይ መሰል ተያያዥነት ያላቸው ግለሰቦችም ጭምር ተይዘው በምርመራ ሂደት በማረሚያ መኖራቸው ይታወቃል።
በታሰሩበት ኬዝ እንዳንድ አክቲቪስቶች ጉዳዩን ወደ ሓይማኖታዊ ለማስመሰል በማጦዝ የሚሞክሩ እንዳላችሁ በማሕበራዊ ሚዲያ እየታየ ያለው ሁኔታ በፖሊስ እና በምርመራ ባለሙያዎች ሂደቱ እየተጣራና ማንም በተጠረጠረበት ወንጀል ታሰሮ አንደሚጣራ የሚታወቅ ስለሆነ ሁሉም ማህበረሰብ በትዕግስት እንዲጠብቅ ስንል እናሳስባችኋለን።
#ይህንን_ተላልፎ የሚገኝ ማንኛውንም አካል በህግ የምንጠይቅ መሆኑን እናውቃለን። "
የመረጃ ምንጭ ፦ ቢቢሲ የአማርኛው አገልግሎት / የሀላባ ዞን የቁሊቶ ከተማ አሰተዳደር ሰላም እና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ናቸው።
@tikvahethiopia
በደቡብ ክልል ሀላባ ቁሊቶ ከተማ በሚገኘው የሀለባ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ10ኛ ክፍል ተማሪዋ #ሊዲያ_አበራ የካቲት 22 ቀን 2015 ዓ/ም ከትምህርት ቤቷ ተወስዳ ከታሰረች በኋላ ጉዳዩ የማኅበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ሆኗል።
ሊዲያ ከታሰራች በኋላ ለ5 ቀናት ፍርድ ቤት ሳትቀርብ መቆየቷን እና በእስር ቤት ውስጥ የሰብአዊ መብት ጥሰት እንደተፈጸመባት አባቷ አቶ አበራ ሻሞሮ እንዲሁም ጠበቃዋ አቶ አበባየሁ ጌታ እንዳገለፁለት ቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት በድረገፁ አስነብቧል።
በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሕግ እና ፖሊስ ሥራ ክፍል ዳይሬክተር ወ/ሮ ታሪኳ ጌታቸው የ14 ዓመቷ ተማሪን ጉዳይ ኮሚሽኑ እየተከታተለ መሆኑን ገልፀዋል።
የሊዲያ እስር ምክንያት ምንድን ነው ?
በሀላባ ቁሊቶ 30 ዓመታት የኖሩት አቶ አበራ ሻሞሮ፣ ሁለት ሴት ልጆች የሃላባ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ10ኛ እና 11ኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸው።
ሊዲያ የካቲት 22/2015 ዓ.ም. በመደበኛ ትምህርቷ ላይ ተገኝታ ነበር።
በዚያን ዕለት ሊዲያ በምትማርበት ክፍል ውስጥ አንዲት ተማሪ መውደቋ የነገሮች ሁሉ መነሻ ነው።
👉 ጉዳዩን በተመለከት ሰሜ አይጠቀስ ያሉ የሀላባ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር የሰጡት ቃል ፦
" ተማሪዋ የወደቀችው ሊዲያ መተት አሰርታባት ነው በሚል በተፈጠረ ግርግር የትምህርት ቤቱ ሥራ በጊዜያዊነት ተስተጓግሎ ነበር።
ከጥቂት ጊዜ በኋላም ፖሊሶች ወደ ትምህርት ቤቱ መጡ።
ያለምንም መጥሪያ...ፖሊሶች መጥተው ከነዩኒፎርሟ፣ ከነደብተሯ እያለቀሰች” ከትምህርት ቤት ወሰዷል።
ይህ በጣም አሳሳቢ እና የሚያሳዝን ነው። "
👉 የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ ወንድሙ መርጋም የሰጡት ቃል ፦
" በዚያን ዕለት ሌላም ተማሪ መውደቋ ለሊዲያ እስር ምክንያት ሆኗል። ሆኖም ታዳጊዋ ላይ ቀደም ብሎ ተማሪዎች እና ወላጆቻቸው አቤቱታ ያቀርቡባት ነበር።
ከእሷ ጋር አብረን ምግብ በልተናል የሚሉ 8 ተማሪዎች ወላጆች ቅሬታ አቅርበዋል፤ ትምህርት ቤቱ እርምጃ ይውሰድ የሚል ጫናም እየበረታ መጥቶ ነበር።
በዚህ ሳቢያ ትምህርት ቤቱ የቅሬታ አቅራቢ ተማሪዎች ወላጆች ጉዳዩን ወደ ፖሊስ ጣቢያ እንዲወስዱ አድርጓል።
በትምህርት ቤት ውስጥ ከእሷ [ሊዲያ] ጋራ ግንኙነት ነበረን፣ ምግብ በልተናል ያሉ 8 ተማሪዎች ወድቀዋል ፤ ይሄ ነገር ከእሷ ጋር ግንኙነት አለው? ወይስ የለውም ? የሚለውን ለማጣራት ነው ክስ ተመስርቶ በዚያው እየታየ ያለው።
በዕለቱ ተማሪዎች ስለተረበሹ እና እርምጃ መውሰድ ስላለብን...ለፖሊስ ልጅቷን በአፋጣኝ ይዛችሁ ብትሄዱ የተሻለ ይሆናል ያልነው። "
ሆኖም ይህ በሊዲያ ላይ የቀረበው ቅሬታ በእህቷ ላይ አልተሰማም ተብሏል።
👉 የሊዲያ ጠበቃ አቶ አበባየሁ ጌታ ፦
" ሊዲያ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ከተወሰደች በኋላ ከሕግ ውጪ ለ5 ቀናት ፍርድ ቤት ሳትቀርብ ታስራ ቆይታለች።
ከአምስት (5) ቀናት በኋላ ሃላባ መጀመሪያ ፍርድ ቤት ካለ ጠበቃ ጋር ቀርባ የ14 ቀናት ቀጥሮ ለምርመራ ከተሰጠ በኋላ ወደ ሃላባ ቁሊቶ ማረሚያ ቤት ተወስዳለች።
