" 18 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶባታል "
" ከሌላ ሴት ጋር ግንኙነት ጀምረሃል " በሚል ምክንያት የሶስት ልጆቿን አባት በመጥረቢያ በመምታት የገደለችው ግለሰብ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት መቀጣቷን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
ግለሰቧ ትዕግስት አዘዘው ትባላለች ፤ ወንጀሉን የፈፀመችው መስከረም 10 ቀን 2014 ዓ/ም በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ልዩ ቦታው አንቆርጫ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው፡፡
ተከሳሿ በዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ገደማ የ3 ልጆቿ አባት የሆነው ባለቤቷን ሟች አወቀ ይርዳውን " ከሌላ ሴት ጋር ግንኙነት ጀምረሃል፤ የተለያዩ ሴቶችንም በስልክ ታናግራለህ " በሚል ምክንያት ሶፋ ላይ በተኛበት ጭንቅላቱን በመጥረቢያ ደጋግማ በመምታት ህይወቱ እንዲያልፍ አድርጋለች።
ትዕግስት በፈፀመችው ወንጀል በቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ ከተጣራባት እና ክስ ከተመሰረተባት በኋላ ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሰው እና በሰነድ ማስረጃ ጥፋተኛ መሆኗን በማረጋገጥ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ ወስኖባታል።
የፖሊስ መልዕክት ፦
በትዳር መካከል አለመግባባቶች በሚያጋጥሙበት ወቅት በመነጋገር ለመፍታት ከመሞከር እና ይህም ካልተሳካ በሰላማዊ መንገድ ከመለያየት በዘለለ በስሜታዊነት እና በቅናት መንፈስ ተነሳስቶ ወንጀል መፈፀም ከሚያስከትለው የህግ ተጠያቂነት ባሻገር በልጆች እና በቤተሰብ ላይ የሚያሳድረው ስነ ልቦናዊ ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን በመረዳት ነገሮችን በሰከነ ሁኔታ ማመዛዘን ይገባል።
Via Addis Ababa Police
@tikvahethiopia
" ከሌላ ሴት ጋር ግንኙነት ጀምረሃል " በሚል ምክንያት የሶስት ልጆቿን አባት በመጥረቢያ በመምታት የገደለችው ግለሰብ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት መቀጣቷን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
ግለሰቧ ትዕግስት አዘዘው ትባላለች ፤ ወንጀሉን የፈፀመችው መስከረም 10 ቀን 2014 ዓ/ም በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ልዩ ቦታው አንቆርጫ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው፡፡
ተከሳሿ በዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ገደማ የ3 ልጆቿ አባት የሆነው ባለቤቷን ሟች አወቀ ይርዳውን " ከሌላ ሴት ጋር ግንኙነት ጀምረሃል፤ የተለያዩ ሴቶችንም በስልክ ታናግራለህ " በሚል ምክንያት ሶፋ ላይ በተኛበት ጭንቅላቱን በመጥረቢያ ደጋግማ በመምታት ህይወቱ እንዲያልፍ አድርጋለች።
ትዕግስት በፈፀመችው ወንጀል በቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ ከተጣራባት እና ክስ ከተመሰረተባት በኋላ ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሰው እና በሰነድ ማስረጃ ጥፋተኛ መሆኗን በማረጋገጥ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ ወስኖባታል።
የፖሊስ መልዕክት ፦
በትዳር መካከል አለመግባባቶች በሚያጋጥሙበት ወቅት በመነጋገር ለመፍታት ከመሞከር እና ይህም ካልተሳካ በሰላማዊ መንገድ ከመለያየት በዘለለ በስሜታዊነት እና በቅናት መንፈስ ተነሳስቶ ወንጀል መፈፀም ከሚያስከትለው የህግ ተጠያቂነት ባሻገር በልጆች እና በቤተሰብ ላይ የሚያሳድረው ስነ ልቦናዊ ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን በመረዳት ነገሮችን በሰከነ ሁኔታ ማመዛዘን ይገባል።
Via Addis Ababa Police
@tikvahethiopia
#ውብ_አረቢያን_መጅሊስ
ከአውሮፓና ከእስያ በሚመረቱ ጥሬ እቃ በብቁ ባለሞያ በዘመነ ማሽን ውብ አረቢያን መጅሊስ የሚያመርታቸውን ውብ እና ማራኪ የሆኑ መጅሊሶቻችን እና ሶፋዎችን እንካቹ ስንል 👉 በ9 ቅርጫፎቻችን ስንጠበቅዎ በታላቅ ደስታ ነው 0910222244 / 0954111133 / 0954111100
ተጨማሪ ፎቶ ለመምረጥ ሊንኩን የጫኑት https://t.iss.one/wubeare
ከአውሮፓና ከእስያ በሚመረቱ ጥሬ እቃ በብቁ ባለሞያ በዘመነ ማሽን ውብ አረቢያን መጅሊስ የሚያመርታቸውን ውብ እና ማራኪ የሆኑ መጅሊሶቻችን እና ሶፋዎችን እንካቹ ስንል 👉 በ9 ቅርጫፎቻችን ስንጠበቅዎ በታላቅ ደስታ ነው 0910222244 / 0954111133 / 0954111100
ተጨማሪ ፎቶ ለመምረጥ ሊንኩን የጫኑት https://t.iss.one/wubeare
#ቻፓ
ቻፓ ፋይናንሺያል ቴክኖሎጅዎች አ.ማ (ቻፓ) ለአለም አቀፍ እና ለሀገር ውስጥ የኦንላይን ክፍያ መቀበያ አገልግሎቱን መጀመሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ አስታውቋል።
ከዚህ ቀደም ለንግድ ተቋማትም ሆነ ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በቀጥታ ክፍያ ለመፈጸም አስቻይ ሁኔታዎች ብዙ የተመቻቹ ባለመሆናቸው በእጅ አዙር የሚደረጉ ክፍያዎችን መጠቀም አስገዳጅ ነበር።
አሁን ላይ " ቻፖ " ከብሔራዊ ባንክ የክፍያ ሥርዓት ኦፕሬተር ፈቃድ በማግኘት ወደ ገቢያው ይዞት የገባው ሥርዓት ተጠቃሚዎች መግዛት የሚፈልጉትን እቃ/ የአገልግሎት ክፍያ በቀጥታ እዛው ላይ በሀገሪቱ ባሉ 9 ባንኮች እንዲሁም ቴሌብርና አለምአቀፍ የክፍያ መንገዶችን በመጠቀም መፈጸም ያስችላቸዋል።
ይህንን ለማድረግ የንግድ ድርጅቶች 6 መስመር ኮድ በራሳቸው ድረገጽ/መተግበሪያ ላይ በማስገባት (API Integeration) መገልገል የሚችሉ ሲሆን መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ተቋማት ደግሞ በቀላል መንገድ ከለጋሾች ድጋፍ መቀበል ያስችላቸዋል።
በቻፖ አሁን ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ አቢሲኒያ ባንክ፣ አዋሽ ባንክ፣ ህብረት ባንክ፣ ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ፣ ብርሃን ባንክ፣ አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ፣ አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ እና የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክን በመጠቀም ክፍያ መፈጸም ይቻላል።
ከአለምአቀፍ የክፍያ መንገዶች ደግሞ Visa፣ Mastercard፣ American Express፣ UnionPay፣ Discover፣ Diners Club፣ JCB እና PayPal በአገልግሎቱ የተካተቱ ናቸው።
@tikvahethiopia
ቻፓ ፋይናንሺያል ቴክኖሎጅዎች አ.ማ (ቻፓ) ለአለም አቀፍ እና ለሀገር ውስጥ የኦንላይን ክፍያ መቀበያ አገልግሎቱን መጀመሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ አስታውቋል።
ከዚህ ቀደም ለንግድ ተቋማትም ሆነ ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በቀጥታ ክፍያ ለመፈጸም አስቻይ ሁኔታዎች ብዙ የተመቻቹ ባለመሆናቸው በእጅ አዙር የሚደረጉ ክፍያዎችን መጠቀም አስገዳጅ ነበር።
አሁን ላይ " ቻፖ " ከብሔራዊ ባንክ የክፍያ ሥርዓት ኦፕሬተር ፈቃድ በማግኘት ወደ ገቢያው ይዞት የገባው ሥርዓት ተጠቃሚዎች መግዛት የሚፈልጉትን እቃ/ የአገልግሎት ክፍያ በቀጥታ እዛው ላይ በሀገሪቱ ባሉ 9 ባንኮች እንዲሁም ቴሌብርና አለምአቀፍ የክፍያ መንገዶችን በመጠቀም መፈጸም ያስችላቸዋል።
ይህንን ለማድረግ የንግድ ድርጅቶች 6 መስመር ኮድ በራሳቸው ድረገጽ/መተግበሪያ ላይ በማስገባት (API Integeration) መገልገል የሚችሉ ሲሆን መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ተቋማት ደግሞ በቀላል መንገድ ከለጋሾች ድጋፍ መቀበል ያስችላቸዋል።
በቻፖ አሁን ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ አቢሲኒያ ባንክ፣ አዋሽ ባንክ፣ ህብረት ባንክ፣ ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ፣ ብርሃን ባንክ፣ አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ፣ አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ እና የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክን በመጠቀም ክፍያ መፈጸም ይቻላል።
ከአለምአቀፍ የክፍያ መንገዶች ደግሞ Visa፣ Mastercard፣ American Express፣ UnionPay፣ Discover፣ Diners Club፣ JCB እና PayPal በአገልግሎቱ የተካተቱ ናቸው።
@tikvahethiopia
" ከፍተኛ የውሀ እጥረት ተከስቷል " - የአ/አ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጣን
የአዲስ አበባ ከተማ ውኃ እና ፍሳሽ ባለስልጣን ፤ በአቃቂ ከርሰ ምድር የውኃ ፕሮጀክት ውስጥ የሚገኙ አምስት የውኃ ጉድጓዶች በጎርፍና ደለል በመሞላታቸው ምክንያት በከተማዋ ከፍተኛ የውኃ እጥረት መከሰቱን አስታወቀ።
ባለስልጣኑ በቀን 20 ሺሕ ሜትር ኪዮብ ውኃ የማምረት አቅም ያላቸው አምስቱ የውኃ ጉድጓዶች ንፋስ ስልክና ቂርቆስ ክ/ከተሞችን ጨምሮ በርካታ የከተማዋን አካባቢዎች የሚሸፍኑ ሲሆን አሁን ሙሉ በሙሉ ማምረት አቁመዋል ብሏል።
በዘንድሮው የክረምት ወቅት ከመደበኛው በላይ የጎርፍ ፍሰት በመኖሩ ምክንያት የውኃ ጉድጓዶችን ከመሰል ችግሮች ለመጠበቅ በተሰራው የመከላከያ ግንብ መቆጣጠር እንዳልተቻለ ተጠቁሟል።
የውኃ እጥረቱን በጊዜያዊነት ለመቅረፍ በሳምንት ሁለት ወይም ሶስት ቀን ውኃ ያገኙ ከነበሩ አካባቢዎች በመቀነስ እጥረቱ ወደተከሰተባቸው አካባቢዎች እየተላከ እንደሆነ ተገልጿል።
የተፈጠረው ወቅታዊ ችግር እስኪፈታ ድረስ የከተማዋ ነዋሪዎች በትዕግስት እንዲጠባበቁ ባለስልጣኑ ጥሪ ማቅረቡን አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዘግቧል።
Via AMN
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ ውኃ እና ፍሳሽ ባለስልጣን ፤ በአቃቂ ከርሰ ምድር የውኃ ፕሮጀክት ውስጥ የሚገኙ አምስት የውኃ ጉድጓዶች በጎርፍና ደለል በመሞላታቸው ምክንያት በከተማዋ ከፍተኛ የውኃ እጥረት መከሰቱን አስታወቀ።
ባለስልጣኑ በቀን 20 ሺሕ ሜትር ኪዮብ ውኃ የማምረት አቅም ያላቸው አምስቱ የውኃ ጉድጓዶች ንፋስ ስልክና ቂርቆስ ክ/ከተሞችን ጨምሮ በርካታ የከተማዋን አካባቢዎች የሚሸፍኑ ሲሆን አሁን ሙሉ በሙሉ ማምረት አቁመዋል ብሏል።
በዘንድሮው የክረምት ወቅት ከመደበኛው በላይ የጎርፍ ፍሰት በመኖሩ ምክንያት የውኃ ጉድጓዶችን ከመሰል ችግሮች ለመጠበቅ በተሰራው የመከላከያ ግንብ መቆጣጠር እንዳልተቻለ ተጠቁሟል።
የውኃ እጥረቱን በጊዜያዊነት ለመቅረፍ በሳምንት ሁለት ወይም ሶስት ቀን ውኃ ያገኙ ከነበሩ አካባቢዎች በመቀነስ እጥረቱ ወደተከሰተባቸው አካባቢዎች እየተላከ እንደሆነ ተገልጿል።
የተፈጠረው ወቅታዊ ችግር እስኪፈታ ድረስ የከተማዋ ነዋሪዎች በትዕግስት እንዲጠባበቁ ባለስልጣኑ ጥሪ ማቅረቡን አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዘግቧል።
Via AMN
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ተቃውሞ እና ደስታ በጎረቤት ኬንያ ! ዛሬ በኬንያ የፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ይፋ መደረጉን ተከትሎ ውጤቱን እንደማይቀበሉ የገለፁ የራይላ ኦዲንጋ ደጋፊዎች ተቃውሞ ማሰማት መጀመራቸው ፤ በአንዳንድ ቦታዎችም አመፅ መቀስቀሳቸው ተሰምቷል። ከዚህ በተቃራኒው በጠባብ ውጤት እንዳሸነፉ የተነገረላቸው የዊሊያም ሩቶ ደጋፊዎች አደባባይ በመውጣት ደስታቸውን እየጨፈሩ በመግለፅ ላይ ናቸው። የራይላ ደጋፊዎች በተለይም በኪሱሙ…
" ውጤቱን አልቀበልም " - ኦዲንጋ
ራይላ ኦዲንጋ የምርጫውን ውጤት አልቀበለም ብለዋል።
ትላንትና ሰኞ የኬንያ ምርጫ ኮሚሽን የኬንያን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዊልያን ሩቶ ማሸነፋቸውን ማሳወቁ አይዘነጋም።
በቦማስ በተደረገው ስነስርዓት ወቅት ጭራሽ በማዕከሉ ያልተገኙት የሩቶ ተፎካካሪ ኦዲንጋ እስከ ዛሬ ከሰዓት ድረስ ስለ ምርጫው ምንም ሳይሉ ቆይተዋል።
ራይላ ኦዲንጋ ዛሬ ከሰዓት በሰጡት መግለጫ የምርጫውን ውጤት ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት እንደሌለውና እሳቸውም እንደማይቀበሉት አሳውቀዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ሁሉም ሰው እንዲረጋጋ እና ህግ እንዲያከብር አሳስበዋል።
@tikvahethiopia
ራይላ ኦዲንጋ የምርጫውን ውጤት አልቀበለም ብለዋል።
ትላንትና ሰኞ የኬንያ ምርጫ ኮሚሽን የኬንያን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዊልያን ሩቶ ማሸነፋቸውን ማሳወቁ አይዘነጋም።
በቦማስ በተደረገው ስነስርዓት ወቅት ጭራሽ በማዕከሉ ያልተገኙት የሩቶ ተፎካካሪ ኦዲንጋ እስከ ዛሬ ከሰዓት ድረስ ስለ ምርጫው ምንም ሳይሉ ቆይተዋል።
ራይላ ኦዲንጋ ዛሬ ከሰዓት በሰጡት መግለጫ የምርጫውን ውጤት ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት እንደሌለውና እሳቸውም እንደማይቀበሉት አሳውቀዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ሁሉም ሰው እንዲረጋጋ እና ህግ እንዲያከብር አሳስበዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኬንያ በኬንያ የተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ውጤት ዛሬ ሰኞ ከሰዓት በኋላ ይፋ ይደረጋል ተብሎ እየተጠበቀ ባለበት ጊዜ አለመግባባት እና ውዝግብ ተፈጥሯል። የፕሬዝዳንታዊ ምርጫውን ውጤት ያሳውቃሉ ተብለው በሚጠበቁት የኮሚሽኑ ባለሥልጣንት መካከል ክፍፍል መፈጠሩ ነው የተነገረው። በዚህም 4 የኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች በይፋ የፕሬዝዳንታዊ ምርጫው ውጤት ከሚነገርበት ማዕከል ውጪ መሃል ናይሮቢ በሚገኘው ሴሬና…
ራይላ ኦዲንጋ በመግለጫቸው ምን አሉ ?
የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር እና በወቅቱ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚደገፉት ራይላ ኦዲንጋ የምርጫ ውጤቱ ሕጋዊ ያልሆነ እና ተፈጻሚ የማይሆን ነው ብለዋል።
ኦዲንጋ በመግለጫቸው ፦
• ውጤቱን አልቀበልም ብለዋል።
• ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት እንደሚወስዱት ተናግረዋል።
• የኮሚሽኑን ዋና ሰብሰቢ ዋፉላ ቼቡካቲን " አምባገነን " ሲሉ በመጥራት ተችተዋቸዋል። ይፋ ያደረጉትንም ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ውጤት ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ አንቀበለውም ሲሉ ገልፀዋል።
• የኮሚሽኑ ዋና ሰብሳቢ የምርጫ ውጤቱን ይፋ ሲያደርጉ የአገሪቱን ሕገ-መንግሥት በመተላለፍ ትልቅ የሕግ ጥሰት ፈጽመዋል ብለዋል። በኮሚሽነሮች መካከል ልዩነት እያለ ዋፉላ ቼቡካቲ የምርጫ ውጤቱን ይፋ ማድረጋቸው ስህተት ነው ሲሉ ገልፀዋል።
NB. የኬንያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫን ያስፈጸመው ገለልተኛ የድንበር እና ምርጫ ኮሚሽን 7 ኮሚሽነሮች ያሉት ሲሆን ከእነዚህ መካከል 4ቱ በፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ውጤቱ አለመስማማታቸውን ትላንት መግለፃቸው ይታወሳል።
ከፍተኛ ደጋፊ ያላቸው ራይላ ኦዲንጋ የምርጫውን ውጤት አልቀበልም ማለታቸው በአገሪቱ ምርጫውን ተከትሎ ግጭት እንዲቀሰቀስ ሊያደርግ ይችላል የሚሉ ስጋቶች ከአሁኑ አይለዋል።
መረጃው ቢቢሲ የራይላን ኦዲንጋን መግለጫ ዋቢ አድርጎ ካዘጋጀው የተወሰደ ሲሆን ፎቶው ከNTV የቀጥታ ስርጭት የተወሰደ ነው።
@tikvahethiopia
የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር እና በወቅቱ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚደገፉት ራይላ ኦዲንጋ የምርጫ ውጤቱ ሕጋዊ ያልሆነ እና ተፈጻሚ የማይሆን ነው ብለዋል።
ኦዲንጋ በመግለጫቸው ፦
• ውጤቱን አልቀበልም ብለዋል።
• ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት እንደሚወስዱት ተናግረዋል።
• የኮሚሽኑን ዋና ሰብሰቢ ዋፉላ ቼቡካቲን " አምባገነን " ሲሉ በመጥራት ተችተዋቸዋል። ይፋ ያደረጉትንም ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ውጤት ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ አንቀበለውም ሲሉ ገልፀዋል።
• የኮሚሽኑ ዋና ሰብሳቢ የምርጫ ውጤቱን ይፋ ሲያደርጉ የአገሪቱን ሕገ-መንግሥት በመተላለፍ ትልቅ የሕግ ጥሰት ፈጽመዋል ብለዋል። በኮሚሽነሮች መካከል ልዩነት እያለ ዋፉላ ቼቡካቲ የምርጫ ውጤቱን ይፋ ማድረጋቸው ስህተት ነው ሲሉ ገልፀዋል።
