#DigitalLottery
የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመሆን የሚያዘጋጀው የአድማስ ዲጂታል ሎተሪ ሽልማት ማደጉን አስታወቀ።
3 ብር የነበረው የአንድ ዕጣ ቁጥር ዋጋ 5 ብር ማደረጉም ተመላክቷል።
በ1ኛ ዕጣ 1,500,000 ብር ያሸልም የነበረው የአድማስ ዲጂታል ሎተሪ የ1ኛው ዕጣ ወደ 3,000,000 ብር መደጉ 2ኛው ዕጣ ደግሞ 1,200,000 ብር፣ 3ኛ ዕጣ 800,000 ብር መደረጉ ተመላክቷል።
አዲሱ የአድማስ ዲጂታል ሎተሪ ዕጣ ድልድል ዝርዝር የሚከተለው ነው ፦
1ኛ ዕጣ 👉 3,000,000
2ኛ ዕጣ 👉 1,200,000
3ኛ ዕጣ 👉 800,000
4ኛ ዕጣ 👉 400,000
5ኛ እጣ 👉 250,000
6ኛ ዕጣ 👉 150,000
7ኛ ዕጣ 👉 100,000
8ኛ እጣ 👉 50,000
9ኛ እጣ 👉 30,000
10ኛ እጣ 👉 25,000
በሌላ በኩል ፤ ሎተሪ አስተዳደሩ የ008- መደብ ሽያጭ ዛሬ የካቲት 21 ቀን 2015 ከለሊቱ 6 ሰዓት እንደሚያበቀ የገለፀ ሲሆን ከዚህ ሰዓት ጀምሮ የቀጣይ ወር ዕጣ ይጀመራል ብሏል።
የ008- መደብ ዕጣ የካቲት 23 ቀን 2015 በህዝብ ፊት ይወጣል ሲልም አሳውቋል።
አዲሱ የዕጣ ድልድል የሚጀምረው ከቀጣይ ወር / ከየካቲት 21 ቀን 2015 ከለሊቱ 6ሰዓት ላይ ከሚጀምረው ዕጣ ይሆናል ተብሏል።
@tikvahethiopia
የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመሆን የሚያዘጋጀው የአድማስ ዲጂታል ሎተሪ ሽልማት ማደጉን አስታወቀ።
3 ብር የነበረው የአንድ ዕጣ ቁጥር ዋጋ 5 ብር ማደረጉም ተመላክቷል።
በ1ኛ ዕጣ 1,500,000 ብር ያሸልም የነበረው የአድማስ ዲጂታል ሎተሪ የ1ኛው ዕጣ ወደ 3,000,000 ብር መደጉ 2ኛው ዕጣ ደግሞ 1,200,000 ብር፣ 3ኛ ዕጣ 800,000 ብር መደረጉ ተመላክቷል።
አዲሱ የአድማስ ዲጂታል ሎተሪ ዕጣ ድልድል ዝርዝር የሚከተለው ነው ፦
1ኛ ዕጣ 👉 3,000,000
2ኛ ዕጣ 👉 1,200,000
3ኛ ዕጣ 👉 800,000
4ኛ ዕጣ 👉 400,000
5ኛ እጣ 👉 250,000
6ኛ ዕጣ 👉 150,000
7ኛ ዕጣ 👉 100,000
8ኛ እጣ 👉 50,000
9ኛ እጣ 👉 30,000
10ኛ እጣ 👉 25,000
በሌላ በኩል ፤ ሎተሪ አስተዳደሩ የ008- መደብ ሽያጭ ዛሬ የካቲት 21 ቀን 2015 ከለሊቱ 6 ሰዓት እንደሚያበቀ የገለፀ ሲሆን ከዚህ ሰዓት ጀምሮ የቀጣይ ወር ዕጣ ይጀመራል ብሏል።
የ008- መደብ ዕጣ የካቲት 23 ቀን 2015 በህዝብ ፊት ይወጣል ሲልም አሳውቋል።
አዲሱ የዕጣ ድልድል የሚጀምረው ከቀጣይ ወር / ከየካቲት 21 ቀን 2015 ከለሊቱ 6ሰዓት ላይ ከሚጀምረው ዕጣ ይሆናል ተብሏል።
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት
የካቲት 23/2015 ዓ.ም የሚከበረውን የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ምክንያት በማድረግ ማለዳ 12 ሰዓት ላይ 21 ጊዜ መድፍ እንደሚተኮስ የኢ.ፌ.ድ.ሪ መከላከያ ሚኒስቴር አሳውቋል።
@tikvahethiopia
የካቲት 23/2015 ዓ.ም የሚከበረውን የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ምክንያት በማድረግ ማለዳ 12 ሰዓት ላይ 21 ጊዜ መድፍ እንደሚተኮስ የኢ.ፌ.ድ.ሪ መከላከያ ሚኒስቴር አሳውቋል።
@tikvahethiopia
#አዲስ_አበባ #የሚዘጉ_መንገዶች
የካቲት 23 ቀን 2015 ዓ/ም የሚከበረው 127ኛው የአድዋ ድል በዓልን ምክንያት በማድረግ የበዓሉ ስነ ስርዓት በሚካሄድባቸው አካባቢዎች የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥም የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