ይህ ድርጊት ከሕግ ጋር የሚጻረር ነው። ለአካለ መጠን ያልደረሰ ሰው በወንጀል ሲጠረጠር ከቤተሰቦቹ ጋር ቆይቶ ለምርመራ ሲፈልግ እንደሚጠራ በሕግ ተደንግጓል።
በተጠረጠረችበት ወንጀል #ጥፋተኛ ሆና ብትገኝ እንኳን የማረሚያ ቤት እስር እንደማይፈረድባት የወንጀል ሕጉ ያስቀምጣል።
በተሰጠው የጊዜ ቀጠሮ ላይ ለሃላባ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ተጠይቋል። ይግባኙም የታዳጊዋ አያያዝ እንዲሁም ለቀናት በእስር ላይ እንድትቆይ መደረጉ ተገቢ አይደለም የሚል ነው።
የሊዲያ ከሳሾች ጉዳት ደርሶብናል ያሉት ተማሪዎች ወላጆች ሲሆኑ ልጆቻችንን ላይ ባደረገችባቸው መተት/ድግምት አፍዝዛ ጉዳት አድርሳባቸዋለች የሚል ማመልከቻ አቅርበው ነው የተከሰሰችው።
ክሱ ተሰራ በተባለው መተት / ድግምት ተጎድተው ሕክምና ላይ የሚገኙ ተማሪዎች አሉ ይላል።
ሊዲያም ባለፈው አርብ አግኝተናት አናግረናት ነበር። በወቅቱም ንቅሳት ካለብሽ እናይሻለን በሚል እርቃኗን እንደፈተሿት ተናግራለች።
ሊዲያ እስሩ በተፈጸመባቸው የመጀመሪያዎቹ ቀናት ታለቅስ ነበር። አሁን መምህራን፣ የትምህርት ቤት ጓደኞቿ እና ሌሎች ሰዎች እየጠየቋት በመሆኑ በጥሩ ሞራል ላይ ትገኛለች።
በኢትዮጵያ ሕግ ድግምት ፣ ጥንቆላ፣ እኔ አውቅልሃለሁ ባይነት፣ መንፈስ መጥራት እና መሰል ወንጀሎች የሚዳኙበት ድንጋጌ አለ።
ሆኖም እነዚህ ወንጀሎች ጥቅምን ለማግኘት በማሰብ እና የሌላን ሰው ገንዘብ ለማግኘት የሚፈጸም እንጂ የግል ጥቅም ምን እንደሆነ በማታውቅ ታዳጊ ልጅ፣ ገንዘብ ያለበትን እጠቁማቸኋለሁ ባላለችበት ሁኔታ. . . [ሕጉ] ይህንን ሁኔታ ሊቀበለው አይችለም።
ሰዎችን ለማፍዘዝ የተለያዩ ዱቄት መሰል ምርቶችን ማምረት፣ መሸጥ እና ማሰተላለፍ ወንጀል ነው ሊዲያ ግን ይህንን ሁሉ አላደረገችም።
በማኅበራዊ ሚዲያዎች ለሕይወቷ የሚያሰጉ ዛቻዎች እና ማስፈራሪያዎች እየተዘዋወሩ ነው። በደረሰባት የሥነ ልቦና ጫና ምክንያት ከሥነ ልቦና ጫናው ተላቃ ትምህርቷን ትቀጥላለች ማለት ይከብዳል። "
👉 የሊዲያ አባት አቶ አበራ ሻሞሮ ፦
" ... የልጄ እስር የተወረወረ ዱብ ዕዳ ነው። ልጆቼ በትምህርታቸው ከአጠቃላይ ተማሪ ተሸላሚ ናቸው። እያጠኑ የሚያድሩ ናቸው።
የተቀረውን የትምህርት ጊዜ ሌላ አካባቢ እንዲጨርሱ እየሞከርኩ ነው።
ልጄም በማረሚያ ቤት ባነጋገርኩበት ወቅት መቼ ነው ከዚህ የምወጣው? ብላ ጠይዋኛለች። "
👉 ጉዳዩን በተመለከተ የሀላባ ዞን የቁሊቶ ከተማ አሰተዳደር ሰላም እና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ከቀናት በፊት በፌስቡክ ገጹ ይህን ብሏል ፦
" ... በከተማችን በሙሰሊም ሴት ተማሪዎች ላይ ድግምት አሲራለች ተብላ በታሰረች ተማሪ ሊዲያ አበራ በተያያዥ ጉዳይ በአቶ ናስር በሀላባ በዚህም ጉዳይ መሰል ተያያዥነት ያላቸው ግለሰቦችም ጭምር ተይዘው በምርመራ ሂደት በማረሚያ መኖራቸው ይታወቃል።
በታሰሩበት ኬዝ እንዳንድ አክቲቪስቶች ጉዳዩን ወደ ሓይማኖታዊ ለማስመሰል በማጦዝ የሚሞክሩ እንዳላችሁ በማሕበራዊ ሚዲያ እየታየ ያለው ሁኔታ በፖሊስ እና በምርመራ ባለሙያዎች ሂደቱ እየተጣራና ማንም በተጠረጠረበት ወንጀል ታሰሮ አንደሚጣራ የሚታወቅ ስለሆነ ሁሉም ማህበረሰብ በትዕግስት እንዲጠብቅ ስንል እናሳስባችኋለን።
#ይህንን_ተላልፎ የሚገኝ ማንኛውንም አካል በህግ የምንጠይቅ መሆኑን እናውቃለን። "
የመረጃ ምንጭ ፦ ቢቢሲ የአማርኛው አገልግሎት / የሀላባ ዞን የቁሊቶ ከተማ አሰተዳደር ሰላም እና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ናቸው።
@tikvahethiopia
#NEBE
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፥ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤን ያሰናከሉ የህግ አስፈጻሚ አካላት ላይ ፍትሕ ሚኒስቴር ክስ እንዲመሰርት ጠየቀ።
ቦርዱ ይህን የጠየቀው ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ ጋር በተያያዘ ከሰሞኑ ያጋጠሙ መስተጓጎሎችን በተመለከተ ዛሬ መግለጫ በሰጠበት ወቅት ነው።
ቦርዱ የፓርቲዎችን ጠቅላላ ጉባኤ ያሰናከሉ የህግ አስፈጻሚ አካላት ላይ ፍትሕ ሚኒስቴር ክስ እንዲመሰርት ከመጠየቅ ባለፈ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ስር የሚተዳደሩ ስብሰባ ቦታዎች እና አዳራሾች ለፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ ክፍት እንዲሆኑም ውሳኔ አሳልፏል።
በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ መሰረት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤያቸውን ቢያንስ በሶስት ዓመት አንድ ጊዜ ማካሄድ አለባቸው።
የፖለቲካ ፓርቲዎች ይህን ግዴታቸውን ለመፈጸም በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ወቅት መስተጓጎል እየገጠማቸው እንደሚገኝ ምርጫ ቦርድ ገልጿል።
ባለፈው እሁድ የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ እንዲሁም ከዛ ቀደም ብሎ የእናት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ መስተጓጎሉ ይታወሳል።
ከዚህ ባለፈ ምርጫ ቦርድ የጎጎት ለጉራጌ ሕዝብ አንድነት እና ፍትሕ ፓርቲ አስተባባሪዎች መጋቢት 3 የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባኤ ተካፍለው በማግስቱ መጋቢት 4 ቀን የጠቅላላ ጉባኤውን ሰነዶችን እንደያዙ 12ት ሰዎች በፌዴራል ፖሊስ ታስረው ወደ ደቡብ ክልል መወሰዳቸውንና ሁለቱ እስካሁን አለመፈታታቸውን አረጋግጦ እንዲፈቱ ጠይቋል።
የተፈፀመውን " ወንጀል " እንደ ተራ ጉዳይ እንደማይመለከተው ያስታወቀው ምርጫ ቦርድ ድርጊቱ " ፓርቲዎቹ ብቻ ሳይሆን ምርጫ ቦርድም እንዳይኖር የሚያደርግ ነው " ሲል ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።
መረጃው የኢትዮጵያ ኢንሳይደር እና ዶቼ ቨለ ነው።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፥ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤን ያሰናከሉ የህግ አስፈጻሚ አካላት ላይ ፍትሕ ሚኒስቴር ክስ እንዲመሰርት ጠየቀ።
ቦርዱ ይህን የጠየቀው ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ ጋር በተያያዘ ከሰሞኑ ያጋጠሙ መስተጓጎሎችን በተመለከተ ዛሬ መግለጫ በሰጠበት ወቅት ነው።
ቦርዱ የፓርቲዎችን ጠቅላላ ጉባኤ ያሰናከሉ የህግ አስፈጻሚ አካላት ላይ ፍትሕ ሚኒስቴር ክስ እንዲመሰርት ከመጠየቅ ባለፈ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ስር የሚተዳደሩ ስብሰባ ቦታዎች እና አዳራሾች ለፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ ክፍት እንዲሆኑም ውሳኔ አሳልፏል።
በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ መሰረት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤያቸውን ቢያንስ በሶስት ዓመት አንድ ጊዜ ማካሄድ አለባቸው።
የፖለቲካ ፓርቲዎች ይህን ግዴታቸውን ለመፈጸም በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ወቅት መስተጓጎል እየገጠማቸው እንደሚገኝ ምርጫ ቦርድ ገልጿል።
ባለፈው እሁድ የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ እንዲሁም ከዛ ቀደም ብሎ የእናት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ መስተጓጎሉ ይታወሳል።
ከዚህ ባለፈ ምርጫ ቦርድ የጎጎት ለጉራጌ ሕዝብ አንድነት እና ፍትሕ ፓርቲ አስተባባሪዎች መጋቢት 3 የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባኤ ተካፍለው በማግስቱ መጋቢት 4 ቀን የጠቅላላ ጉባኤውን ሰነዶችን እንደያዙ 12ት ሰዎች በፌዴራል ፖሊስ ታስረው ወደ ደቡብ ክልል መወሰዳቸውንና ሁለቱ እስካሁን አለመፈታታቸውን አረጋግጦ እንዲፈቱ ጠይቋል።
የተፈፀመውን " ወንጀል " እንደ ተራ ጉዳይ እንደማይመለከተው ያስታወቀው ምርጫ ቦርድ ድርጊቱ " ፓርቲዎቹ ብቻ ሳይሆን ምርጫ ቦርድም እንዳይኖር የሚያደርግ ነው " ሲል ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።
መረጃው የኢትዮጵያ ኢንሳይደር እና ዶቼ ቨለ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
ብሊንከን ከኢጋድ ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ጋር ተወያዩ።
የአሜሪካውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በአዲስ አበባ የስራ ጉብኝት ላይ ይገኛሉ።
በዚህም ጉብኝታቸው ከኢጋድ ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ጋር መወያየታቸው ታውቋል።
ውይይቱን በተመለከተ ዶ/ር ወርቅነህ ፤ አዲስ አበባ ውስጥ ከብሊንከን ጋር ተገናኝተው መወያያታቸውን ይኸው ውይይትም ካለፈው ዓመት የናይሮቢ ውይይት የቀጠለ መሆኑን ገልጸዋል።
በውይይቱ ወቅት ፤ ኢጋድ በቀጠናው ሰላም እና ደህንነት ላይ ያለው ወሳኝ ሚና አፅንኦት እንደተሰጠው እንዲሁም የኢጋድ-አሜሪካን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማጠናከርን ለማስቀጠል ቃል መገባቱን አመልክተዋል።
@tikvahethiopia
ብሊንከን ከኢጋድ ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ጋር ተወያዩ።
የአሜሪካውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በአዲስ አበባ የስራ ጉብኝት ላይ ይገኛሉ።
በዚህም ጉብኝታቸው ከኢጋድ ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ጋር መወያየታቸው ታውቋል።
ውይይቱን በተመለከተ ዶ/ር ወርቅነህ ፤ አዲስ አበባ ውስጥ ከብሊንከን ጋር ተገናኝተው መወያያታቸውን ይኸው ውይይትም ካለፈው ዓመት የናይሮቢ ውይይት የቀጠለ መሆኑን ገልጸዋል።
በውይይቱ ወቅት ፤ ኢጋድ በቀጠናው ሰላም እና ደህንነት ላይ ያለው ወሳኝ ሚና አፅንኦት እንደተሰጠው እንዲሁም የኢጋድ-አሜሪካን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማጠናከርን ለማስቀጠል ቃል መገባቱን አመልክተዋል።
@tikvahethiopia
#AddisAbaba
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የገቢዎች ቢሮ ኃላፊን ጨምሮ አዳዲስ ሹመቶችን መስጠቱ ተገልጿል።
ሹመቶቹ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባዔ እየተካሄደ በሚገኝበት ወቅት ነው የተሰጠው።
በዚህም ፡-
1. ዶክተር ጀማሉ ጀንበሩ - በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአረንጓዴ ውበትና ልማት ቢሮ ሃላፊ
2. አቶ ቢኒያም ምክሩ - የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ሃላፊ
3. አቶ አብርሃም ታደሰ - የአዲስ አበባ የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ቢሮ ሃላፊ
4. አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን - የፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ
5. አቶ አደም ኑሪ - የገቢዎች ቢሮ ሃላፊ
6. አቶ በላይ ደጀን - የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሃላፊ
7. ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ - የአዲስ አበባ የቴክኒክና ትምህርት ስልጠና ቢሮ ሃላፊ
8. አቶ ካሳሁን ጎንፋ - የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ዋና ስራ አስፈጻሚ
9. አቶ አያሌው መላኩ - የመሬት ይዞታ ማስለቀቅና አቤቱታ ሰሚ ጉባዔ ሃላፊ
10. ወ/ሮ እናታለም መለሰ - የአዲስ አበባ የኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ ሆነው ሹመታቸው በሙሉ ድምፅ ጸድቋል፡፡
ተሿሚዎቹ በምክር ቤት ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ ፈጽመዋል ።
#MayorOfficeofAddisAbaba
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የገቢዎች ቢሮ ኃላፊን ጨምሮ አዳዲስ ሹመቶችን መስጠቱ ተገልጿል።
ሹመቶቹ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባዔ እየተካሄደ በሚገኝበት ወቅት ነው የተሰጠው።
በዚህም ፡-
1. ዶክተር ጀማሉ ጀንበሩ - በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአረንጓዴ ውበትና ልማት ቢሮ ሃላፊ
