#NationalExam
በአ/አ ከተማ የ12ኛ ክፍል ፈተና ያለ ምንም እንከን እንዲካሄድ ሁሉም ባለድርሻ አካል ኃላፊነቱን እንዲወጣ ተጠየቀ።
ዛሬ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የመማር ማስተማር ሂደቱ ሰላማዊ በሆነ መንገድ መቀጠል በሚችልበት ጉዳዮች ዙሪያ ከሁሉም ትምህርት ቤቶች ከተውጣጡ ርዕሳነ መምህራንና ሱፐር ቫይዘሮች ጋር ውይይት አካሂዷል።
የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኜ ገብሩ ርዕሰ መምህራን በየትምህርት ቤቱ የሰላም እና ጸጥታ ጉዳዮችን በበላይነት መከታተል እና ከጸጥታ አካላት ጋር በጋራ መስራት ይገባቸዋል ብለዋል።
ከዚሁ ጋር በተገናኘ ከከተማ ጀምሮ እስከ ትምህርት ቤት ድረስ የሰላምና ጸጥታ ጉዳዮችን የሚከታተል የአብይ እና ቴክኒክ ኮሚቴ እንደሚዋቀር አሳውቀዋል።
ፈተናው በሰላም እንዲጠናቀ ሁሉን ኃላፊነቱን ይወጣ ተብሏል።
በሌላ በኩል ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫን ተከትሎ በየትምህርት ቤቱ የጸጥታ ችግር እንዳይከሰት ከወዲሁ መስራት እንደሚገባ ተጠቁሟል።
መረጃው ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የተገኘው ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአ/አ ከተማ የ12ኛ ክፍል ፈተና ያለ ምንም እንከን እንዲካሄድ ሁሉም ባለድርሻ አካል ኃላፊነቱን እንዲወጣ ተጠየቀ።
ዛሬ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የመማር ማስተማር ሂደቱ ሰላማዊ በሆነ መንገድ መቀጠል በሚችልበት ጉዳዮች ዙሪያ ከሁሉም ትምህርት ቤቶች ከተውጣጡ ርዕሳነ መምህራንና ሱፐር ቫይዘሮች ጋር ውይይት አካሂዷል።
የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኜ ገብሩ ርዕሰ መምህራን በየትምህርት ቤቱ የሰላም እና ጸጥታ ጉዳዮችን በበላይነት መከታተል እና ከጸጥታ አካላት ጋር በጋራ መስራት ይገባቸዋል ብለዋል።
ከዚሁ ጋር በተገናኘ ከከተማ ጀምሮ እስከ ትምህርት ቤት ድረስ የሰላምና ጸጥታ ጉዳዮችን የሚከታተል የአብይ እና ቴክኒክ ኮሚቴ እንደሚዋቀር አሳውቀዋል።
ፈተናው በሰላም እንዲጠናቀ ሁሉን ኃላፊነቱን ይወጣ ተብሏል።
በሌላ በኩል ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫን ተከትሎ በየትምህርት ቤቱ የጸጥታ ችግር እንዳይከሰት ከወዲሁ መስራት እንደሚገባ ተጠቁሟል።
መረጃው ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የተገኘው ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትምህርት_ሚኒስቴር የ2014 12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተናን በ12 ኮድ (በጥያቄ አቀማመጥ ስብጥር) ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው። የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከዚህ በፊት እንደነበረው በ4 ኮድ (4 የተለያዩ ፈተናዎች/በጥያቄ አቀማመጥ) ሳይሆን እስከ 12 እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል። ይህ የፈተና ኩረጃን ለመከላከል ከሚሰሩት ስራዎች መካከል አንዱ…
#NationalExam
የ12ኛ ክፍል ፈተና ከመስከረም 30 ቀን 2015 ጀምሮ ይሰጣል።
የ2014 የትምህርት ዘመን ብሔራዊ 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ማጠቃለያ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
ፈተናው ከመስከረም 30/2015 ዓ/ም ጀምሮ በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
የፈተና ደንብ ጥሰቶች #በህግ ያስጠይቃሉም ተብሏል።
የ2014 ዓ/ም ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተናን በዩኒቨርሲቲዎች ከመስጠት ባለፈ የፈተና ኩረጀ እና ስርቆትን ለመከላከል በ12 ኮድ (በጥያቄ አቀማመጥ ስብጥር) ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ከቀናት በፊት መገለፁ ይታወሳል።
የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፤ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከዚህ በፊት እንደነበረው በ4 ኮድ (4 የተለያዩ ፈተናዎች/በጥያቄ አቀማመጥ) ሳይሆን እስከ 12 እንዲሆን እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀው እንደነበር አይዘነጋም።
