TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION ሰንበቴ ! የሰንበቴ ከተማ አስተዳደር ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ ከነሐሴ 26/ 2014 ዓ/ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የሰዓት እላፊ ገደብ አውጇል። በዚህም መሰረት ፦ - የከተማ ባለ 3 እግር ተሽከርካሪዎች (ባጃጆች) ከምሽቱ 12 ሰአት ጀምሮ በከተማው ውስጥ ማሽከርከር ተከልክለዋል። - ከተመደበው የጸጥታ ኃይል በስተቀር ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት…
#ATTENTION
የጎንደር ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት ወቅታዊ ጉዳዮችን ታሳቢ በማድረግ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል።
ከውሳኔዎቹ መካከል ፦
- ከተፈቀደላቸው የፀጥታ አካላት ውጭ የተለያዩ የፀጥታ አካላት አልባሳትን መልበስ ተከልክሏል።
- ከፀጥታ መዋቅሩ ውጭ፣ በከተማው በብሎክ አደረጃጀት አካባቢን እንዲጠብቅ በተሰጠው ተራው ከተሰማራው ውጭ በየትኛውም ቦታ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው፡፡
- ማህበረሰቡን የሚያውኩ አሉባልታዎች ወይም የሃሰት መረጃዎችን በተለያዩ ሚዲያዎች፣ በመጠጥ ቤቶች ወዘተ ማሰራጨት ህዝቡን ማወዛገብ፣ ማሰጨነቅ በጥብቅ ተከልክሏል።
- በከተማው ያሉ ተፈናቃዮች ከተሰጣቸው መጠለያ ካምፕ ውጭ መንቀሳቀስ የተከለከለ ሲሆን ለገበያ፣ ለህክምና፣ ለአንገብጋቢ ጉዳዮች፣ ለተለያዩ ስራዎች ከመጠለያው መውጣት ያለበት ተፈናቃይ በሚመለከታቸው የካምፕ አስተባባሪዎችና በክ/ከተማው የፀጥታ መዋቅር እውቅና እና የመውጫና የመግቢያ ፈቃድ መለያ ካርድ ይዞ ተመዝግቦ ተፈቅዶለት የሚንቀሳቀስ ይሆናል፡፡
- በአሉባልታ ወሬዎችና ስበብ በመፈለግ ለህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ እንደ ባንክ ቤት፣ ሱቆችና ሆቴሎች፣ የገበያ ማዕከሎች እና የመሳሰሉትን መዝጋት ተከልክሏል።
- ከነሀሴ 27 ጀምሮ የቀበሌ መታወቂያ መስጠት ተከልክሏል። አስቸኳይ የሆነ ለምሳሌ ለህክምና፣ ወደ ዩኒቨርስቲ ለመሄድ፣ ወደ ውጭ አገር ለሚደረግ ጉዞ ከገጠሙ የክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚና የክ/ከተማው ሰላምና ደህንነት በጋራ በማየት መታወቂያ ሊሰጡ ይችላሉ።
- አግባብነት የሌለው የዋጋ ንረት የሚፈጥሩ በሸቀጦች በግብርና ምርቶች ላይ ተገቢ ያልሆነ ዋጋ ጨምሮ ህዝቡን ማስቃየት በጥብቅ ተከልክሏል።
- በጫት ቤቶች ተሰብስቦ በመቃም አሉባልታና ሽብር መንዛት ተከልክሏል።
(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የጎንደር ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት ወቅታዊ ጉዳዮችን ታሳቢ በማድረግ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል።
ከውሳኔዎቹ መካከል ፦
- ከተፈቀደላቸው የፀጥታ አካላት ውጭ የተለያዩ የፀጥታ አካላት አልባሳትን መልበስ ተከልክሏል።
- ከፀጥታ መዋቅሩ ውጭ፣ በከተማው በብሎክ አደረጃጀት አካባቢን እንዲጠብቅ በተሰጠው ተራው ከተሰማራው ውጭ በየትኛውም ቦታ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው፡፡
- ማህበረሰቡን የሚያውኩ አሉባልታዎች ወይም የሃሰት መረጃዎችን በተለያዩ ሚዲያዎች፣ በመጠጥ ቤቶች ወዘተ ማሰራጨት ህዝቡን ማወዛገብ፣ ማሰጨነቅ በጥብቅ ተከልክሏል።
- በከተማው ያሉ ተፈናቃዮች ከተሰጣቸው መጠለያ ካምፕ ውጭ መንቀሳቀስ የተከለከለ ሲሆን ለገበያ፣ ለህክምና፣ ለአንገብጋቢ ጉዳዮች፣ ለተለያዩ ስራዎች ከመጠለያው መውጣት ያለበት ተፈናቃይ በሚመለከታቸው የካምፕ አስተባባሪዎችና በክ/ከተማው የፀጥታ መዋቅር እውቅና እና የመውጫና የመግቢያ ፈቃድ መለያ ካርድ ይዞ ተመዝግቦ ተፈቅዶለት የሚንቀሳቀስ ይሆናል፡፡
- በአሉባልታ ወሬዎችና ስበብ በመፈለግ ለህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ እንደ ባንክ ቤት፣ ሱቆችና ሆቴሎች፣ የገበያ ማዕከሎች እና የመሳሰሉትን መዝጋት ተከልክሏል።
- ከነሀሴ 27 ጀምሮ የቀበሌ መታወቂያ መስጠት ተከልክሏል። አስቸኳይ የሆነ ለምሳሌ ለህክምና፣ ወደ ዩኒቨርስቲ ለመሄድ፣ ወደ ውጭ አገር ለሚደረግ ጉዞ ከገጠሙ የክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚና የክ/ከተማው ሰላምና ደህንነት በጋራ በማየት መታወቂያ ሊሰጡ ይችላሉ።
- አግባብነት የሌለው የዋጋ ንረት የሚፈጥሩ በሸቀጦች በግብርና ምርቶች ላይ ተገቢ ያልሆነ ዋጋ ጨምሮ ህዝቡን ማስቃየት በጥብቅ ተከልክሏል።
- በጫት ቤቶች ተሰብስቦ በመቃም አሉባልታና ሽብር መንዛት ተከልክሏል።
(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia