TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#BidenHarris

በአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዶናልድ ትረምፕን ያሸነፉት ጆ ባይደን ከወዲሁ የአስተዳደር ርክክብ ዝግጅት ፈጥነው ጀምረዋል።

በመጪው ጥር 20 (እ.አ.አ) ቃለ መሃላ ፈጽመው ሲረከቡ ቁልፍ የሆኑ የትረምፕ ፖሊሲዎችን ይቀለብሳሉ ተብሏል።

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ፥ ጆ ባይደን 'በጠባብ አጠቃላይ ድምጽ' ባሸነፉባቸው ክፍለ ግዛቶች ላይ የተፈጸሙ የድምጽ ቆጠራ መዛባቶች ሲፈተሹ ውጤቶቹ ተቀልብሰው አሸናፊ እኔ እሆናለሁ በማለት ክሶች መስርተዋል።

ተመራጩ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን እና ምክትላቸው ካማላ ሃሪስ ትናንት የሽግግር ዌብሳያታቸውን ከፍተዋል።

ፕሬዚዳንት ትረምፕ በምርጫው መሸነፋቸውን ለመቀበልም ሆነ ለጆ ባይደን ስልክ ደውለው ለማነጋገር ፈቃደኛ አልሆኑም ሲል #ቪኦኤ በድረገፁ አስነብቧል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
አሜሪካ ስለህዳሴው ግድብ ፦

ኢትዮጵያ ፣ ግብጽ እና ሱዳን የታላቁ የኅዳሴ ግድብን (GERD) በተመለከተ ያላቸውን አለመግባባት በትብብር እና ገንቢ በሆነ ጥረት እንዲፈቱ አሜሪካ ድጋፍ መስጠቷን እንደምትቀጥል ማስታወቋን #ቪኦኤ በድረገፁ አስነብቧል።

ሦስቱ ሃገሮች ውጤታማ ወደሆነ ውይይት እንዲመለሱ እናበረታታለን ሲል የዋይት ሃውስ የብሄራዊ ጸጥታ ምክር ቤት ቃል አቀባይ ቢሮ አስታውቋል።

ውዝግቡ ገንቢ መፍትሄ እንዲያገኝ እና በክልሉ ያለው ውጥረት እንዲረግብ ለመርዳት በምንሰጠው ድጋፍ ከግድቡ ጋር የተገናኙ ጉዳዮች ሚዛናዊ በሆነ መንገድ መያዛቸውን በማረጋገጥ መስራታችንን እንቀጥላለን ብሏል መግለጫው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
PHOTO : በኮቪድ -19 ምክንያት ለአንድ ዓመት ተራዝሞ የነበረው የቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ ዛሬ አነስ ባለ ነገር ግን በደማቅ የመክፈቻ ሥነ ስርዓት ተጀምሯል።

በየ4 ዓመቱ የሚካሄደው ኦሎምፒክ በዓለም አቀፍ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ለአንድ ዓመት እንዲዘገይ ሆኗል።

በዛሬው በቶኪዮ ኦሊምፒክ ስቴዲየም የመክፈቻ ሥነ ስርዓት ላይ ለኮቪድ-19 ጥንቃቄ ሲባል ወደ 900 የሚሆኑ ተጋባዥ እንግዶች እና ባለሥልጣናት ብቻ በታደሙበት ነው መክፈቻው የተካሄደው።

#ቪኦኤ

Photo Credit : AP

@tikvahethiopoa
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ሀገር መከላከያ ሰራዊት ትላንት ካማሽ ገብቷል።

የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ካማሽ ከተማ ሙሉ ለሙሉ መግባቱን የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ ም/ኮሚሽነር ኢንስፔክተር ምስጋናው እንጂፈታ አሳውቀዋል።

የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ካማሽ መግባቱን ተከትሎ በአካባቢው ይሰማ የነበረው የተኩስ ልውውጥ መቆሙንና በአካባቢው የነበረውን ታጣቂ ኃይልም ማፈግፈጉን ገልፀዋል።

