#ETHIOPIA
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፤ ትላንት ባካሄደው ጉባኤ መጅሊሱን ለቀጣዮቹ 4 አመታት የሚመሩ አመራሮች ምርጫ መካሄዱን በተረጋገጠው የማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ አሳውቋል።
ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ፕሬዜዳንት፣ ሸይኽ አብዱልከሪም በድረዲን ተ/ም/ፕሬዜዳንት እና አብዱልዐዚዝ አብዱልወሌ ምክትል ፕሬዜዳንት፣ ሸይኽ ሀሚድ ሙሳ ዋና ፀሀፊ ሆነው መመረጣቸውን ጠቅላይ ም/ቤቱ አሳውቋል።
ተመራጩ ፕሬዜዳንት ሸይኽ ኢብራሂም ቱፋ ከምርጫው በኃላ ባሰሙት ንግግር የህዝበ ሙስሊሙን አንድነት ለማስጠበቅ በትኩረት እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።
ትላንት ከተካሄደው ጉባኤ በኃላ አዲስ የተመረጡ አመራሮች በይፋ ስራ መጀመራቸውን ያበሰሩ ሲሆን ከቀድሞው የምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዜዳንት ዶ/ር ጄይላን ከድር እጅ የፅ/ቤቱን ቁልፍ መረከባቸውን ምክር ቤቱ በማህበራዊ ትስስር ገፁ አሳውቋል።
ትላንት በነበረው ርክክብ ወቅት እና በጉባኤው ላይ ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር እድሪስን ጨምሮ ሌሎችም አባቶች እንዳልተገኙ ለማወቅ ተችሏል። ከትላንት ምርጫ ጋር በተያያዘ ቅሬታ አለን ያሉ ወገኖች ቅሬታቸውን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሲያጋሩ ተመልክተናል።
ከጉባኤው አንድ ቀን ቀደም ብሎም በተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር እድሪስ የተመራ ስብሰባ ተካሂዶ የነበረ ሲሆን በዚሁ ገባኤ ላይ በትላንትናው ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ፍቃደኛ እንዳልሆኑ ባወጡት መግለጫ አሳውቀው ነበር።
ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር እድሪስ ችግሮች ከተስተካከሉ ለውይይት፣ ለመፍትሄ ፣ለሰላም ዝግጁ ነን ያሉ ሲሆን መንግስት ያለውን ችግር በአስቸኳይ እንዲያስተካክል ፤ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትርም ዑለማውን እና የሃይማኖት አባቶችን ቀርበው እንዲያነጋግሩ እና ችግሩ እንዲያወያዩ ጠይቀዋል።
ያንብቡ : telegra.ph/EIASC-07-19
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፤ ትላንት ባካሄደው ጉባኤ መጅሊሱን ለቀጣዮቹ 4 አመታት የሚመሩ አመራሮች ምርጫ መካሄዱን በተረጋገጠው የማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ አሳውቋል።
ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ፕሬዜዳንት፣ ሸይኽ አብዱልከሪም በድረዲን ተ/ም/ፕሬዜዳንት እና አብዱልዐዚዝ አብዱልወሌ ምክትል ፕሬዜዳንት፣ ሸይኽ ሀሚድ ሙሳ ዋና ፀሀፊ ሆነው መመረጣቸውን ጠቅላይ ም/ቤቱ አሳውቋል።
ተመራጩ ፕሬዜዳንት ሸይኽ ኢብራሂም ቱፋ ከምርጫው በኃላ ባሰሙት ንግግር የህዝበ ሙስሊሙን አንድነት ለማስጠበቅ በትኩረት እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።
ትላንት ከተካሄደው ጉባኤ በኃላ አዲስ የተመረጡ አመራሮች በይፋ ስራ መጀመራቸውን ያበሰሩ ሲሆን ከቀድሞው የምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዜዳንት ዶ/ር ጄይላን ከድር እጅ የፅ/ቤቱን ቁልፍ መረከባቸውን ምክር ቤቱ በማህበራዊ ትስስር ገፁ አሳውቋል።
ትላንት በነበረው ርክክብ ወቅት እና በጉባኤው ላይ ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር እድሪስን ጨምሮ ሌሎችም አባቶች እንዳልተገኙ ለማወቅ ተችሏል። ከትላንት ምርጫ ጋር በተያያዘ ቅሬታ አለን ያሉ ወገኖች ቅሬታቸውን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሲያጋሩ ተመልክተናል።
ከጉባኤው አንድ ቀን ቀደም ብሎም በተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር እድሪስ የተመራ ስብሰባ ተካሂዶ የነበረ ሲሆን በዚሁ ገባኤ ላይ በትላንትናው ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ፍቃደኛ እንዳልሆኑ ባወጡት መግለጫ አሳውቀው ነበር።
ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር እድሪስ ችግሮች ከተስተካከሉ ለውይይት፣ ለመፍትሄ ፣ለሰላም ዝግጁ ነን ያሉ ሲሆን መንግስት ያለውን ችግር በአስቸኳይ እንዲያስተካክል ፤ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትርም ዑለማውን እና የሃይማኖት አባቶችን ቀርበው እንዲያነጋግሩ እና ችግሩ እንዲያወያዩ ጠይቀዋል።
ያንብቡ : telegra.ph/EIASC-07-19
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትኩረት📣 ነዋሪዎችን ከፍተኛ ስጋት ላይ የጣለው የፀጥታ ችግር ! ከቲክቫህ ቤተሰብ አባል ከአጣዬ አካባቢ ፦ " እንደ ሁል ጊዜው ሁሉ አጣዬ ከተማ ዳግም ከፍተኛ የፀጥታ ስጋት ውስጥ ገብታለች። ይሄም የሆነው በሰሜን ሸዋ እና በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር አዋሳኝ ቦታዎች ዳግም ግጭት በመቀስቀሱ ነው። ትላንት ማለትም በ02/11/2014 " የቤት እንሰሶች የተዘራ ሰብልን በሉብን " በማለት ልዩ ቦታው…
#Update
" 4 የፖለቲካ አመራሮች እና አንድ የፖሊስ አመራር ላይ እርምጃ ተወስዷል " - አቶ ጀማል ሀሰን
ከጥቂት ቀናት በፊት በሰሜን ሸዋ ዞን እና በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር አዋሳኝ ቦታዎች ተከስቶ የነበረውን ግጭት ማብረድ የተቻለ ሲሆን ችግሩን መከላከል አልቻሉም በተባሉ ላይ እርንጃ እየተወሰደ ነው።
የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር የህዝብን ሰላም፣ ደህንነት አላረጋገጡም ባላቸው አመራሮች ላይ ፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አሳውቋል።
የብሄረሰብ አስተዳደሩ ኮሚኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ጀማል ሀሰን ለቪኦኤ በሰጡት ቃል ፥ " አምስት አመራሮች ላይ እምርጃ ተወስዷል። አራቱ የፖለቲካ አመራሮች ናቸው አንድ የፖሊስ አመራር ደግሞ በህግ ተጠያቂ እንዲሆን በቁጥጥር ስር አውለናል " ብለዋል።
ፖሊሶች አስፈላጊውን እርምጃ ወስደው ጉዳዩን ማብረድ ይችሉ ነበር ከስምሪት እና ተያያዥ ጉዳዮች ጋር ተገምግሞ በቁጥጥር ስር የማዋል ስራ ተሰርቷል ሲሉ ገልፀዋል።
እየተወሰደ ያለው እምርጃ እስከ ታች ቀበሌ እንደሚደርስም ገልፀዋል።
የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ እና ምክትላቸው እንዲሁም ሁለት የወረዳው የድርጅት አመራሮች የፖለቲካ እርምጃ እንደተወሰደባቸው ገልፀው ከስልጣናቸው እንዲነሱ ተደርገዋል ብለዋል።
ያንብቡ : https://telegra.ph/VOA-07-19
@tikvahethiopia
" 4 የፖለቲካ አመራሮች እና አንድ የፖሊስ አመራር ላይ እርምጃ ተወስዷል " - አቶ ጀማል ሀሰን
ከጥቂት ቀናት በፊት በሰሜን ሸዋ ዞን እና በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር አዋሳኝ ቦታዎች ተከስቶ የነበረውን ግጭት ማብረድ የተቻለ ሲሆን ችግሩን መከላከል አልቻሉም በተባሉ ላይ እርንጃ እየተወሰደ ነው።
የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር የህዝብን ሰላም፣ ደህንነት አላረጋገጡም ባላቸው አመራሮች ላይ ፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አሳውቋል።
የብሄረሰብ አስተዳደሩ ኮሚኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ጀማል ሀሰን ለቪኦኤ በሰጡት ቃል ፥ " አምስት አመራሮች ላይ እምርጃ ተወስዷል። አራቱ የፖለቲካ አመራሮች ናቸው አንድ የፖሊስ አመራር ደግሞ በህግ ተጠያቂ እንዲሆን በቁጥጥር ስር አውለናል " ብለዋል።
ፖሊሶች አስፈላጊውን እርምጃ ወስደው ጉዳዩን ማብረድ ይችሉ ነበር ከስምሪት እና ተያያዥ ጉዳዮች ጋር ተገምግሞ በቁጥጥር ስር የማዋል ስራ ተሰርቷል ሲሉ ገልፀዋል።
እየተወሰደ ያለው እምርጃ እስከ ታች ቀበሌ እንደሚደርስም ገልፀዋል።
የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ እና ምክትላቸው እንዲሁም ሁለት የወረዳው የድርጅት አመራሮች የፖለቲካ እርምጃ እንደተወሰደባቸው ገልፀው ከስልጣናቸው እንዲነሱ ተደርገዋል ብለዋል።
ያንብቡ : https://telegra.ph/VOA-07-19
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Peace የተደራዳሪ ቡድኑ ! የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት #በሰላም_ድርድር እንዲፈታ ገዢው የብልፅግና ፓርቲ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወቃል። በዚህም መሰረት በፌዴራል መንግሥት በኩል የሰላም ተደራዳሪ ቡድን መሰየሙ ተረጋግጧል። የቡድኑ አባላት ፦ 1ኛ. አቶ ደመቀ መኮንን ➡️ ሰብሳቢ 2ኛ. ዶ/ር ጌድዮን ጢሞቲዎስ ➡️ አባል 3ኛ. አቶ ተመስገን ጥሩነህ ➡️ አባል 4ኛ. አምባሳደር ሀሰን አብዱልቃድር ➡️…
#Update
ከጥቂት ሳምንታት በፊት የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በሰላም መቋጫ እንዲያገኝ የፌዴራል መንግስት የሰላም ተደራዳሪ ቡድን መቋቋሙ ይታወሳል።
የተደራዳሪ ቡድን አባላቱም ይፋ መደረጋቸው አይዘነጋም።
አሁን ደግሞ ትግራይ ክልልን እያስተዳደረ የሚገኘው ህወሓት ተደራዳሪ ቡድን ማቋቋሙን ገልጿል።
የህወሓት ቃል አቀባይ ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የዜና ወኪል በሰጡት ቃል ፤ ለድርድር የሚሆን ልዑክ ወደ #ናይሮቢ ለመላክ ዝግጁ እንሆናለን ብለዋል።
በከፍተኛ ሥልጣን ደረጃ የሚገኙ አባላት ያሉት ኮሚቴም ተቋቁሟል ሲሉ አሳውቀዋል።
ተደራዳሪ ሊሆኑ የሚችሉ ግለሰቦች እነማን እንደሆኑ እንዲሁም ቁጥራቸውን በተመለከተ የተባለ ነገር የለም።
ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ መንግስት ከህወሓት ጋር የሚደረገው ምንም አይነት ድርድር ሊመራ የሚችለው በአፍሪካ ኅብረት ብቻ መሆኑን ያስታወቀ ሲሆን፣ የህወሓት አመራሮች ድርድሩ በኅብረቱ ጥላ ስር ብቻ እንዲሆን እንደማይፈልጉ ገልጸዋል።
" ሁሉንም የድርድር ሂደቶች ለአፍሪካ ኅብረት መስጠቱ ለእኛ በጣም ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው” ያሉት አቶ ጌታቸው፣ ማንኛውም ድርድር በሰላም ጥረት ውስጥ ንቁ ሚና የተጫወቱትን ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታን ማካተት አለበት " ብለዋል።
መረጃው የአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ /ቢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
ከጥቂት ሳምንታት በፊት የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በሰላም መቋጫ እንዲያገኝ የፌዴራል መንግስት የሰላም ተደራዳሪ ቡድን መቋቋሙ ይታወሳል።
የተደራዳሪ ቡድን አባላቱም ይፋ መደረጋቸው አይዘነጋም።
አሁን ደግሞ ትግራይ ክልልን እያስተዳደረ የሚገኘው ህወሓት ተደራዳሪ ቡድን ማቋቋሙን ገልጿል።
የህወሓት ቃል አቀባይ ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የዜና ወኪል በሰጡት ቃል ፤ ለድርድር የሚሆን ልዑክ ወደ #ናይሮቢ ለመላክ ዝግጁ እንሆናለን ብለዋል።
በከፍተኛ ሥልጣን ደረጃ የሚገኙ አባላት ያሉት ኮሚቴም ተቋቁሟል ሲሉ አሳውቀዋል።
ተደራዳሪ ሊሆኑ የሚችሉ ግለሰቦች እነማን እንደሆኑ እንዲሁም ቁጥራቸውን በተመለከተ የተባለ ነገር የለም።
ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ መንግስት ከህወሓት ጋር የሚደረገው ምንም አይነት ድርድር ሊመራ የሚችለው በአፍሪካ ኅብረት ብቻ መሆኑን ያስታወቀ ሲሆን፣ የህወሓት አመራሮች ድርድሩ በኅብረቱ ጥላ ስር ብቻ እንዲሆን እንደማይፈልጉ ገልጸዋል።
" ሁሉንም የድርድር ሂደቶች ለአፍሪካ ኅብረት መስጠቱ ለእኛ በጣም ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው” ያሉት አቶ ጌታቸው፣ ማንኛውም ድርድር በሰላም ጥረት ውስጥ ንቁ ሚና የተጫወቱትን ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታን ማካተት አለበት " ብለዋል።