2. አቶ ቢኒያም ምክሩ - የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ሃላፊ
3. አቶ አብርሃም ታደሰ - የአዲስ አበባ የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ቢሮ ሃላፊ
4. አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን - የፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ
5. አቶ አደም ኑሪ - የገቢዎች ቢሮ ሃላፊ
6. አቶ በላይ ደጀን - የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሃላፊ
7. ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ - የአዲስ አበባ የቴክኒክና ትምህርት ስልጠና ቢሮ ሃላፊ
8. አቶ ካሳሁን ጎንፋ - የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ዋና ስራ አስፈጻሚ
9. አቶ አያሌው መላኩ - የመሬት ይዞታ ማስለቀቅና አቤቱታ ሰሚ ጉባዔ ሃላፊ
10. ወ/ሮ እናታለም መለሰ - የአዲስ አበባ የኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ ሆነው ሹመታቸው በሙሉ ድምፅ ጸድቋል፡፡
ተሿሚዎቹ በምክር ቤት ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ ፈጽመዋል ።
#MayorOfficeofAddisAbaba
@tikvahethiopia
#ErmiasAyele
ኢትዮጵያዊው ሮም ላይ በባዶ እግሩ ሊሮጥ ነው።
ከቀናት በኃላ (እሁድ) የ2023 የሮም ማራቶን ይካሄዳል።
በዚህም ማራቶን ታሪክ ራሱን ይደግማል የተባለ ሲሆን ኢትዮጵያዊው የባዶ እግር ሯጭ እንዲሁም ለረጅም አመታት በኢትዮጵያ ታላቁ ሩጫ ቁልፍ ሰው (ዳይሬክተር) በመሆን የሰራው የ45 ዓመቱ ኤርሚያስ አየለ ሙሉ ማራቶን በባዶ እግሩ ይሮጣል።
ኤርሚያስ አየለ ይህንን የሚያደርገው ለኢትዮጵያው ታላቅ አትሌት አበበ ቢቂላ ክብር እንዲሁም ለሀገር ገፅታ ግንባታ ሲል ነው።
" አበበ ቢቂላ በኦሎምፒክ ጨዋታዎች የወርቅ ሜዳሊያ በማግኘት የመጀመሪያው ጥቁር በመሆኑ ለኢትዮጵያውያን አትሌቶች ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ ለአፍራካውያን ስኬት መሰረት ጥሏል " የሚለው ኤርሚያስ " ሆኖም ግን ለሰራው ታሪክ የሚገባውን ያህል እውቅና እንዳላገኘ ይሰማኝ ነበር " ብሏል።
ኤርሚያስ ፤ የአትሌት አበበ ቢቃላ ታሪክ ሁሌም እንደሚያነሳሳው ገልጾ ለዚህም እሱ ለአትሌቲክስ እና ለኢትዮጵያ ላደረገው ነገር ክብር እና ምስጋና ለመስጠት በተመሳሳይ ቦታ እና በተመሳሳይ መንገድ ታሪክ በሰራበት ቦታ በባዶ እግሩ እንደሚሮጥ አስረድቷል።
የሮም ውድድሩ ቀላል እንደማይሆንና ስሜታዊም የሚያደርግ እንደሆነ የገለፀው ኤርሚያስ " ይህን ትልቅ ትርጉም ያለውና ታሪካዊ ውድድር ለማድረግ ዝግጅቴን አጠናቅቄያለሁ " ብሏል።
ኤርሚያስ ውድድሩን ከ3:30 እስከ 4:00 ባለው አጠናቅቃለሁ ብሎ እንደሚጠብቅ ገልጾ የሮሙ ማራቶን በመጪዎቹ 18 ወራት ከአበበ ቢቂላ ጋር በአንድም ይሁን በሌላ መልኩ ግንኙነት ባላቸው በአቴንስ ፣ ቶኪዮ እና ፓሪስ ማራቶን በባዶ እግር ለሚያደርገው የማራቶን ሩጫ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግለት አመልክቷል።
የባዶ እግር የማራቶን ሩጫው አትሌት አበበ ቢቂላ ለሰራው ታሪክ ክብር ለመስጠት ከማድረግ ባለፈ ለሀገር ገፅታ ግንባታ ያለው አስታዋፆ ከፍተኛ ስለመሆኑ ገልጿል።
ኤርሚያስ ከዚህ ቀደም የታላቁ ሩጫን ሙሉውን ሁለት ጊዜ ፤ የሀዋሳ ግማሽ ማራቶን ሙሉ በባዶ እግሩ የሮጠ ሲሆን ለእሁዱ የሮም ማራቶን ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል።
ኤርሚያስ አየለ በሮም ስለሚያደርገው የባዶ እግር የማራቶን ሩጫ የውጭ መገናኛ ብዙሃን ያዘጋጁት ዘገባዎች ፦
https://www.aipsmedia.com/aips/pages/articles/2023/33598.html
https://www.aipsmedia.com/aips/pages/articles/2023/33598.html
Credit 👇
#ኤልያስመሰረት #ሀይለእግዚአብሔር_አድሃኖም
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያዊው ሮም ላይ በባዶ እግሩ ሊሮጥ ነው።
ከቀናት በኃላ (እሁድ) የ2023 የሮም ማራቶን ይካሄዳል።