በዕለቱ በ #ምኒሊክ_አደባባይ በመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ለበዓሉ መታሰቢያ ጉንጉን አበባ በማስቀመጥ የአከባበር ስነ ስርዓቱ እንደሚጀምር ፖሊስ የገለፀ ሲሆን ከዚያ በመቀጠል ወደ አድዋ ድልድይ የእግር ጉዞ እንደሚደረግና ዋናው ስነ ስርዓት በመስቀል አደባባይ እንደሚከናወን አሳውቋል።
በመሆኑም ፦
👉 በምኒሊክ አደባባይ በሚከናወነው የአከባበር ስነ ስርዓት ምክንያት ፦
• ከሰሜን ሆቴል ትራፊክ መብራት ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከዮሀንስ መብራት ወደ አቡነ ጴጥሮስ አደባባይ
• ከአፍንጮ በር ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከጊዮርጊስ ቴሌ ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከራስ መኮንን ድልድይ ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከራስ መኮንን ድልድይ ወደ ደጎል አደባባይ
• ከሀገር ፍቅር መታጠፊያ ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከብሪቲሽ ካውንስል ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከሲኒማ አምፒር ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከእሪ በከንቱ ( እሪ በስራ) ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከቴዎድሮስ አደባባይ ወደ ምኒሊክ አደባባይ
• ከአራዳ ህንፃ ወደ ወደ ምኒሊክ አደባባይ
• ከአቡነ ጴጥሮስ አደባባይ ወደ ወደ ምኒሊክ አደባባይ
• ከሰባራ ባቡር ቶታል ወደ ጊዮርጊስ ቴሌ መስቀለኛ
• ከዳትሰን ሰፈር መገንጠያ ወደ ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን የሚወስዱ መንገዶች ከንጋቱ 11 ሰዓት ጀምሮ ስነ ስርዓቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚደረጉ ይሆናል ፡፡
👉 ከምኒሊክ አደባባይ ወደ አደዋ ድልድይ የእግር ጉዞ በማድረግ በአድዋ ድልድይ የሚከናወነው ስነ ስርኣት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ፦
• ከእንግሊዝ ኤምባሲ ትራፊክ መብራት ወደ አድዋ ድልድይ
• ከፈረስ ቤት ኮንደሚኒየም መታጠፊያ ወደ አድዋ ድልድይ
• ከምስራቅ መገንጠያ ወደ ምስራቅ አጠቃላይ
• ከሴፍቲ መብራት ወደ ምስራቅ አጠቃላይ
• ከ22 አደባባይ ወደ ዘሪሁን ህንፃ
• ከዘሪሁን ህንፃ ወደ አድዋ ድልድይ
• ከቺቺኒያ ወደ ወደ አድዋ ድልድይ
• ከካዛንቺስ ቶታል ወደ አቧሬ
• ከድሮው ሰንደይ ማርኬት ወደ ሴቶች አደባባይ
• ከሴቶች አደባባይ ወደ አድዋ ድልድይ
• ከአቧሬ ጀርመን አደባባይ ወደ ሴቶች አደባባይ ያሉት መንገዶችን ከንጋቱ 11 ጀምሮ ለተሽከርካሪ #ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
👉 በመስቀል አደባባይ የሚከናወነው የበዓሉ አከባበር ስነ ስርዓት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ፦
• ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ
• ከዘሪሁን ህንፃ ወደ መስቀል አደባባይ
• ከአትላስ መብራት ወደ ኡራኤል
• ከፒኮክ ትራፊክ መብራት ወደ ኡራኤል
• ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ ኡራኤል
• ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ ባምቢስ
• ከጥላሁን አደባባይ( መሿለኪያ) ወደ ሴንጆሴፍ ት/ቤት
• ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ
• በቂርቆስ አዲሱ መንገድ ወደ ቂርቆስ ቤ/ክርስቲያን መስቀለኛ
• ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ ለገሀር
• አልሳምጨለለቅ ህንፃ ወደ ለገሀር
• ከገነት መብራት ወደ ለገሀር
• ከጠማማ ፎቅ (ገነት ሆቴል) ወደ ሜክሲኮ