NB. የኬንያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫን ያስፈጸመው ገለልተኛ የድንበር እና ምርጫ ኮሚሽን 7 ኮሚሽነሮች ያሉት ሲሆን ከእነዚህ መካከል 4ቱ በፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ውጤቱ አለመስማማታቸውን ትላንት መግለፃቸው ይታወሳል።
ከፍተኛ ደጋፊ ያላቸው ራይላ ኦዲንጋ የምርጫውን ውጤት አልቀበልም ማለታቸው በአገሪቱ ምርጫውን ተከትሎ ግጭት እንዲቀሰቀስ ሊያደርግ ይችላል የሚሉ ስጋቶች ከአሁኑ አይለዋል።
መረጃው ቢቢሲ የራይላን ኦዲንጋን መግለጫ ዋቢ አድርጎ ካዘጋጀው የተወሰደ ሲሆን ፎቶው ከNTV የቀጥታ ስርጭት የተወሰደ ነው።
@tikvahethiopia
የአስተዳደር ወሰን !
በአዲስ አበባ ከተማ እና የፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን የአስተዳደር ወሰን ማካለል ስራ መጠናቀቁ ተገለፀ።
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የተደረሰውን ስምምነት እና ውሳኔ " ታሪካዊ እና ዘመን ተሻጋሪ ነው " ሲሉ ገልፀዋል።
ኦሮምያም በሚያስተዳድርበት ፤ አዲስ አበባም ስታስተዳድርበት በነበረው ቦታ እንድትቀጥል ከስምምነት መደረሱን ከንቲባ አዳነች አሳውቀዋል።
በኦሮምያ የፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን ውስጥ በመግባት በርቀት በአዲስ አበባ የተገነቡ ኮንዶሚኒየሞች ለአብነት ኮየፈጨ፤ ቱሉዲምቱ በከፊልና ጀሞ ቁጥር ሁለት የሚገኙበትን ወደ ኦሮምያ ልዩ ዞን ተካለዋል ብለዋል።
ኦሮምያ የገነባው የቆጣሪ ኮንዶሚኒየም ወይም ለቡ አካባቢ ከፉሪ ሃናና የኦሮምያ ኮንዶሚኒየሞች ጨምሮ እስከ ቀርሳ ወንዝ ያለውን ወደ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እንዲካለሉ በማድረግ ስምምነት መፈፀሙን ገልፀዋል።
ከዚያ ውጪ ሁሉም ባለበት ቦታ እንዲያስተዳድር ስምምነት ላይ መደረሱን ከንቲባ አዳነች አቤቤ አሳውቀዋል።
የአስተዳደር ወሰን በሚነካባቸው አካባቢዎች፦
- የትኛውም አይነት መንግስታዊ አገልግሎት እንደማይቋረጥ፤
- የአገልግሎትና የፀጥታ ስራዎች በሁለቱም ወገን በጋራ በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚሰራ ፤
- በግንባታ ሂደት ላይ ያሉ ፕሮጀክቶች እንደማይቆሙ፤
- የትምህርት አሰጣጥ ሂደቱና የተማሪዎች የቋንቋ ጉዳይ በነበረበት እንደሚቀጥል፤
- የሚሰጡ መንግስታዊ አገልግሎቶች ላይ ቋንቋ ምንም አይነት ተፅእኖ እንዳያሳርፍ እንደሚደረግ አስረድተዋል።
(ከንቲባዋ ከአስተዳደር ወሰን ውሳኔ ጋር በተያያዘ ያሰራጩት መልዕክት ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ እና የፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን የአስተዳደር ወሰን ማካለል ስራ መጠናቀቁ ተገለፀ።