ይህ የፈተና ኩረጃን ለመከላከል ከሚሰሩት ስራዎች መካከል አንዱ ሲሆን ለጎን ያሉ ተማሪዎች እርስ በእርስ የሚፈተኑት ፈተና የጥያቄው ዝርዝር (order) በፍፁም የተገናኘ እንዳይሆን ለማድረግ የታሰበ ነው።
@tikvahethiopia @tikvahuniversity
የ12ኛ ክፍል ፈተና ከመስከረም 30 ቀን 2015 ጀምሮ ይሰጣል።
የ2014 የትምህርት ዘመን ብሔራዊ 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ማጠቃለያ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
ፈተናው ከመስከረም 30/2015 ዓ/ም ጀምሮ በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
የፈተና ደንብ ጥሰቶች #በህግ ያስጠይቃሉም ተብሏል።
የ2014 ዓ/ም ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተናን በዩኒቨርሲቲዎች ከመስጠት ባለፈ የፈተና ኩረጀ እና ስርቆትን ለመከላከል በ12 ኮድ (በጥያቄ አቀማመጥ ስብጥር) ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ከቀናት በፊት መገለፁ ይታወሳል።
የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፤ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከዚህ በፊት እንደነበረው በ4 ኮድ (4 የተለያዩ ፈተናዎች/በጥያቄ አቀማመጥ) ሳይሆን እስከ 12 እንዲሆን እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀው እንደነበር አይዘነጋም።
ይህ የፈተና ኩረጃን ለመከላከል ከሚሰሩት ስራዎች መካከል አንዱ ሲሆን ለጎን ያሉ ተማሪዎች እርስ በእርስ የሚፈተኑት ፈተና የጥያቄው ዝርዝር (order) በፍፁም የተገናኘ እንዳይሆን ለማድረግ የታሰበ ነው።
@tikvahethiopia @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE " የ2014 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከመስከረም 30 /2015 ዓ/ም ጀምሮ በ2 ዙር እንዲሰጥ ታቅዷል " - ትምህርት ሚኒስቴር የ2ዐ14 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርስቲዎች እንዲሰጥ መወሰኑ ይታወቃል፡፡ ፈተናው ከመስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ #በሁለት_ዙር እንዲሰጥ መታቀዱን በትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ተፈርሞ ለ42 ዩኒቨርሲቲዎች…
#NationalExam
መስከረም 30 ቀን 2015 መሰጠት የሚጀምረው የ2014 ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና " ተሰርቆ ወጥቷል " በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆነን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
የአገልግሎተ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር እሸቱ ከበደ ከፈተና ስርቆት ጋር በተያያዘ እተሰራጨ ያለው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ገልፀዋል።
በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ " የዘንድሮ " ነው ተብሎ የሚሰራጨው ፈተና በ2013/14 (2021) ዓ.ም የተሰጠ እንደሆነ አስረድተዋል። እየተሰራጩ ያሉት ፈተናዎች ዓመቱ ኤዲት ተደርጎ መሆኑንም አመልክተዋል።
" ተፈታኝ ተማሪዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚሰራጩ መሰል መረጃዎችን ከማመናቸው በፊት የአሰራጩን ታማኝነት እንዲያጣሩና ትክክለኛነቱን እንዲመረምሩ " መልዕክታቸውን አስተላፈዋል።
የአገር አቀፍ ፈተናን የተመለከቱ ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት " ፖለቲካን ከታዳጊዎች ህይዎት ቢለዩ መልካም ነው " ሲሉ ለ " ኢትዮጵያ ቼክ " መረጃ አጣሪ ድረገፅ በሰጡት ቃል አሳስበዋል።
የ2014 ዓ/ም የሀገር አቀፍ ፈተና ከመስከረም 30/2015 ዓ/ም ጀምሮ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በሁለት ዙር የሚሰጥ ይሆናል።
ከትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንደሰማነው ፈተናው ተዘጋጅቶ እየታተመ ይገኛል ፤ ፈተናው እስከሚሰጥበት ቀን ድረስ ተፈታኞች እራሳቸውን ማዘጋጀት አለባቸው ተብሏል።
@tikvahethiopia @tikvahuniversity