• ከሱዳን ኤምባሲ (ጠማማ ፎቅ) ወደ ሜክሲኮ
• ከአፍሪካ ህብረት ትራፊክ መብራት ወደ ሜክሲኮ
• ከዲአፍሪክ ሆቴል ወደ ሜክሲኮ
• ከሰንጋ ተራ 40/60 ኮንዶሚኒየም ወደ ለገሐር
• ከጎማ ቁጠባ ወደ ብሔራዊ ቲያትር
• ከሜትሮሎጂ ወደ ፖስታ ቤት መብራት
• ከጥቁር አንበሳ ሼል ወደ ኢምግሬሽን መብራት
• ከጎላ ሚካኤል መስቀለኛ ወደ ኢምግሬሽን
• ከቴዎድሮስ አደባባይ ወደ ኢምግሬሽን መብራት(ፖስታ ቤት)
• ከንግድ ማተሚያ ወደ ኦርማ ጋራዥ
• ከሚያዚያ 27 አደባባይ (4 ኪሎ) ወደ ፓርላማ መብራት
• ከጥይት ቤት ወደ ግቢ ገብርኤል
• ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ ቶታል የሚወስዱ መንገዶች ከንጋቱ 11 ጀምሮ ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረጉ ፖሊስ ገልጿል።
ፖሊስ አሽከርካሪዎች #ሌሎች_አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ መልዕክት አስተላልፏል።
ከነገ እሮብ የካቲት 22 ቀን 2015 ዓ.ም ምሽት ጀምሮ በተገለጹት መንገዶች ላይ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ሰዓታት ተሸከርካሪን #አቁሞ_መሄድ የተከለከለ ነው ተብሏል።
@tikvahethiopia
የካቲት 23 ቀን 2015 ዓ/ም የሚከበረው 127ኛው የአድዋ ድል በዓልን ምክንያት በማድረግ የበዓሉ ስነ ስርዓት በሚካሄድባቸው አካባቢዎች የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥም የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
በዕለቱ በ #ምኒሊክ_አደባባይ በመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ለበዓሉ መታሰቢያ ጉንጉን አበባ በማስቀመጥ የአከባበር ስነ ስርዓቱ እንደሚጀምር ፖሊስ የገለፀ ሲሆን ከዚያ በመቀጠል ወደ አድዋ ድልድይ የእግር ጉዞ እንደሚደረግና ዋናው ስነ ስርዓት በመስቀል አደባባይ እንደሚከናወን አሳውቋል።
በመሆኑም ፦
👉 በምኒሊክ አደባባይ በሚከናወነው የአከባበር ስነ ስርዓት ምክንያት ፦
• ከሰሜን ሆቴል ትራፊክ መብራት ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከዮሀንስ መብራት ወደ አቡነ ጴጥሮስ አደባባይ
• ከአፍንጮ በር ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከጊዮርጊስ ቴሌ ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከራስ መኮንን ድልድይ ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከራስ መኮንን ድልድይ ወደ ደጎል አደባባይ
• ከሀገር ፍቅር መታጠፊያ ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከብሪቲሽ ካውንስል ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከሲኒማ አምፒር ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከእሪ በከንቱ ( እሪ በስራ) ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከቴዎድሮስ አደባባይ ወደ ምኒሊክ አደባባይ
• ከአራዳ ህንፃ ወደ ወደ ምኒሊክ አደባባይ
• ከአቡነ ጴጥሮስ አደባባይ ወደ ወደ ምኒሊክ አደባባይ
• ከሰባራ ባቡር ቶታል ወደ ጊዮርጊስ ቴሌ መስቀለኛ
• ከዳትሰን ሰፈር መገንጠያ ወደ ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን የሚወስዱ መንገዶች ከንጋቱ 11 ሰዓት ጀምሮ ስነ ስርዓቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚደረጉ ይሆናል ፡፡
👉 ከምኒሊክ አደባባይ ወደ አደዋ ድልድይ የእግር ጉዞ በማድረግ በአድዋ ድልድይ የሚከናወነው ስነ ስርኣት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ፦