መረጃው የአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ /ቢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
" ተዘርፈናል አፋልጉን "
የማየትና መስማት የተሳናቸው ህጻናት ለትራንስፖርት የሚገለገሉበት መኪና ተሰርቋል።
የኢትዮጵያ ማየትና መስማት የተሳናቸው ብሔራዊ ማኅበር ማየትና መስማት በተሳናቸው ሰዎች የተቋቋመ ማኅበር ነው።
ማየትና መስማት የተሳናቸው ሰዎች በአካል ጉዳታቸው ምክንያት የሚደርስባቸውን እንግልትና ተፅእኖ ለመቀነስ፣ እንዲሁም ማየትና መስማት የተሳናቸውን ህጻናትና ሴቶች የህይወት ክህሎት ስልጠና እና የሙያ ስልጠና በመስጠት እራሳቸውን እንዲችሉ እየተንቀሳቀሰ ያለ ማኅበር ነው።
ማኅበሩ ሐምሌ 10 ቀን 2014 ዓ.ም ከባድ የሆነ ዝርፊያ ተፈጽሞበታል።
በዚህ የዝርፊያ ወንጀል ማህበሩ ሲገለገልበት የነበረው 1 ሚኒባስ መኪና ኮድ 5 AA 02363 ነጭ ቶዮታ ተሰርቋል።
ሁለተኛው መኪና የቶዮታ ላንድ ክሩዘር 4 ጎማዎች ከነቸርኬያቸው ፈተው - መኪናውን በድንጋይ አንተርሰው ሄደዋል። የቢሮ መስኮቶች ተሰብረው ኮምፒውተር߹ እስካነር ያለው ፕሪንተር፣ 1 ፎቶ ኮፒ ማሽን ተውስዷል።
አፋልጉን፦
+25111 126 7600
+25111 126 7880
0911108984 ሮማን መስፍን
0924450267 እየሩሳሌም
0913587910 ቤተልሄም
@tikvahethiopia
የማየትና መስማት የተሳናቸው ህጻናት ለትራንስፖርት የሚገለገሉበት መኪና ተሰርቋል።
የኢትዮጵያ ማየትና መስማት የተሳናቸው ብሔራዊ ማኅበር ማየትና መስማት በተሳናቸው ሰዎች የተቋቋመ ማኅበር ነው።
ማየትና መስማት የተሳናቸው ሰዎች በአካል ጉዳታቸው ምክንያት የሚደርስባቸውን እንግልትና ተፅእኖ ለመቀነስ፣ እንዲሁም ማየትና መስማት የተሳናቸውን ህጻናትና ሴቶች የህይወት ክህሎት ስልጠና እና የሙያ ስልጠና በመስጠት እራሳቸውን እንዲችሉ እየተንቀሳቀሰ ያለ ማኅበር ነው።
ማኅበሩ ሐምሌ 10 ቀን 2014 ዓ.ም ከባድ የሆነ ዝርፊያ ተፈጽሞበታል።
በዚህ የዝርፊያ ወንጀል ማህበሩ ሲገለገልበት የነበረው 1 ሚኒባስ መኪና ኮድ 5 AA 02363 ነጭ ቶዮታ ተሰርቋል።
ሁለተኛው መኪና የቶዮታ ላንድ ክሩዘር 4 ጎማዎች ከነቸርኬያቸው ፈተው - መኪናውን በድንጋይ አንተርሰው ሄደዋል። የቢሮ መስኮቶች ተሰብረው ኮምፒውተር߹ እስካነር ያለው ፕሪንተር፣ 1 ፎቶ ኮፒ ማሽን ተውስዷል።
አፋልጉን፦
+25111 126 7600
+25111 126 7880
0911108984 ሮማን መስፍን
0924450267 እየሩሳሌም
0913587910 ቤተልሄም
@tikvahethiopia
#ጥቆማ
የአማራ መልሶ ማቋቋም እና ልማት ድርጅት (አመልድ) በአዲስ አበባ ከተማ ለገሃር አካባቢ ያስገነባውን ዘርፈ ብዙ አገልግሎት የሚሰጥ ግዙፍ ህንጻ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማከራየት እንደሚፈልግ አስታውቋል።
ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ማግስት ከሃምሌ 11/2014 ዓ.ም እስከ ሃምሌ 22/2014 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ለ10 ተከታታይ የስራ ቀናት ይቆያል።
ተጫራቾች የሚከራዩ ክፍሎችን ዓይነትና ስፋት ዝርዝር መግለጫ በጨረታ ሰነዱ ላይ እንዲሁም ህንጻው በሚገኝበት ለገሃር የአማራ ባንክ ዋናው መ/ቤት በአካል በመገኘት መመልከት ይችላሉ፡፡
ዝርዝር መረጃ https://telegra.ph/አመልድ-07-19
@tikvahethmagazine @tikvahethiopia
የአማራ መልሶ ማቋቋም እና ልማት ድርጅት (አመልድ) በአዲስ አበባ ከተማ ለገሃር አካባቢ ያስገነባውን ዘርፈ ብዙ አገልግሎት የሚሰጥ ግዙፍ ህንጻ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማከራየት እንደሚፈልግ አስታውቋል።
ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ማግስት ከሃምሌ 11/2014 ዓ.ም እስከ ሃምሌ 22/2014 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ለ10 ተከታታይ የስራ ቀናት ይቆያል።
ተጫራቾች የሚከራዩ ክፍሎችን ዓይነትና ስፋት ዝርዝር መግለጫ በጨረታ ሰነዱ ላይ እንዲሁም ህንጻው በሚገኝበት ለገሃር የአማራ ባንክ ዋናው መ/ቤት በአካል በመገኘት መመልከት ይችላሉ፡፡