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የተደረሰውን ስምምነት እና ውሳኔ " ታሪካዊ እና ዘመን ተሻጋሪ ነው " ሲሉ ገልፀዋል።
ኦሮምያም በሚያስተዳድርበት ፤ አዲስ አበባም ስታስተዳድርበት በነበረው ቦታ እንድትቀጥል ከስምምነት መደረሱን ከንቲባ አዳነች አሳውቀዋል።
በኦሮምያ የፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን ውስጥ በመግባት በርቀት በአዲስ አበባ የተገነቡ ኮንዶሚኒየሞች ለአብነት ኮየፈጨ፤ ቱሉዲምቱ በከፊልና ጀሞ ቁጥር ሁለት የሚገኙበትን ወደ ኦሮምያ ልዩ ዞን ተካለዋል ብለዋል።
ኦሮምያ የገነባው የቆጣሪ ኮንዶሚኒየም ወይም ለቡ አካባቢ ከፉሪ ሃናና የኦሮምያ ኮንዶሚኒየሞች ጨምሮ እስከ ቀርሳ ወንዝ ያለውን ወደ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እንዲካለሉ በማድረግ ስምምነት መፈፀሙን ገልፀዋል።
ከዚያ ውጪ ሁሉም ባለበት ቦታ እንዲያስተዳድር ስምምነት ላይ መደረሱን ከንቲባ አዳነች አቤቤ አሳውቀዋል።
የአስተዳደር ወሰን በሚነካባቸው አካባቢዎች፦
- የትኛውም አይነት መንግስታዊ አገልግሎት እንደማይቋረጥ፤
- የአገልግሎትና የፀጥታ ስራዎች በሁለቱም ወገን በጋራ በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚሰራ ፤
- በግንባታ ሂደት ላይ ያሉ ፕሮጀክቶች እንደማይቆሙ፤
- የትምህርት አሰጣጥ ሂደቱና የተማሪዎች የቋንቋ ጉዳይ በነበረበት እንደሚቀጥል፤
- የሚሰጡ መንግስታዊ አገልግሎቶች ላይ ቋንቋ ምንም አይነት ተፅእኖ እንዳያሳርፍ እንደሚደረግ አስረድተዋል።
(ከንቲባዋ ከአስተዳደር ወሰን ውሳኔ ጋር በተያያዘ ያሰራጩት መልዕክት ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
#MohamedSalah
ከሰሞኑን በግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን 5 ሺህ ምዕመናን በተሰበሰቡበት በተነሳ የእሳት አደጋ የቤተክርስቲያኑን አገልጋይ ካህን እንዲሁም እድሜያቸው ከ3 እስከ 16 ዓመት የሚሆኑ 18 ሕጻናትን ጨምሮ 41 ምዕመናን ሕይወታቸውን አጥተው ነበር።
ይህን እጅግ አሳዛኝ ክስተት የሰማው የ #ሊቨርፑል እግር ኳስ ክለብ ኮከቡ ግብፃዊው ሞሀመድ ሳላህ ጉዳት የደረሰባት ቤተክርስቲያን ዳግም እንድትገነባ ለማገዝ ድጋፍ ማድረጉ ተነግሯል።
ሞሀመድ ሳላህ ድጋፍ ያደረገው ሶስት ሚሊዮን የግብፅ ፓውንድ መሆኑ ተገልጿል።
የሳላህ ድጋፍ በዝነኛው የግብፅ ስፖርት ጋዜጠኛ ኢብራሂም አብድል ጋዋድ የተረጋገጠ ሲሆን የተጫዋቹን በጎ ተግባር የሰሙ ሁሉ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ከፍተኛ ምስጋና እያቀረቡለት ይገኛሉ ሲል ዘ ናሽናል በድረገፁ ላይ አስነብቧል።
ምንጭ፦ www.thenationalnews.com (Cairo)
@tikvahethiopia