• ከእንግሊዝ ኤምባሲ ትራፊክ መብራት ወደ አድዋ ድልድይ
• ከፈረስ ቤት ኮንደሚኒየም መታጠፊያ ወደ አድዋ ድልድይ
• ከምስራቅ መገንጠያ ወደ ምስራቅ አጠቃላይ
• ከሴፍቲ መብራት ወደ ምስራቅ አጠቃላይ
• ከ22 አደባባይ ወደ ዘሪሁን ህንፃ
• ከዘሪሁን ህንፃ ወደ አድዋ ድልድይ
• ከቺቺኒያ ወደ ወደ አድዋ ድልድይ
• ከካዛንቺስ ቶታል ወደ አቧሬ
• ከድሮው ሰንደይ ማርኬት ወደ ሴቶች አደባባይ
• ከሴቶች አደባባይ ወደ አድዋ ድልድይ
• ከአቧሬ ጀርመን አደባባይ ወደ ሴቶች አደባባይ ያሉት መንገዶችን ከንጋቱ 11 ጀምሮ ለተሽከርካሪ #ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
👉 በመስቀል አደባባይ የሚከናወነው የበዓሉ አከባበር ስነ ስርዓት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ፦
• ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ
• ከዘሪሁን ህንፃ ወደ መስቀል አደባባይ
• ከአትላስ መብራት ወደ ኡራኤል
• ከፒኮክ ትራፊክ መብራት ወደ ኡራኤል
• ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ ኡራኤል
• ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ ባምቢስ
• ከጥላሁን አደባባይ( መሿለኪያ) ወደ ሴንጆሴፍ ት/ቤት
• ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ
• በቂርቆስ አዲሱ መንገድ ወደ ቂርቆስ ቤ/ክርስቲያን መስቀለኛ
• ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ ለገሀር
• አልሳምጨለለቅ ህንፃ ወደ ለገሀር
• ከገነት መብራት ወደ ለገሀር
• ከጠማማ ፎቅ (ገነት ሆቴል) ወደ ሜክሲኮ
• ከሱዳን ኤምባሲ (ጠማማ ፎቅ) ወደ ሜክሲኮ
• ከአፍሪካ ህብረት ትራፊክ መብራት ወደ ሜክሲኮ
• ከዲአፍሪክ ሆቴል ወደ ሜክሲኮ
• ከሰንጋ ተራ 40/60 ኮንዶሚኒየም ወደ ለገሐር
• ከጎማ ቁጠባ ወደ ብሔራዊ ቲያትር
• ከሜትሮሎጂ ወደ ፖስታ ቤት መብራት
• ከጥቁር አንበሳ ሼል ወደ ኢምግሬሽን መብራት
• ከጎላ ሚካኤል መስቀለኛ ወደ ኢምግሬሽን
• ከቴዎድሮስ አደባባይ ወደ ኢምግሬሽን መብራት(ፖስታ ቤት)
• ከንግድ ማተሚያ ወደ ኦርማ ጋራዥ
• ከሚያዚያ 27 አደባባይ (4 ኪሎ) ወደ ፓርላማ መብራት
• ከጥይት ቤት ወደ ግቢ ገብርኤል
• ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ ቶታል የሚወስዱ መንገዶች ከንጋቱ 11 ጀምሮ ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረጉ ፖሊስ ገልጿል።
ፖሊስ አሽከርካሪዎች #ሌሎች_አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ መልዕክት አስተላልፏል።
ከነገ እሮብ የካቲት 22 ቀን 2015 ዓ.ም ምሽት ጀምሮ በተገለጹት መንገዶች ላይ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ሰዓታት ተሸከርካሪን #አቁሞ_መሄድ የተከለከለ ነው ተብሏል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE የትምህርት ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች እና ት/ቤቶች እውቅናና ሽልማት ሊሰጥ ነው። ሚኒስቴሩ በ2014 ዓ/ም በሀገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እና ትምህርት ቤቶች ሀገር አቀፍ እውቅናና ሽልማት እንደሚሰጥ አሳውቋል። የእውቅናና ሽልማት ፕሮግራሙ የፊታችን የካቲት 21 ቀን 2015 ዓ/ም እንደሚካሄድ ነው ሚኒስቴሩ የገለፀው። @tikvahethiopia
#Update
በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች እና ትምህርት ቤቶች ተሸለሙ።