ኢስፔክተር ምስጋናው እንጅፈታ ለ#ቪኦኤ በሰጡት ቃል ፥ በካማሺ ዞን የሚንቀሳቀሱ እራሳቸው የቤንሻንጉል ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ (ቤህነን) የሚባሉ ታጣቂዎች የዞኑን በርካታ ቦታዎች ተቆጣጥረው መቆየታቸውን አስረድተዋል።

"የቤህነን ታጣቂ ከኦነግ ሸኔ ጋር ቅንጅት አላቸው፣ ከእነሱ ጋር እየተጋገዙ ነው ይህን የሚያደርጉት፣ በዞኑ 5 ወረዳ ነው ያለው ከዞን እና የወረዳ ማዕከሎች ውጪ አንድም ቀበሌ በመንግስት እጅ ላይ የለም" ሲሉ አክለዋል።

ከመንግስት እጅ በወጡ ቦታዎች በፖለቲካው እንቅስቃሴ የለም፣ ሙሉ በሙሉ ግንኙነቶችም ተቋርጠዋል በዚህ ምክንያት በዞኑ ሰብዓዊ ቀውስ ተፈጥሯል ሲሉ ገልፀዋል።

ኢንስፔክተር ምስጋናው ፥ ባለው የፀጥታ ኃይል ውስንነት የተነሳ ችግር አለባቸው ተብሎ በጥናት የተለዩ ቦታዎች በመግባት ህግ ማስከበር እንዳልተቻለ አመልክተው ፤ ከዚህ ጋር በተያያዘ ህብረተሰቡ በተጎሳቆለ ሁኔታ ውስጥ ነው ያለው ብለዋል።

ከመንግስት ቁጥጥር ውጭ በሆኑ ቦታዎች ያልተዘረፈ ከብት የለም፤ ያልተዘረፈ ንብረት የለም፣ የከፋ ሰብዓዊ ቀውስ ነው ያለው ፤ ህብረተሰቡ በረሃብ እየተጎዳ ነው፣ መድሃኒት የለም ተዘርፏል፣ ጤና ኬላዎች ግብአት አይገባላቸውም ግንኙነት የለም ተቋርጧል በዚህም ህብረተሰቡ ከፍተኛ ስቃይ ላይ መሆኑን አመልክተዋል።

ያንብቡ : telegra.ph/Benishangul-Gumuz-09-25

@tikvahethiopia
#ትኩረት_የሚሻ_የፀጥታ_ጉዳይ 📣

በደቡብ ወሎ ዞን የአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ እና በአፋር ተላላክ ወረዳ በአንድ ግለሰብ ሞት ምክንያት የተቀሰቀሰ ግጭት ወደ ተኩስ ልውውጥ ተቀይሮ ለሰዎች ሞት እና መቁሰል ምክንያት ሆኗል።

አሁን ያለው የፀጥታ እጅግ ልዩ ትኩረት የሚፈልግ ነው ተብሏል።

ችግሩ የተከሰተው ባለፈው ማክሰኞ ዕለት ሲሆን አንድ የአፋር ተወላጅ አርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ መድና ከተማ ገበያ ውሎ ሲመለስ መሃል መንገድ ላይ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ከተገደለ በኃላ ነው።

ባለፉት ተከታታይ ቀናት መዲናን ጨምሮ በበርካታ አካባቢዎች ላይ የተኩስ እሩምታ የሚሰማ ሲሆን የግለሰብ ቤቶችም መቃጠል መጃመራቸው ተነግሯል። እስካሁን ምን ያህል ሰው እንደተጎዳ ማወቅ አልተቻለም።