ከሰሞኑን በግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን 5 ሺህ ምዕመናን በተሰበሰቡበት በተነሳ የእሳት አደጋ የቤተክርስቲያኑን አገልጋይ ካህን እንዲሁም እድሜያቸው ከ3 እስከ 16 ዓመት የሚሆኑ 18 ሕጻናትን ጨምሮ 41 ምዕመናን ሕይወታቸውን አጥተው ነበር።
ይህን እጅግ አሳዛኝ ክስተት የሰማው የ #ሊቨርፑል እግር ኳስ ክለብ ኮከቡ ግብፃዊው ሞሀመድ ሳላህ ጉዳት የደረሰባት ቤተክርስቲያን ዳግም እንድትገነባ ለማገዝ ድጋፍ ማድረጉ ተነግሯል።
ሞሀመድ ሳላህ ድጋፍ ያደረገው ሶስት ሚሊዮን የግብፅ ፓውንድ መሆኑ ተገልጿል።
የሳላህ ድጋፍ በዝነኛው የግብፅ ስፖርት ጋዜጠኛ ኢብራሂም አብድል ጋዋድ የተረጋገጠ ሲሆን የተጫዋቹን በጎ ተግባር የሰሙ ሁሉ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ከፍተኛ ምስጋና እያቀረቡለት ይገኛሉ ሲል ዘ ናሽናል በድረገፁ ላይ አስነብቧል።
ምንጭ፦ www.thenationalnews.com (Cairo)
@tikvahethiopia
#USA
የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን #በአየር_ንብረትና #በጤና ዙርያ የቀረቡ ረቂቅ ሕጎች ላይ ፊርማቸውን እንዳኖሩ ቢቢሲ ዘግቧል።
ባይደን በፊርማቸው ያጸኑት ሕግ በሃብታሞች ላይ ጠንከር ያለ ግብር የሚጥል ነው።
ይህ ረቂቅ ሕግ ከፍተኛ ገቢ ባላቸው ኩባንያዎች ላይ ግብር በመጣል በአየር ንብረት ለውጥና በጤና ዙርያ ለሚሠሩ ሥራዎች የሚውል ገንዘብ የሚያስገኝ እንዲሆን የተዘጋጀ ነው ተብሏል።
ጆ ባይደን ትናንት በረቂቅ ሕጉ ላይ ፊርማቸውን በማኖር ሕግ እንዲሆን አጽንተውታል።
ይህ ሕግ ከዚህ ወዲያ በጤና ዙርያ በሐኪም የሚታዘዙ መድኃኒቶች ዋጋ እንዲስተካከል የሚያደርግ ነው።
የአሜሪካ የሕዝብ ተወካዮች ለዓመታት በሚታዘዙ መድኃኒቶች ዋጋ ላይ #ቅናሽ እንዲደረግ ሲወተውቱ የቆዩትን ጥያቄ ይመልሳል ተብሏል።
ተጨማሪ : https://telegra.ph/BBC-08-17
@tikvahethiopia
የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን #በአየር_ንብረትና #በጤና ዙርያ የቀረቡ ረቂቅ ሕጎች ላይ ፊርማቸውን እንዳኖሩ ቢቢሲ ዘግቧል።
ባይደን በፊርማቸው ያጸኑት ሕግ በሃብታሞች ላይ ጠንከር ያለ ግብር የሚጥል ነው።
ይህ ረቂቅ ሕግ ከፍተኛ ገቢ ባላቸው ኩባንያዎች ላይ ግብር በመጣል በአየር ንብረት ለውጥና በጤና ዙርያ ለሚሠሩ ሥራዎች የሚውል ገንዘብ የሚያስገኝ እንዲሆን የተዘጋጀ ነው ተብሏል።
ጆ ባይደን ትናንት በረቂቅ ሕጉ ላይ ፊርማቸውን በማኖር ሕግ እንዲሆን አጽንተውታል።
ይህ ሕግ ከዚህ ወዲያ በጤና ዙርያ በሐኪም የሚታዘዙ መድኃኒቶች ዋጋ እንዲስተካከል የሚያደርግ ነው።
የአሜሪካ የሕዝብ ተወካዮች ለዓመታት በሚታዘዙ መድኃኒቶች ዋጋ ላይ #ቅናሽ እንዲደረግ ሲወተውቱ የቆዩትን ጥያቄ ይመልሳል ተብሏል።
ተጨማሪ : https://telegra.ph/BBC-08-17
@tikvahethiopia