በዛሬው ዕለት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን እና ትምህርት ቤቶችን መሸለማቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የፎቶ ባለቤት ፦ የጠ/ሚ ፅ/ቤት
@tikvahethiopia
በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች እና ትምህርት ቤቶች ተሸለሙ።
በዛሬው ዕለት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን እና ትምህርት ቤቶችን መሸለማቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የፎቶ ባለቤት ፦ የጠ/ሚ ፅ/ቤት
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች እና ትምህርት ቤቶች ተሸለሙ። በዛሬው ዕለት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን እና ትምህርት ቤቶችን መሸለማቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። የፎቶ ባለቤት ፦ የጠ/ሚ ፅ/ቤት @tikvahethiopia
#Update #UAE
በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 273 ተማሪዎች የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ሙሉ ስኮላርሺፕ መስጠቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ መናገራቸውን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ዛሬ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ወስደው ከግማሽ በላይ ውጤት ካስመዘገቡ ተማሪዎች ውስጥ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 273 ተማሪዎች እውቅና በሰጡበት ወቅት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለተማሪዎቹ " እንኳን ደስ ያላችሁ " ካሉ በኋላ የተሰጣቸውን ፈተና በአግባቡ መስራት በመቻላቸው " ኢትዮጵያን የሚያግዙ 273 ተማሪዎች ተገኝተዋል በዚህም ደስታ ይሰማናል" ብለዋል፡፡
ተማሪዎቹ እጅግ ዘመናዊ በሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን እንደሚከታተሉና ለኢትዮጵያ እና አፍሪካ የሚደርሱ እንዲሆኑም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ተማሪዎቹ በርትተው ተምረው ሀገራቸውን ሳይረሱ የሚጠቅሙ እንዲሆኑም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።
ዶ/ር ዐቢይ ሁሉም ተማሪ ጥበብን እንዲሻ እና ሀገሩን ለመለወጥ እንዲሰራ ጠይቀዋል፤ በተለይ " ለእውነት የቆመ ተማሪ ነገ ሃገሩን ይለውጣል፤ እናንተ የላቀ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎችም እውነትን የምትሹ መሆን አለባችሁ እንደዛ ሲሆን ደግሞ ሀገርን የምትገነቡ ትሆናላችሁ " ብለዋል።
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 273 ተማሪዎች የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ሙሉ ስኮላርሺፕ መስጠቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ መናገራቸውን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ዛሬ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ወስደው ከግማሽ በላይ ውጤት ካስመዘገቡ ተማሪዎች ውስጥ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 273 ተማሪዎች እውቅና በሰጡበት ወቅት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለተማሪዎቹ " እንኳን ደስ ያላችሁ " ካሉ በኋላ የተሰጣቸውን ፈተና በአግባቡ መስራት በመቻላቸው " ኢትዮጵያን የሚያግዙ 273 ተማሪዎች ተገኝተዋል በዚህም ደስታ ይሰማናል" ብለዋል፡፡