ዝርዝር መረጃ https://telegra.ph/አመልድ-07-19
@tikvahethmagazine @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሳዑዲ_አረቢያ የሳዑዲ አረቢያ መንግስት በሪያድ የቀስተደመና ቀለም ያላቸውን እቃዎች ከሱቆች እና ከመደብሮች እየሰብሰበ ይገኛል። የሳዑዲ መንግስት የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ያስተዋውቃል በሚል የቀስተደመና ቀለም ያላቸውን አሸንጉሊቶች፣ ቲሸርቶች፣ የጸጉር ማስያዣዎች፣ ኮፊያ፣ እና የእርሳስ መያዣወችን ከየመደብሩ እንዲሰበሰቡ እያደረገ ነው። የሀገሪቱ መንግስት ህፃናትን ለመጠበቅ ሲል " መርዛማ መልዕክት…
" እኛ የሙስሊም ሀገር ነን። ባህሎች እና ወጎች አሉን እናም እስልምና እነዚህን ድርጊቶች (የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን) ይከለክላል " - አል ሃማሚ
ኢራቅ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ወንጀል እንዲሆንና ከፍተኛ የሆነ ቅጣት እንዲጣል እየሰራች መሆኗን አሳውቃለች።
የኢራቅ መንግስት የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት የሚከለክል ህግ ለማፅደቅ ማቀዱን አስታውቋል።
ኢራቅ በመካከለኛው ምስራቅ ከሚገኙ ሶስት ብዙ አረቦች ከሚኖሩበት ሀገር መካከል አንዷና የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን #በግልፅ ወንጀል እንደሆነ ካላወጁ ሀገራት የምትጠቀስ ናት፤ ሌሎቹ ጆርዳን እና ባህሬን ናቸው።
ምንም እንኳን በግልፅ ወንጀል ነው ተብሎ ባይገለፅም ድርጊቱ በማህበረሰቡ ዘንድ እጅግ በጣም የተወገዘ ነው።
አሁን ያለው ሁኔታ ያላማራት ኢራቅ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ወንጀል እንደሆነ በህግ ለመደንገግ እየሰራች ሲሆን ህጉ ከወጣ ኢራቅ ሌሎች ድርጊቱን በህግ ወንጀል እንደሆነ ካፀደቁ ሀገራት ተርታ ትሆናለች።
አብዛኛዎቹ የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን በቀጥታ በግልፅ የሚከለክሉ እና ወንጀል ነው ያሉ ሲሆን ከገንዘብ ቅጣት እስከ እስራት ፤ ሳውዲ አረቢያ ደግሞ #የሞት_ቅጣት ትቀጣለች።
በኢራቅ ፓርላማ የህግ ኮሚቴ ውስጥ ያሉት የፓርላማ አባል አሬፍ አል ሃማሚ ለDW በሰጡት ቃላቸው ፥ " አዲሱ ህግ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት ያላቸውን በወንጀል ተጠያቂ ያደርጋል ፤ በእነሱ ላይም ከባድ ቅጣት ይጥላል " ብለዋል።
ህጉ እስካሁን ድምጽ ያልተሰጠበት ሲሆን ድምፅ እንዲሰጥበት እየተሰራ ነው።
አል ሃማሚ ፤ ከሀገር ውስጥ እና ከዓለም አቀፍ #የሰብአዊ_መብት_ተሟጋች_ድርጅቶች ትችት ቢሰነዘርም ህጉ ይፀድቃል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል።
ያንብቡ telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-07-19
@tikvahethiopia
ኢራቅ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ወንጀል እንዲሆንና ከፍተኛ የሆነ ቅጣት እንዲጣል እየሰራች መሆኗን አሳውቃለች።
የኢራቅ መንግስት የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት የሚከለክል ህግ ለማፅደቅ ማቀዱን አስታውቋል።
ኢራቅ በመካከለኛው ምስራቅ ከሚገኙ ሶስት ብዙ አረቦች ከሚኖሩበት ሀገር መካከል አንዷና የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን #በግልፅ ወንጀል እንደሆነ ካላወጁ ሀገራት የምትጠቀስ ናት፤ ሌሎቹ ጆርዳን እና ባህሬን ናቸው።
ምንም እንኳን በግልፅ ወንጀል ነው ተብሎ ባይገለፅም ድርጊቱ በማህበረሰቡ ዘንድ እጅግ በጣም የተወገዘ ነው።
አሁን ያለው ሁኔታ ያላማራት ኢራቅ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ወንጀል እንደሆነ በህግ ለመደንገግ እየሰራች ሲሆን ህጉ ከወጣ ኢራቅ ሌሎች ድርጊቱን በህግ ወንጀል እንደሆነ ካፀደቁ ሀገራት ተርታ ትሆናለች።
