TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ሶማሌክልል : በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል በኩል ሀገርን ሊዳፈር የሞከረው የአልሸባብ የሽብር ቡድን በክልሉ ልዩ ኃይል የማያዳግም ፣ ሁሌም የማይረሳው አስተማሪ ቅጣት መቀጣቱ ይታወቃል።

ባለፉት ቀናት በአፍዴር ዞን ቆህሌ ወረዳ በሁልሁል ንዑስ ቀበሌ ላይ ሰርጎ በገባው አልሸባብ ላይ በተካሄደው ጠንካራ ኦፕሬሽን ድል ያደረገው የሶማሌ ልዩ ኃይል ለሌላ ግዳጅ ደግሞ ወደ ሀገሪቱ ድንበር ተሸኝቷል።

በሌላ መረጃ ፦ የሶማሊያ ፌዴራሉ መንግስት ባልፈው ሳምንት የአልሸባብ የሽብር ቡድን ከባኮል ግዛት ከፍቶት በነበረው ጥቃት ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች የምግብ እና የመድሃኒት ድጋፎችን ልኳል። አካባቢው በድርቅም የተጎዳ ነው። ባኮል በ420 ኪ/ሜ ከሞቃዲሹ የሚርቅ ሲሆን ከኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ጋር የሚዋሰን የሀገሪቱ ክፍል ነው።

Photo Credit : Somali Region Communication

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ🇪🇹

የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ሌሊት በሚደረጉ ተጠባቂ ውድድሮች ፍፃሜውን የሚያገኝ ይሆናል።

በዛሬው የመጨረሻ የውድድር ቀን የሀገራችን ልጆች የሚሳተፉባቸው ውድድሮች ይካሄዳሉ።

🏟️ የወንዶች 5,000 ሜትር #ፍፃሜ

🇪🇹 ሰለሞን ባረጋ
🇪🇹 ሙክታር እድሪስ
🇪🇹 ዮሚፍ ቀጀልቻ

(ሰዓት - ሌሊት 10:05)

🏟️ የሴቶች 800 ሜትር #ፍፃሜ

🇪🇹 ድርቤ ወልተጂ

(ሰዓት - ሌሊት 10:35)

ድል ለሀገራችን ኢትዮጵያ 🇪🇹 !!

@tikvahethsport @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ🇪🇹 የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ሌሊት በሚደረጉ ተጠባቂ ውድድሮች ፍፃሜውን የሚያገኝ ይሆናል። በዛሬው የመጨረሻ የውድድር ቀን የሀገራችን ልጆች የሚሳተፉባቸው ውድድሮች ይካሄዳሉ። 🏟️ የወንዶች 5,000 ሜትር #ፍፃሜ ፦ 🇪🇹 ሰለሞን ባረጋ 🇪🇹 ሙክታር እድሪስ 🇪🇹 ዮሚፍ ቀጀልቻ (ሰዓት - ሌሊት 10:05) 🏟️ የሴቶች 800 ሜትር #ፍፃሜ ፦ 🇪🇹 ድርቤ ወልተጂ (ሰዓት …
#ተጀመረ

እጅግ በጉጉት የሚጠበቀው የወንዶች 5000 ሜትር ፍፃሜ ውድድር ተጀምሯል።

ውድድሩ ፍጥነትን ከጥንካሬ ጋር አዳምሮ የሚጠይቅ ነው።

ሀገራችን በውድድሩ ፦

🇪🇹 ሙክታር እድሪስ
🇪🇹 ዩሚፍ ቀጀልቻ
🇪🇹 ሰለሞን ባረጋ ተወክላለች።

ትላንት ለሊት በሴቶች 5 ሺህ ሜትር ከከፍተኛ የቡድን ስራ ጋር የተመዘገበው ድል ትልቅ የሞራል ስንቅ እንደሚሆናቸው አንጠራጠርም።

ድል ለሀገራችን 🇪🇹❤️ !