ተማሪዎቹ እጅግ ዘመናዊ በሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን እንደሚከታተሉና ለኢትዮጵያ እና አፍሪካ የሚደርሱ እንዲሆኑም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ተማሪዎቹ በርትተው ተምረው ሀገራቸውን ሳይረሱ የሚጠቅሙ እንዲሆኑም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።
ዶ/ር ዐቢይ ሁሉም ተማሪ ጥበብን እንዲሻ እና ሀገሩን ለመለወጥ እንዲሰራ ጠይቀዋል፤ በተለይ " ለእውነት የቆመ ተማሪ ነገ ሃገሩን ይለውጣል፤ እናንተ የላቀ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎችም እውነትን የምትሹ መሆን አለባችሁ እንደዛ ሲሆን ደግሞ ሀገርን የምትገነቡ ትሆናላችሁ " ብለዋል።
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
#ትኩረት
በምስራቅ ሀረርጌ ዞን የተከሰተው ድርቅ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ህጻናት አድን ድርጅት አስታወቀ፡፡
ድርጅቱ በዞኑ ውሃ ፤ የጤናና ሌሎች መሰረታዊ አገልግሎቶች በአፋጣኝ እንደሚያስፈልጉ አሳውቋል።
የኢትዬጵያ ህጻናት አድን ድርጅት የምስራቅ ሀረርጌ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የሚዲያ ዘርፍ ዳይሬክተር አቶ አብዱራዛቅ አህመድ " የተከተሰው ድርቅ ከፍተኛ ችግር እያስከተለ በመሆኑ በ35 ወረዳዎች ላይ ድጋፍ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ናቸው " ብለዋል።
ድርጅቱ ከ2 መቶ በላይ ትምህርት ቤቶች ላይ ለተማሪዎች ምገባ እያደረገ መሆኑን አሳውቀዋል።
በድርቁ ምክንያት ለተፈናቀሉ ዜጎች የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተሩ በድርቁ ከ2 ሚሊየን በላይ እንስሳት እስካሁን መሞታቸውን አንስተዋል፡፡
ቦረና ላይ ከተከሰተው ድርቅ ባልተናነሰ በምስራቅ ሀረርጌም በዜጎች እና በእንስሳት ላይ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን ገልጸው በዚህ ምክንያት ግን እስካሁን የሞተ ሰው ስለመኖሩ ያገኙት መረጃ እንደሌለ ተናግረዋል፡፡
ድርቁ ነአርሶ አደሩ ላይ ከፍተኛ ጫና እንደፈጠረ የተናገሩት ዳይሬክተሩ ዝናብ ካልዘነበ አሁንም በዞኑ ያለው ችግሩ እየተባባሰ እንደሚመጣ አመልክተዋል።
በዞኑ ካለው ችግር፤ አንፃር የሚደርሰው እርዳታ ተመጣጣኝ እንዳልሆነ አመልክተዋል።
በሌላ በኩል ፤ ድርጅቱ ቦረና ላይ ለደረሰው ድርቅ እርዳታ ተደራሽ ለማድረግ ድጋፎችን እያሰባሰበ መሆኑን አሳውቀዋል።
Credit : አሀዱ ሬድዮ እና ቴሌቪዥን
@tikvahethiopia
በምስራቅ ሀረርጌ ዞን የተከሰተው ድርቅ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ህጻናት አድን ድርጅት አስታወቀ፡፡
ድርጅቱ በዞኑ ውሃ ፤ የጤናና ሌሎች መሰረታዊ አገልግሎቶች በአፋጣኝ እንደሚያስፈልጉ አሳውቋል።
የኢትዬጵያ ህጻናት አድን ድርጅት የምስራቅ ሀረርጌ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የሚዲያ ዘርፍ ዳይሬክተር አቶ አብዱራዛቅ አህመድ " የተከተሰው ድርቅ ከፍተኛ ችግር እያስከተለ በመሆኑ በ35 ወረዳዎች ላይ ድጋፍ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ናቸው " ብለዋል።
ድርጅቱ ከ2 መቶ በላይ ትምህርት ቤቶች ላይ ለተማሪዎች ምገባ እያደረገ መሆኑን አሳውቀዋል።
በድርቁ ምክንያት ለተፈናቀሉ ዜጎች የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተሩ በድርቁ ከ2 ሚሊየን በላይ እንስሳት እስካሁን መሞታቸውን አንስተዋል፡፡
ቦረና ላይ ከተከሰተው ድርቅ ባልተናነሰ በምስራቅ ሀረርጌም በዜጎች እና በእንስሳት ላይ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን ገልጸው በዚህ ምክንያት ግን እስካሁን የሞተ ሰው ስለመኖሩ ያገኙት መረጃ እንደሌለ ተናግረዋል፡፡
ድርቁ ነአርሶ አደሩ ላይ ከፍተኛ ጫና እንደፈጠረ የተናገሩት ዳይሬክተሩ ዝናብ ካልዘነበ አሁንም በዞኑ ያለው ችግሩ እየተባባሰ እንደሚመጣ አመልክተዋል።
በዞኑ ካለው ችግር፤ አንፃር የሚደርሰው እርዳታ ተመጣጣኝ እንዳልሆነ አመልክተዋል።
በሌላ በኩል ፤ ድርጅቱ ቦረና ላይ ለደረሰው ድርቅ እርዳታ ተደራሽ ለማድረግ ድጋፎችን እያሰባሰበ መሆኑን አሳውቀዋል።
Credit : አሀዱ ሬድዮ እና ቴሌቪዥን
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba 🛫 #Mekelle
ቅዱስ ፓትርያርኩ ወደ ትግራይ መቐለ አቅንተዋል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በብፁዕ አቡነ ዮሐንስ የሽኝት ሥነ ሥርዓት ላይ ለመገኘት ዛሬ ወደ መቐለ አቅንተዋል።
ቅዱስነታቸው ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትንና ሊቃውንትን አስከትለው ነው ወደ መቐለ የተጓዙት።
ቅዱስነታቸው ወደ ትግራይ፣ መቐለ ሲጓዙ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የኒውዮርክ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን ቦሌ ኤርፖርት ተገኝተው ከቅዱስነታቸው ቡራኬ መቀበላቸውን የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልጹ ፅ/ቤት አሳውቋል።
ምንጭ፦ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልጹ ፅ/ቤት
@tikvahethiopia
ቅዱስ ፓትርያርኩ ወደ ትግራይ መቐለ አቅንተዋል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በብፁዕ አቡነ ዮሐንስ የሽኝት ሥነ ሥርዓት ላይ ለመገኘት ዛሬ ወደ መቐለ አቅንተዋል።
ቅዱስነታቸው ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትንና ሊቃውንትን አስከትለው ነው ወደ መቐለ የተጓዙት።
ቅዱስነታቸው ወደ ትግራይ፣ መቐለ ሲጓዙ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የኒውዮርክ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን ቦሌ ኤርፖርት ተገኝተው ከቅዱስነታቸው ቡራኬ መቀበላቸውን የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልጹ ፅ/ቤት አሳውቋል።
ምንጭ፦ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልጹ ፅ/ቤት
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ፎቶ፦ ቅዱስ ፓትርያርኩ መቐለ ገቡ።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በብፁዕ አቡነ ዮሐንስ የሽኝት ሥነ ሥርዓት ላይ ለመገኘት በሰላም መቐለ ገብተዋል።
ቅዱስነታቸው ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትንና ሊቃውንትን አስከትለው መቐለ ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
Photo : Social Media
@tikvahethiopia
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በብፁዕ አቡነ ዮሐንስ የሽኝት ሥነ ሥርዓት ላይ ለመገኘት በሰላም መቐለ ገብተዋል።
ቅዱስነታቸው ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትንና ሊቃውንትን አስከትለው መቐለ ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
Photo : Social Media
@tikvahethiopia