አብዛኛዎቹ የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን በቀጥታ በግልፅ የሚከለክሉ እና ወንጀል ነው ያሉ ሲሆን ከገንዘብ ቅጣት እስከ እስራት ፤ ሳውዲ አረቢያ ደግሞ #የሞት_ቅጣት ትቀጣለች።
በኢራቅ ፓርላማ የህግ ኮሚቴ ውስጥ ያሉት የፓርላማ አባል አሬፍ አል ሃማሚ ለDW በሰጡት ቃላቸው ፥ " አዲሱ ህግ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት ያላቸውን በወንጀል ተጠያቂ ያደርጋል ፤ በእነሱ ላይም ከባድ ቅጣት ይጥላል " ብለዋል።
ህጉ እስካሁን ድምጽ ያልተሰጠበት ሲሆን ድምፅ እንዲሰጥበት እየተሰራ ነው።
አል ሃማሚ ፤ ከሀገር ውስጥ እና ከዓለም አቀፍ #የሰብአዊ_መብት_ተሟጋች_ድርጅቶች ትችት ቢሰነዘርም ህጉ ይፀድቃል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል።
ያንብቡ telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-07-19
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ህግ ይከበር ፤ ፍትህ ይሰጠን " ለማስፋፊያ ስራ ተብሎ #ህግን_ባልተከተለ መልኩ ቤታችን ፈረሰብን ያሉ በአዲስ አበባ ከተማ ፤ ገርጂ ኮርያ ሆስፒታል አካባቢ የሚገኙ ነዋሪዎች ቅሬታ አቅርበዋል። ያሉበት ቦታ ለማስፋፊያ ስራ ይፈለጋል የተባሉ ዜጎች ለማስፋፊያ አንደሚፈለግ ያወቁት ሰኔ 29/2013 ዓ/ም አንደሆነ ከዛ በፊት ስለጉዳዩ ምንም እንደማያቁ / እንዳልተነገራቸው ፤ ጉዳዩን የሚያውቁት ከወረዳው…
" ፍትህ ሳናገኝ አንድ ወር ሞላን " - ነዋሪዎች
ከዛሬ አንድ ወር በፊት በአዲስ አበባ ከተማ ገርጂ ኮርያ ሆስፒታል አካባቢ ቤታቸው የፈረሰባቸው ነዋሪዎች ፍትህ ሳያገኙ አንድ ወር እንደሞላቸው ተናገሩ።
ነዋሪዎቹ ከዚህ ቀደም የነበረውን ሁኔታ በዝርዝር ማስረዳታቸው አይዘነጋም።
ቤታቸው የፈረሰው ፍርድ ቤት ለእነሱ ወስኖላቸው (በቦታው እንዲፀኑ) መሆኑንና አፍራሽ ግብረኃይል በኃይል ህግ እና ስርዓትን በመጣስ እንዳፈረሰው መግለፃቸው ይታወሳል።
እኚህ ወገኖች እስካሁን ድረስ አንዳች መፍትሄ ሆነ ፍትህ ሳያገኙ ከ30 ቀን እንዳለፋቸው ተናግረው አሁንም ይመለከተኛል የሚል የመንግስት አካል ፍትህ እንዲሰጣቸው ፤ ህግን በጣሱ እና የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ባላከበሩት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀዋል።
በሌላ በኩል ፥ ቤታቸው በግፍ የፈረሰባቸውን 30ኛ ቀን ምክንያት በማድረግ የቦሌ ኆህተ ብርሃን ቤተ ክርስትያን በፀሎት እና በትምህርት አስባው ማምሸቷን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል
ፍ/ቤት በቦታው ላይ እንዲፀኑ ፈርዶላቸው ፍትህ ያጡበትን ሁኔታ በማየት የሚመለከተው አካል ፍትህ እንዲያሰፍንና ሜዳ ላይ የተበተኑበትን ሁኔታ ተመልክቶ አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጣቸው የጠየቀች ሲሆን ለተጎዱትም ወገኖች የተለያዩ እርዳታዎችን አድርጋለች፡፡
ነዋሪዎቹ ከዚህ ቀደም የተፈፀመውን ድርጊት የሰሙ የተለያየ እምነት ተከታዮችም እንዳፅናኗቸው ፣ መጥተው እንደጠየቋቸውም ገልፀዋል።
አሁንም ለፍትህ የቆመ አካል ፍትህ እንዲሰጣቸው እየጠየቁ ነው።
@tikvahethiopia
ከዛሬ አንድ ወር በፊት በአዲስ አበባ ከተማ ገርጂ ኮርያ ሆስፒታል አካባቢ ቤታቸው የፈረሰባቸው ነዋሪዎች ፍትህ ሳያገኙ አንድ ወር እንደሞላቸው ተናገሩ።
ነዋሪዎቹ ከዚህ ቀደም የነበረውን ሁኔታ በዝርዝር ማስረዳታቸው አይዘነጋም።
ቤታቸው የፈረሰው ፍርድ ቤት ለእነሱ ወስኖላቸው (በቦታው እንዲፀኑ) መሆኑንና አፍራሽ ግብረኃይል በኃይል ህግ እና ስርዓትን በመጣስ እንዳፈረሰው መግለፃቸው ይታወሳል።
እኚህ ወገኖች እስካሁን ድረስ አንዳች መፍትሄ ሆነ ፍትህ ሳያገኙ ከ30 ቀን እንዳለፋቸው ተናግረው አሁንም ይመለከተኛል የሚል የመንግስት አካል ፍትህ እንዲሰጣቸው ፤ ህግን በጣሱ እና የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ባላከበሩት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀዋል።
በሌላ በኩል ፥ ቤታቸው በግፍ የፈረሰባቸውን 30ኛ ቀን ምክንያት በማድረግ የቦሌ ኆህተ ብርሃን ቤተ ክርስትያን በፀሎት እና በትምህርት አስባው ማምሸቷን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል
ፍ/ቤት በቦታው ላይ እንዲፀኑ ፈርዶላቸው ፍትህ ያጡበትን ሁኔታ በማየት የሚመለከተው አካል ፍትህ እንዲያሰፍንና ሜዳ ላይ የተበተኑበትን ሁኔታ ተመልክቶ አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጣቸው የጠየቀች ሲሆን ለተጎዱትም ወገኖች የተለያዩ እርዳታዎችን አድርጋለች፡፡
ነዋሪዎቹ ከዚህ ቀደም የተፈፀመውን ድርጊት የሰሙ የተለያየ እምነት ተከታዮችም እንዳፅናኗቸው ፣ መጥተው እንደጠየቋቸውም ገልፀዋል።
አሁንም ለፍትህ የቆመ አካል ፍትህ እንዲሰጣቸው እየጠየቁ ነው።
@tikvahethiopia
" ... ካልተጨበጠ መረጃ በቀር የሶማሊያ ወታደሮች በኢትዮጵያው ጦርነት ላይ ተሳትፈዋል የሚል መረጃ ተመልክታችኋል? " - አብዲካሪም አሊ ካር
አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼይክ ሞሐመድ አስተዳደር በኤርትራ ስልጠና ሲወስዱ የነበሩት የሃገሪቱ ወታደሮች በኢትዮጵያ የእርስ በእርስ ጦርነት አልተሳተፉም አለ።
የተመድ እና ህወሓት የሶማሊያ ወታደሮች በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ከፌደራል መንግሥቱ ጎን ተሰልፈው ተዋግተዋል ማለታቸው ይታወሳል።
ይሁን እንጂ የቀድሞ የሶማሊያ መንግሥት ፕሬዝዳንት አስተዳደርም ሆነ አዲሱ መንግሥት፤ የሶማሊያ ወታደሮች በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት አልተሳተፉም ብለዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት የሶማሊያ ወታደሮች በትግራዩ ጦርነት ተሳትፈዋል የሚለውን ክስ ማስተባበሉን አይዘነጋም።
ትናንት ሐምሌ 12/2014 ዓ.ም. የፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐመድቃል አቀባይ በሰጡት መግለጫ የሶማሊያ ወታደሮች በኢትዮጵያው ጦርነት ተሳትፈዋል መባሉ ያልተረጋገጠ መረጃ ነው ብለዋል።
ቃል አቀባዩ አብዲካሪም አሊ ካር ፥ " ካልተጨበጠ መረጃ በቀር የሶማሊያ ወታደሮች በኢትዮጵያው ጦርነት ተሳትፈዋል የሚል መረጃ ተመልክታችኋል? " ሲሉ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ጠይቀዋል።
በርካታ ሶማሊያውያን ወታደሮች ፤ መቼ እና በምን ሁኔታ ወደ ሶማሊያ እንደሄዱ ሳይገለጽ ቆይቶ ሰሞኑን የፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐመድ ጉብኝትን ተከትሎ የኤርትራ መንግሥት ሐምሌ 3/2014 ዓ.ም ለሶስት ዓመታት ያህል ወታደራዊ ሥልጠና ሲወስዱ የነበሩት የሶማሊያ ወታደሮች ተመርቀዋል ተብሏል።
ተቀናቃኞች በበኩላቸው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ፋርማጆ ወታደሮቹን ወዳልታወቀ ስፍራ ልከው በኢትዮጵያ የእርስ በእርስ ጦርነት ላይ ማግደዋቸዋል በሚል ሲወቅሷቸው ቆይተዋል።
የወታደሮቹ ቤተሰብ አባላትም ስለልጆቻቸው ሁኔታ በመጠየቅ መንግሥትን አስጨንቀው ነበር።
የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ቃል አቀባይ አብዲካሪም አሊ ካር ፤ በኢትዮጵያ ተሰልፈው ተጋዋግተዋል የሚለው ብቻ ሳይሆን የሶማሊያ ወታደሮች በኤርትራ የቆዩት ሶማሊያ የሚጠበቅባትን ገንዘብ መክፈል ባለመቻሏ ወታደሮቹ እንደመያዣነት ተይዘው ነው የሚባለውም ሐሰት ነው ብለዋል።
አብዲካሪም አሊ ካር ፦
" ... ሐሰት ነው ወታደሮቹ እንደመያዣነት አልተያዙም። ለማንም መክፈል ያለብን ገንዘብ የለም።
እንደ ተርኪዬ ፣ ኡጋንዳ እና ኢትዮጵያ ያሉ ሃገራት የሶማሊያንወታደሮች ያሰለጥናሉ።
ስልጠና የሚሰጣቸው ለገንዘብ አይደለም " ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት ኤርትራ ውስጥ የሚገኙት የሶማሊያ ወታደሮች ብዛት 5 ሺህ መሆኑን ጠቅሰው፤ የሞቃዲሹ መንግሥት ወታደሮቹን ወደ ሃገር ቤት ለመመለስ እየሠራ ይገኛል ማለታቸውን ቢቢሲ በድረገፁ ላይ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼይክ ሞሐመድ አስተዳደር በኤርትራ ስልጠና ሲወስዱ የነበሩት የሃገሪቱ ወታደሮች በኢትዮጵያ የእርስ በእርስ ጦርነት አልተሳተፉም አለ።
የተመድ እና ህወሓት የሶማሊያ ወታደሮች በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ከፌደራል መንግሥቱ ጎን ተሰልፈው ተዋግተዋል ማለታቸው ይታወሳል።
ይሁን እንጂ የቀድሞ የሶማሊያ መንግሥት ፕሬዝዳንት አስተዳደርም ሆነ አዲሱ መንግሥት፤ የሶማሊያ ወታደሮች በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት አልተሳተፉም ብለዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት የሶማሊያ ወታደሮች በትግራዩ ጦርነት ተሳትፈዋል የሚለውን ክስ ማስተባበሉን አይዘነጋም።
ትናንት ሐምሌ 12/2014 ዓ.ም. የፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐመድቃል አቀባይ በሰጡት መግለጫ የሶማሊያ ወታደሮች በኢትዮጵያው ጦርነት ተሳትፈዋል መባሉ ያልተረጋገጠ መረጃ ነው ብለዋል።
ቃል አቀባዩ አብዲካሪም አሊ ካር ፥ " ካልተጨበጠ መረጃ በቀር የሶማሊያ ወታደሮች በኢትዮጵያው ጦርነት ተሳትፈዋል የሚል መረጃ ተመልክታችኋል? " ሲሉ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ጠይቀዋል።
በርካታ ሶማሊያውያን ወታደሮች ፤ መቼ እና በምን ሁኔታ ወደ ሶማሊያ እንደሄዱ ሳይገለጽ ቆይቶ ሰሞኑን የፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐመድ ጉብኝትን ተከትሎ የኤርትራ መንግሥት ሐምሌ 3/2014 ዓ.ም ለሶስት ዓመታት ያህል ወታደራዊ ሥልጠና ሲወስዱ የነበሩት የሶማሊያ ወታደሮች ተመርቀዋል ተብሏል።
ተቀናቃኞች በበኩላቸው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ፋርማጆ ወታደሮቹን ወዳልታወቀ ስፍራ ልከው በኢትዮጵያ የእርስ በእርስ ጦርነት ላይ ማግደዋቸዋል በሚል ሲወቅሷቸው ቆይተዋል።
የወታደሮቹ ቤተሰብ አባላትም ስለልጆቻቸው ሁኔታ በመጠየቅ መንግሥትን አስጨንቀው ነበር።
የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ቃል አቀባይ አብዲካሪም አሊ ካር ፤ በኢትዮጵያ ተሰልፈው ተጋዋግተዋል የሚለው ብቻ ሳይሆን የሶማሊያ ወታደሮች በኤርትራ የቆዩት ሶማሊያ የሚጠበቅባትን ገንዘብ መክፈል ባለመቻሏ ወታደሮቹ እንደመያዣነት ተይዘው ነው የሚባለውም ሐሰት ነው ብለዋል።
አብዲካሪም አሊ ካር ፦
" ... ሐሰት ነው ወታደሮቹ እንደመያዣነት አልተያዙም። ለማንም መክፈል ያለብን ገንዘብ የለም።
እንደ ተርኪዬ ፣ ኡጋንዳ እና ኢትዮጵያ ያሉ ሃገራት የሶማሊያንወታደሮች ያሰለጥናሉ።
ስልጠና የሚሰጣቸው ለገንዘብ አይደለም " ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት ኤርትራ ውስጥ የሚገኙት የሶማሊያ ወታደሮች ብዛት 5 ሺህ መሆኑን ጠቅሰው፤ የሞቃዲሹ መንግሥት ወታደሮቹን ወደ ሃገር ቤት ለመመለስ እየሠራ ይገኛል ማለታቸውን ቢቢሲ በድረገፁ ላይ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ጋምቤላ - ሰዓት እላፊ ! በጋምቤላ ከተማ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ሕገወጥ እንቅስቃሴን ለመቆጣጠር የሰዓት እላፊ ገደብ መጣሉን የክልሉ መንግስት አስታውቋል። ከዚህ ቀደም በጋምቤላ ከተማ ተከስቶ በነበረው የፀጥታ መደፍረስ ምክንያት የሰዓት እላፊ ተጥሎ እንደነበር ይታወሳል። ይሁን እንጂ ለማህበረሰቡ ደህንነት ታስቦ የተጣለው የሰዓት እላፊ ገደብ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር ክፍተት መታየቱን ተገልጿል።…
#Update #ጋምቤላ
" የሰዓት እላፊ ገደቡ ተነስቷል "
ከሰሞኑን በጋምቤላ ከተማ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ ከቀናት በፊት ተጥሎ የነበረው የሰዓት እላፊ ገደብ መነሳቱን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
@tikvahethiopia
" የሰዓት እላፊ ገደቡ ተነስቷል "
ከሰሞኑን በጋምቤላ ከተማ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ ከቀናት በፊት ተጥሎ የነበረው የሰዓት እላፊ ገደብ መነሳቱን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
@tikvahethiopia