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
3 ዙር ይቀራል ! የወንዶች 5 ሺህ ሜትር ውድድር እጅግ ፈጣን ከፍተኛ ፉክክር እየተካሄደባት ነው። የሀገራችን ልጆች ከመሪዎቹ በቅርብ ርቀት በመሆን ባለድል ለመሆን እየተፋለሙ ነው። @tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ

በወንዶች 5 ሺህ ሜትር ድል አልቀናንም፦

🇪🇹 ዩሚፍ ቀጀልቻ 8ኛ
🇪🇹 ሰለሞን ባረጋ 12ኛ
🇪🇹 ሙክታር እድሪስ 13ኛ ሆነው አጠናቀዋል።

በ10 ሺህ ሜትር ፍፃሜ ውድድር ያልተገኘው ድል በዚህኛው ውድድር ይገኛል ተብሎ ተጠብቆ ነበር፤ ነገር ግን የወንዶች 5 ሺህ ሜትር እንደተጠበቀው አልሆነም።

የውድድሩ የወርቅ፣ ብር እና ነሀስ ባለድሎች ፦

1ኛ ኖርዌይ 🥇
2ኛ ኬንያ 🥈
3ኛ ዩጋንዳ 🥉

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ተጀመረ ሀገራችን በድርቤ ወልተጂ የተወከለችበት የ800 ሜትር የሴቶች #ፍፃሜ ውድድር ተጀምሯል። ድል ለሀገራችን 🇪🇹❤️ ! @tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ🇪🇹

በ800 ሜትር የሴቶች ፍፃሜ ብቸኛዋ የሀገራችን ተወካይ ድርቤ ወልተጂ አራተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች። ነሀስ ለማግኘት ከፍተኛ ትግል ነው ያደረገችው 👏

ውድድሩን ፦

1ኛ አሜሪካ 🥇(ወርቅ)
2ኛ እንግሊዝ 🥈(ብር)
3ኛ ኬንያ 🥉(ነሀስ) በመሆን አጠናቀዋል።

ሀገራችን #ኢትዮጵያ በተለይም #በሴቶች ከፍተኛ ድል ያስመዘገበችበት የኦሪገን ዓለም ሻምፒዮና በዚህ አብቅቷል።

@tikvahethsport
#ኢትዮጵያ❤️

ሀገራችን ኢትዮጵያ ከፍተኛ ድል ያስመዘገበችበት የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጠናቋል።

#ከዓለም ከአሜሪካ ቀጥላ ሁለተኛ እንዲሁም #ከአፍሪካ ቀዳሚውን ደረጃ በመያዝ ነው ያጠናቀቀችው።

በዓለም ሻምፒዮናው 4 ወርቆችን ያገኘን ሲሆን የዘንድሮው ውድድር በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሆኗል።

ከተገኙት አራት #ወርቆች 🥇 መካከል ታምራት ቶላ በማራቶን ያገኘው ወርቅ በዓለም ሻምፒዮናው በወንዶች የተገኘው #ብቸኛው ወርቅ ነው።

ለሀገራቸው ሜዳሊያ ያስገኙ አትሌቶቻችን እነማን ናቸው ?

ወርቅ 🥇

🇪🇹 ለተሰንበት ግደይ
🇪🇹 ጉዳፍ ፀጋይ
🇪🇹 ጎተይቶም ገ/ስላሴ
🇪🇹 ታምራት ቶላ

ብር🥈

🇪🇹 ወርቅውሀ ጌታቸው
🇪🇹 ሞስነት ገረመው
🇪🇹 ለሜቻ ግርማ
🇪🇹 ጉዳፍ ፀጋይ

ነሐስ🥉

🇪🇹 ዳዊት ስዩም
🇪🇹 መቅደስ አበበ

አጠቃላይ ከተገኘው 10 ሜዳሊያ ሰባቱ በሴቶች የተገኘ ነው፤ የቀረው 3 ሜዳሊያ ደግሞ በወንዶች ውድድር የተገኘ ነው።

የዓለም ሻምፒዮናው ምንም እንኳን ከፍተኛው ድል የተመዘገበበት ቢሆንም በወንዶች ውድድሮች ላይ የተሻለ መስራት እንደሚጠይቅ የሚጠቁም ነው።

የአትሌቲክስ ቡድናችን ወደ ሀገሩ ሲመለስ የጀግና ፣ የክብር አቀባበል እንደሚደረግለት ይጠበቃል።

ውድ አትሌቶቻችን ፤ ላደረጋችሁት ከፍተኛ ተጋድሎ ላስመዘገባችሁት ድል ፣ የሀገራችሁን ህዝብ ክብር ከፍ ስላደረጋችሁ ምስጋና ይገባችኃል።

እንኳን ደስ አለን 🇪🇹❤️ !

@tikvahethiopia @tikvahethsport