ችግሩን ለመፍታት በአፋርም አማራ ክልል በኩልም ብዙ ቢጣርም ውጤት አላመጣም ይልቅም እየባሰ ሄዷል።

በርካቶች ባለው የፀጥታ ችግር ከቄያቸው እየሸሹ መሆናቸውም ተነግሯል።

የአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ፅህፈት ቤት ኃላፊ ሰኢድ ኢብራሂም አሁን ያለው ሁኔታ ከግለሰብም አልፎ መልኩን ቀይሮ እጅግ አሰቃቂ የሆነና መጥፎ ጉዳት ሊያደርስ በሚችልበት ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ገልፀው የክልሉ መንግስት እና የፌዴራል መንግስት መኃል ገብተው ካላስቆመው ቀጠናው በጣም አስጊ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል።

ከአፋር ክልል ተላላክ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት እና የአርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት በኩል ለቪኦኤ ሬድዮ የሰጡት ቃሎች በዚህ ተያይዟል ያንብቡ ⬇️

https://telegra.ph/Attention-06-04-2

#አርጎባ_ብሄረሰብ_ልዩ_ወረዳ #ተላላክ_ወረዳ

#ቪኦኤ

@tikvahethiopia
#OLF

በእስር ላይ የሚገኙት የኦሮሞ ነፃነት ግንባር አመራሮች ጉዳይ ላይ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ አስተላልፏል።

በቡራዩ እስር ላይ ካሉ 7 የኦነግ አመራሮች 4ቱ ከእስር እንዲለቀቁ የቡራዩ ወረዳ ፍ/ቤት ትዕዛዝ አስተላልፏል።

ጠበቃ አቶ ደምሴ ፍቃዱ ጉዳዩን በተመለከተ ለ #ቪኦኤ_ሬድዮ በሰጡት ቃል አራቱ የኦነግ አመራሮች አካልን ነፃ የማውጣት አቤቱታ አቅርበው እንደነበር፤ አቤቱታ የቀረበለት የቡራዩ ከተማ ፍ/ ቤት ግለሰቦቹ በማን እና ለምን እንደታሰሩ ለመረዳት ለሶስት ተከታታይ ችሎት ጥሪ ሲያቀርብ ነበር።

ነገር ግን ፖሊስ ሆነ እስረኞች አልቀረቡም። አርብ ሀምሌ 8 የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ማብራሪያ ሠጥቷል።

ጠበቃ ደምሴ ፍቃዱ ፦

" 1ኛ አመልካች የሆነው ሚካኤል በቀለ ከዚህ ቀደም የወንጀል መዝገብ ተጣርቶበት በወንጀል አንቀፅ 42 መሰረት የተጠረጠረበት ጉዳይ ወንጀል ነው ተብሎ የሚያስከስስ ባለመሆኑ መዝገቡ ተዘግቶ ፖሊስ ከእስር ቤት እንዲለቀው ትዕዛዝ ፅፈንለት ፖሊስ ግን አለቅም ማለቱን አቃቤ ህግ ገልጿል።

2ኛ እና 3ኛ አመልካቾች ለሚ ቤኛ እና ዳዊት አብደታን በተመለከተ በተጠረጠሩበት ወንጀል ተከሰው የአቃቤ ህግ ምስክሮች ከተሰሙ በኃላ ፍርድ ቤት ጉዳዩን መርምሮ የሚያስቀጣ አይደለም በማለት በነፃ ካሰናበታቸው በኃላ ፖሊስ በራሱ ስልጣን ነው ያሰረው ሲል አቃቤ ህግ ለፍ/ ቤት አመልክቷል።

4ኛ አመልካች ገዳ ገቢሳ የተጠረጠረበት ወንጀል አቃቤ ህግ ከመረመረ በኃላ አያስከስስም ብሎ መዝገቡን ዘግቶ ከእስር እንዲለቀቅ ለፖሊስ ትዕዛዝ መስጠቱን አብራርቷል።

ከአቃቤ ህግም ምንም መዝገብ የላቸውም ሲል ነው የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ለፍ/ ቤት ያስረዳው። "

ፍ/ቤት ሀምሌ 11 ከእስር እንዲለቀቁ የወሰነ ቢሆንን ታሳሪዎቹ እስካሁን አልተለቀቁም።

@TIKVAHETHIOPIA