በዚህም ማራቶን ታሪክ ራሱን ይደግማል የተባለ ሲሆን ኢትዮጵያዊው የባዶ እግር ሯጭ እንዲሁም ለረጅም አመታት በኢትዮጵያ ታላቁ ሩጫ ቁልፍ ሰው (ዳይሬክተር) በመሆን የሰራው የ45 ዓመቱ ኤርሚያስ አየለ ሙሉ ማራቶን በባዶ እግሩ ይሮጣል።
ኤርሚያስ አየለ ይህንን የሚያደርገው ለኢትዮጵያው ታላቅ አትሌት አበበ ቢቂላ ክብር እንዲሁም ለሀገር ገፅታ ግንባታ ሲል ነው።
" አበበ ቢቂላ በኦሎምፒክ ጨዋታዎች የወርቅ ሜዳሊያ በማግኘት የመጀመሪያው ጥቁር በመሆኑ ለኢትዮጵያውያን አትሌቶች ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ ለአፍራካውያን ስኬት መሰረት ጥሏል " የሚለው ኤርሚያስ " ሆኖም ግን ለሰራው ታሪክ የሚገባውን ያህል እውቅና እንዳላገኘ ይሰማኝ ነበር " ብሏል።
ኤርሚያስ ፤ የአትሌት አበበ ቢቃላ ታሪክ ሁሌም እንደሚያነሳሳው ገልጾ ለዚህም እሱ ለአትሌቲክስ እና ለኢትዮጵያ ላደረገው ነገር ክብር እና ምስጋና ለመስጠት በተመሳሳይ ቦታ እና በተመሳሳይ መንገድ ታሪክ በሰራበት ቦታ በባዶ እግሩ እንደሚሮጥ አስረድቷል።
የሮም ውድድሩ ቀላል እንደማይሆንና ስሜታዊም የሚያደርግ እንደሆነ የገለፀው ኤርሚያስ " ይህን ትልቅ ትርጉም ያለውና ታሪካዊ ውድድር ለማድረግ ዝግጅቴን አጠናቅቄያለሁ " ብሏል።
ኤርሚያስ ውድድሩን ከ3:30 እስከ 4:00 ባለው አጠናቅቃለሁ ብሎ እንደሚጠብቅ ገልጾ የሮሙ ማራቶን በመጪዎቹ 18 ወራት ከአበበ ቢቂላ ጋር በአንድም ይሁን በሌላ መልኩ ግንኙነት ባላቸው በአቴንስ ፣ ቶኪዮ እና ፓሪስ ማራቶን በባዶ እግር ለሚያደርገው የማራቶን ሩጫ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግለት አመልክቷል።
የባዶ እግር የማራቶን ሩጫው አትሌት አበበ ቢቂላ ለሰራው ታሪክ ክብር ለመስጠት ከማድረግ ባለፈ ለሀገር ገፅታ ግንባታ ያለው አስታዋፆ ከፍተኛ ስለመሆኑ ገልጿል።
ኤርሚያስ ከዚህ ቀደም የታላቁ ሩጫን ሙሉውን ሁለት ጊዜ ፤ የሀዋሳ ግማሽ ማራቶን ሙሉ በባዶ እግሩ የሮጠ ሲሆን ለእሁዱ የሮም ማራቶን ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል።
ኤርሚያስ አየለ በሮም ስለሚያደርገው የባዶ እግር የማራቶን ሩጫ የውጭ መገናኛ ብዙሃን ያዘጋጁት ዘገባዎች ፦
https://www.aipsmedia.com/aips/pages/articles/2023/33598.html
https://www.aipsmedia.com/aips/pages/articles/2023/33598.html
Credit 👇
#ኤልያስመሰረት #ሀይለእግዚአብሔር_አድሃኖም
@tikvahethiopia
#ብርሃን_ባንክ
በሆቴሎች፤ በሱፐርማርኬቶች እና በቅርንጫፎቻችን በሚገኙት የፖስ ማሽኖቻችን የቪዛና ማስተር ካርድዎን ተጠቅመው ግብይትዎን ያቅልሉ፡፡
አዳዲስ እና ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ !
Facebook: https://www.facebook.com/berhanbanksc
Telegram: https://t.iss.one/berhanbanksc
Instagram: https://www.instagram.com/berhanbanksc/
Twitter: https://twitter.com/berhanbanksc
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/76151001
YouTube: https://www.youtube.com/channel/UCvOxWe439dzMSvNnMrjcYVQ
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ስራችን!
በሆቴሎች፤ በሱፐርማርኬቶች እና በቅርንጫፎቻችን በሚገኙት የፖስ ማሽኖቻችን የቪዛና ማስተር ካርድዎን ተጠቅመው ግብይትዎን ያቅልሉ፡፡
አዳዲስ እና ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ !
Facebook: https://www.facebook.com/berhanbanksc
Telegram: https://t.iss.one/berhanbanksc
Instagram: https://www.instagram.com/berhanbanksc/
Twitter: https://twitter.com/berhanbanksc
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/76151001
YouTube: https://www.youtube.com/channel/UCvOxWe439dzMSvNnMrjcYVQ
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ስራችን!