መስከረም 30 ቀን 2015 መሰጠት የሚጀምረው የ2014 ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና " ተሰርቆ ወጥቷል " በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆነን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
የአገልግሎተ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር እሸቱ ከበደ ከፈተና ስርቆት ጋር በተያያዘ እተሰራጨ ያለው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ገልፀዋል።
በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ " የዘንድሮ " ነው ተብሎ የሚሰራጨው ፈተና በ2013/14 (2021) ዓ.ም የተሰጠ እንደሆነ አስረድተዋል። እየተሰራጩ ያሉት ፈተናዎች ዓመቱ ኤዲት ተደርጎ መሆኑንም አመልክተዋል።
" ተፈታኝ ተማሪዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚሰራጩ መሰል መረጃዎችን ከማመናቸው በፊት የአሰራጩን ታማኝነት እንዲያጣሩና ትክክለኛነቱን እንዲመረምሩ " መልዕክታቸውን አስተላፈዋል።
የአገር አቀፍ ፈተናን የተመለከቱ ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት " ፖለቲካን ከታዳጊዎች ህይዎት ቢለዩ መልካም ነው " ሲሉ ለ " ኢትዮጵያ ቼክ " መረጃ አጣሪ ድረገፅ በሰጡት ቃል አሳስበዋል።
የ2014 ዓ/ም የሀገር አቀፍ ፈተና ከመስከረም 30/2015 ዓ/ም ጀምሮ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በሁለት ዙር የሚሰጥ ይሆናል።
ከትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንደሰማነው ፈተናው ተዘጋጅቶ እየታተመ ይገኛል ፤ ፈተናው እስከሚሰጥበት ቀን ድረስ ተፈታኞች እራሳቸውን ማዘጋጀት አለባቸው ተብሏል።
@tikvahethiopia @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
* ብሔራዊ ፈተና የ2014 ዓ/ም 12ኛ ክፍል ፈተናን በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው። በዚህም መሰረት ዩኒቨርሲቲዎች በአካዳሚክ ካላንደራቸው ላይ ማስተካከያ እያደረጉ ይገኛሉ። ይህ እየተደረገ ያለው ተማሪዎች ፈተናቸውን በሚወስዱበት ወቅት በቅጥር ግቢዎቹ ውስጥ ማንኛውም የዩኒቨርሲቲ ተማሪ መገኘት ስለሌለበት ነው። በሌላ በኩል ፤ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት #ለሪፖርተር_ጋዜጣ…
#NationalExam
ለ12ኛ ክፍል የብሄራዊ ፈተና አስፈፃሚዎች ስልጠና ተሰጣቸው።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፤ የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ት/ት ማጠናቀቂያ ፈተና አስፈጻሚዎች ሥልጠና እንደተሰጣቸው ገልጿል።
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ፈንታ ማንደፍሮ የፈተና አስፈፃሚዎች ትልቅ ኃላፊነት የተጣለባቸው መሆኑን በመገንዝብ በትጋትና በታማኝነት እንዲወጡ በማሳሰብ ዝርዝር የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በበኩላቸው ፤ የፈተና አስፈፃሚዎች በቂ ትኩረት በመስጠት ያለ ምንም አድልዎ ሙያዊ በሆነ አግባብ እንዲሁም በቁርጠኝነት የተጣለባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ አስገንዝበዋል።
ዝርዝር ስልጠና በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አመራርና በዘርፉ ባለሙያዎች ተሰጥቷል።
የ2014 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ከመጪው መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ በሁለት ዙር ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል።
ፎቶ : የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
@tikvahethiopia
ለ12ኛ ክፍል የብሄራዊ ፈተና አስፈፃሚዎች ስልጠና ተሰጣቸው።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፤ የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ት/ት ማጠናቀቂያ ፈተና አስፈጻሚዎች ሥልጠና እንደተሰጣቸው ገልጿል።
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ፈንታ ማንደፍሮ የፈተና አስፈፃሚዎች ትልቅ ኃላፊነት የተጣለባቸው መሆኑን በመገንዝብ በትጋትና በታማኝነት እንዲወጡ በማሳሰብ ዝርዝር የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በበኩላቸው ፤ የፈተና አስፈፃሚዎች በቂ ትኩረት በመስጠት ያለ ምንም አድልዎ ሙያዊ በሆነ አግባብ እንዲሁም በቁርጠኝነት የተጣለባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ አስገንዝበዋል።
ዝርዝር ስልጠና በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አመራርና በዘርፉ ባለሙያዎች ተሰጥቷል።
የ2014 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ከመጪው መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ በሁለት ዙር ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል።
ፎቶ : የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ለፈተና ሄደው ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ለወለዱ ተፈታኞች በቀጣይ እንደመደበኛ ተማሪ እንዲፈተኑ ዕድል ይሰጣቸዋል " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በእርግዝና ላይ ላሉ እና ወልደው ህጻንን ጡት እየመገቡ ላሉ ለተመዘገቡ ሴት የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የእነርሱን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ የመፈተኛ ስርዓት በቀጣይ መዘጋጀቱን አሳውቋል። በመሆኑም ተፈታኞቹ ከመስከረም…
#NationalExam
የ2014 የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከነገ መስከረም 30 ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል።
ነገ ፈተናቸውን የሚፈተኑት በመጀመሪያ ዙር ወደ መፈተኛ ማዕከላት / ዩኒቨርሲቲ የገቡ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ናቸው።
ተማሪዎቹ ስለፈተናው አጠቃላይ (ኦረንቴሽን) ገለፃ ተደርጎላቸዋል።
በፈተና ወቅት መከተል ስላለባቸው የስነምግባር መርሆች፣ የሰዓት አከባበርን በተመለከተ ፣ የተብራራላቸው ሲሆን የመፈተኛ ጣቢያ እና ክፍላቸውን ለይተውም እንዲያውቁ መደረጉን ሰምተናል።
ከተፈታኝ ተማሪዎች በተጨማፊ ፈታኞች፣ ለፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች፣ ለሱፐርቫይዘሮች፣ ማየት ለተሳናቸው ተፈታኝ አንባቢዎችና ለመልስ ወረቀት ቆጣሪዎች ገለፃ (ኦረንቴሽን) ተሰጥቷቸዋል።
የማህበራዊ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከነገ ጥዋት ጀምሮ እስከ ጥቅምት 2 ድረስ ይሰጣል፤ ከጥቅምት 3 - ጥቅምት 4 ተፈታኞች ወደየአካባቢያቸው ይመለሳሉ።
የ12ኛ መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናው ጥብቅ በሆነ ዲሲፕሊን እንደሚመራ ተገልጾልናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለተፈታኞች በሙሉ መልካም ፈታናን ይመለኛል!
@tikvahethiopia
የ2014 የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከነገ መስከረም 30 ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል።
ነገ ፈተናቸውን የሚፈተኑት በመጀመሪያ ዙር ወደ መፈተኛ ማዕከላት / ዩኒቨርሲቲ የገቡ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ናቸው።
ተማሪዎቹ ስለፈተናው አጠቃላይ (ኦረንቴሽን) ገለፃ ተደርጎላቸዋል።
በፈተና ወቅት መከተል ስላለባቸው የስነምግባር መርሆች፣ የሰዓት አከባበርን በተመለከተ ፣ የተብራራላቸው ሲሆን የመፈተኛ ጣቢያ እና ክፍላቸውን ለይተውም እንዲያውቁ መደረጉን ሰምተናል።
ከተፈታኝ ተማሪዎች በተጨማፊ ፈታኞች፣ ለፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች፣ ለሱፐርቫይዘሮች፣ ማየት ለተሳናቸው ተፈታኝ አንባቢዎችና ለመልስ ወረቀት ቆጣሪዎች ገለፃ (ኦረንቴሽን) ተሰጥቷቸዋል።
የማህበራዊ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከነገ ጥዋት ጀምሮ እስከ ጥቅምት 2 ድረስ ይሰጣል፤ ከጥቅምት 3 - ጥቅምት 4 ተፈታኞች ወደየአካባቢያቸው ይመለሳሉ።
የ12ኛ መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናው ጥብቅ በሆነ ዲሲፕሊን እንደሚመራ ተገልጾልናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለተፈታኞች በሙሉ መልካም ፈታናን ይመለኛል!
@tikvahethiopia