#አሚጎስ_ብድር_እና_ቁጠባ
ንግድዎን በፍጥነት ለማሳደግ፣
በአጭር ጊዜ የሚደርስ አስቸኳይ ብድር፣
ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችንን በዚህ ሊንክ ይቀላቀሉ፡ https://t.iss.one/amigossacco
ንግድዎን በፍጥነት ለማሳደግ፣
በአጭር ጊዜ የሚደርስ አስቸኳይ ብድር፣
ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችንን በዚህ ሊንክ ይቀላቀሉ፡ https://t.iss.one/amigossacco
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ብሊንከን ከኢጋድ ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ጋር ተወያዩ። የአሜሪካውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በአዲስ አበባ የስራ ጉብኝት ላይ ይገኛሉ። በዚህም ጉብኝታቸው ከኢጋድ ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ጋር መወያየታቸው ታውቋል። ውይይቱን በተመለከተ ዶ/ር ወርቅነህ ፤ አዲስ አበባ ውስጥ ከብሊንከን ጋር ተገናኝተው መወያያታቸውን ይኸው ውይይትም ካለፈው ዓመት የናይሮቢ ውይይት የቀጠለ…
#Update
" በኢትዮጵያ እና አሜሪካ መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ስምምነት ላይ ተደርሷል " - የጠ/ሚ ፅ/ቤት
ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ቢንከንን በፅ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ይህን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ባወጣው መረጃ ውይይቱ በተለያዩ የሀገር ውስጥ፣ ቀጣናዊ እና የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር።
በውይይቱ በኢትዮጵያ እና አሜሪካ መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ስምምነት ላይ መደረሱን ገልጿል።
ኢትዮጵያ በሰላም ስምምነቱ ላይ እያስመዘገበች ያለችው ስኬት ተቀባይነት አግኝቷልም ብሏል።
በኢኮኖሚው፣ በልማት ጥረቶች፣ በተለይ በግብርናና በቀጣናዊ መረጋጋት ላይ ያሉ ጉዳዮችም ትኩረት እንደተሰጠባቸው ፅ/ቤቱ አመልክቷል።
@tikvahethiopia
" በኢትዮጵያ እና አሜሪካ መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ስምምነት ላይ ተደርሷል " - የጠ/ሚ ፅ/ቤት
ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ቢንከንን በፅ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ይህን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ባወጣው መረጃ ውይይቱ በተለያዩ የሀገር ውስጥ፣ ቀጣናዊ እና የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር።
በውይይቱ በኢትዮጵያ እና አሜሪካ መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ስምምነት ላይ መደረሱን ገልጿል።
ኢትዮጵያ በሰላም ስምምነቱ ላይ እያስመዘገበች ያለችው ስኬት ተቀባይነት አግኝቷልም ብሏል።
በኢኮኖሚው፣ በልማት ጥረቶች፣ በተለይ በግብርናና በቀጣናዊ መረጋጋት ላይ ያሉ ጉዳዮችም ትኩረት እንደተሰጠባቸው ፅ/ቤቱ አመልክቷል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አብን አብን የፌዴራል መንግስቱ/ገዢው ብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ከንቲባን ከስልጣን እንዲያስነሳ እና ለፍርድ እንዲያቀርብ ጠየቀ። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ፓርቲ ( #አብን ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዛሬ ለምክር ቤት ያቀረቡትን ሪፖርት አጥብቆ አውግዟል። ፓርቲው ከንቲባ አዳነች አበቤ ዛሬ ለአዲስ አበባ ከተማ ም/ ቤት ባቀረቡት ሪፖርት " ከአንዳንድ ክልሎች የሚደረገው ከፍተኛ ፍልሰት…
#Update
እናት፣ መኢአድ እና ኢሕአፓ ፓርቲዎች ከትላንቱ የአዲስ አበባ ምክር ቤት የከንቲባ አዳነች አቤቤ ሪፖርት ጋር በተያያዘ ዛሬ የጋራ መግለጫ አውጥተዋል።
በመግለጫቸው ላይ ፤ " ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀስ አልፎም በመረጡት ቦታ የመኖር መብት በሕገ መንግሥቱ ለዜጎች የተሰጣቸው መብት እንጂ አንዳንድ ባለስልጣናት ደስ ሲላቸው የሚቸሩት ካልፈለጉ ደግሞ የሚነፍጉት ጉዳይ አይደለም " ብለዋል።
ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ ከተማ በሚጓዙ መንገደኞች ላይ እናቶቻችን ጨምሮ በተለያዩ ጊዜያት ሰበባ ሰበብ እየተፈለገ ሲፈጸም የነበረው ማዋከብ፣ እንግልትና ማጉላላት ከነገ ዛሬ መሻሻል ይታይበታል ተብሎ ተስፋ ሲደረግ ይባስ ብሎ “ከአንዳንድ ክልሎች ወደ አዲስ አበባ የሚደረገው ከፍተኛ ፍልሰት መንግሥትን በመጣል በኃይል ስልጣን ለመቆጣጠር ያለመ ነው” በሚል የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ በቀን 5/07/2015 ዓ.ም ለምክር ቤት ባቀረቡት ሪፖርት ላይ የገለጹበት መንገድ ያለፈውን ስህተት ከማረም ይልቅ የዜጎችን ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀስ መብት የሚነፍግ፣ በከፍተኛ ሴራና ፍረጃ ለበለጠው የዘር ፍጅት የሚያመቻችና ዜጎችን የማሸማቀቅ አካል ነው ሲሉ ፓርቲዎቹ ገልፀዋል።
" በሌላ በኩል ፥ ትናንትና ካህን በጥፊ ሲመቱ፣ ሕጻናትንና ሴቶችን ሲያዋክቡና በማንነታቸው ሲያሸማቅቁ፣ ሲሰውሩ፣ ሲገድሉና ሲዘርፉ ለኖሩ ኃይሎች ሽፋን የመስጠትና ጥብቅና የመቆም አካል አድርገን እንወስደዋለን። " ሲሉ ፓርቲዎቹ በጋራ መግለጫቸው ገልፀዋል።
" ድርጊቱ በ ' ኦሮሚያ ብልጽግና ' በንግግርም በተግባርም በተጠናና መዋቅራዊ በሆነ ሁኔታ እንደሚፈጸም ዐቢይ ማረጋገጫና በቀጣይም ሰቆቃና ማወከቡ ቢብስ እንጂ እንደማይረግብ ጉልህ ማሳያ ነው "ም ብለዋል።
ፓርቲዎቹ ፤ " ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ አዲስ አበባ እንዳይገቡ የሚከለከሉ ዜጎቻችን ጉዳይ የሌላ ሀገር ድንበር አቋርጠው በሕገወጥ መንገድ ለመግባት የሚሞክሩ መንገደኞች እንጂ ከሀገራቸው አንድ ክፍል አባቶቻቸው ወደአቀኑላቸው ዋና ከተማቸው የሚደረግ ሕጋዊ እንቅስቃሴ አይመስልም " ሲሉም በመግለጫው ላይ አስፍረዋል።
በሌላው ዓለም ቢሆን እጅግ መርዘኛ እና ፍጅት ቀስቃሽ ንግግሮችና ተናጋሪዎች ተገቢው እርምት በቶሎ በተሰጣቸው ነበር ያሉት ፓርቲዎቹ በእኛ ሀገር ኹኔታ ሕጋዊነት ሳይሆን ሕገ ወጥነት፣ “የእኛ” ሳይሆን “ለእኔ ብቻ” ባዮች፣ ተጠያቂነት ሳይሆን ተረኝነት የሰፈነበት በመሆኑ ለዚህ አልታደለንም ብለዋል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድነት ሕግና ሥርዓት ሰፍኖ አጥፊዎች በፍትሕ አደባባይ እንዲቀርቡ የበኩሉን እንዲወጣ፣ እንዲህ ላሉ ከፋፋይ ንግግሮችም ጆሮ ባለመስጠት አንድነቱን እንዲያጸና ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
(ሙሉ መግለጫቸው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
እናት፣ መኢአድ እና ኢሕአፓ ፓርቲዎች ከትላንቱ የአዲስ አበባ ምክር ቤት የከንቲባ አዳነች አቤቤ ሪፖርት ጋር በተያያዘ ዛሬ የጋራ መግለጫ አውጥተዋል።
በመግለጫቸው ላይ ፤ " ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀስ አልፎም በመረጡት ቦታ የመኖር መብት በሕገ መንግሥቱ ለዜጎች የተሰጣቸው መብት እንጂ አንዳንድ ባለስልጣናት ደስ ሲላቸው የሚቸሩት ካልፈለጉ ደግሞ የሚነፍጉት ጉዳይ አይደለም " ብለዋል።
ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ ከተማ በሚጓዙ መንገደኞች ላይ እናቶቻችን ጨምሮ በተለያዩ ጊዜያት ሰበባ ሰበብ እየተፈለገ ሲፈጸም የነበረው ማዋከብ፣ እንግልትና ማጉላላት ከነገ ዛሬ መሻሻል ይታይበታል ተብሎ ተስፋ ሲደረግ ይባስ ብሎ “ከአንዳንድ ክልሎች ወደ አዲስ አበባ የሚደረገው ከፍተኛ ፍልሰት መንግሥትን በመጣል በኃይል ስልጣን ለመቆጣጠር ያለመ ነው” በሚል የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ በቀን 5/07/2015 ዓ.ም ለምክር ቤት ባቀረቡት ሪፖርት ላይ የገለጹበት መንገድ ያለፈውን ስህተት ከማረም ይልቅ የዜጎችን ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀስ መብት የሚነፍግ፣ በከፍተኛ ሴራና ፍረጃ ለበለጠው የዘር ፍጅት የሚያመቻችና ዜጎችን የማሸማቀቅ አካል ነው ሲሉ ፓርቲዎቹ ገልፀዋል።
" በሌላ በኩል ፥ ትናንትና ካህን በጥፊ ሲመቱ፣ ሕጻናትንና ሴቶችን ሲያዋክቡና በማንነታቸው ሲያሸማቅቁ፣ ሲሰውሩ፣ ሲገድሉና ሲዘርፉ ለኖሩ ኃይሎች ሽፋን የመስጠትና ጥብቅና የመቆም አካል አድርገን እንወስደዋለን። " ሲሉ ፓርቲዎቹ በጋራ መግለጫቸው ገልፀዋል።
" ድርጊቱ በ ' ኦሮሚያ ብልጽግና ' በንግግርም በተግባርም በተጠናና መዋቅራዊ በሆነ ሁኔታ እንደሚፈጸም ዐቢይ ማረጋገጫና በቀጣይም ሰቆቃና ማወከቡ ቢብስ እንጂ እንደማይረግብ ጉልህ ማሳያ ነው "ም ብለዋል።
ፓርቲዎቹ ፤ " ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ አዲስ አበባ እንዳይገቡ የሚከለከሉ ዜጎቻችን ጉዳይ የሌላ ሀገር ድንበር አቋርጠው በሕገወጥ መንገድ ለመግባት የሚሞክሩ መንገደኞች እንጂ ከሀገራቸው አንድ ክፍል አባቶቻቸው ወደአቀኑላቸው ዋና ከተማቸው የሚደረግ ሕጋዊ እንቅስቃሴ አይመስልም " ሲሉም በመግለጫው ላይ አስፍረዋል።
በሌላው ዓለም ቢሆን እጅግ መርዘኛ እና ፍጅት ቀስቃሽ ንግግሮችና ተናጋሪዎች ተገቢው እርምት በቶሎ በተሰጣቸው ነበር ያሉት ፓርቲዎቹ በእኛ ሀገር ኹኔታ ሕጋዊነት ሳይሆን ሕገ ወጥነት፣ “የእኛ” ሳይሆን “ለእኔ ብቻ” ባዮች፣ ተጠያቂነት ሳይሆን ተረኝነት የሰፈነበት በመሆኑ ለዚህ አልታደለንም ብለዋል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድነት ሕግና ሥርዓት ሰፍኖ አጥፊዎች በፍትሕ አደባባይ እንዲቀርቡ የበኩሉን እንዲወጣ፣ እንዲህ ላሉ ከፋፋይ ንግግሮችም ጆሮ ባለመስጠት አንድነቱን እንዲያጸና ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
(ሙሉ መግለጫቸው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia