TIKVAH-ETHIOPIA
#Gambella " በጥቃቱ የ8 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 5 ሰዎች ከባድ እና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል " - ፖሊስ በጋምቤላ ክልል ከደቡብ ሱዳን የሚነሱ የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ድንበር አቋርጠው በመግባት ጥቃት ማድረሳቸውን የክልሉ ፖሊስ አስታወቀ። በጥቃቱ የ8 ሠዎች ህይወት ሲያልፍ በ5 ሠዎች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል ጉዳት መድረሱን ተገልጿል። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቡላ ኡቦንግ ፥ በጋምቤላ…
#Gambella
ትላንትና በጋምቤላ ክልል ከደቡብ ሱዳን የሚነሱ የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ድንበር አቋርጠው በመግባት በዲማ ስደተኛ ካምፕና በጎግ ወረዳ ጥቃት ማድረሳቸውን የጋምቤላ ክልል አስታውቋል።
በጥቃቱ የአንድ ሠው ህይወትሲያልፍ ሁለት ሠዎች ላይ ጉዳት መድረሱንና ሶስት ህፃናት ታፍነው ተወስደዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በጎግ ወረዳ ከፑኝዶ ከተማ ወደ ቴዶ ቀበሌ የሚሄድ ሞተር ሳይክል ላይ ባደረሱት ጥቃት የአንድ ሰው ህይወት ተገልጿል።
በቅርቡም መነሻውን ከጋምቤላ ከተማ አድርጎ ወደ ኑዌር ዞን በመጓዝ ላይ ባለ የጭነት መኪና ላይ ማንነታቸው ያልታወቁ ግለሰቦች ባደረሱት ጥቃት የመኪናው አሽከርካሪ እና ረዳቱ ህይወታቸው እንዳለፈ የክልሉ መንግሥት አስታውቋል።
ጥቃት ያደረሱትን ግለሰቦች በክልሉ ልዩ ሀይልና ሚሊሻዎች አማካኝነት ተከታትሎ አስፈላጊውን እርምጃ ለመውሰድ ጠንካራ ስራ እየተከናወነ እንደሆነ ክልሉ ገልጿል።
ህብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጎን በመሆን አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ተጠይቋል።
በአሁኑ ሰዓት ክልሉ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ በመጠቀም ጥቃት በደረሰባቸው አካባቢዎች ሰላምና ፀጥታ የማስከበር ስራውን እየሰራ መሆኑንና የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በየቦታው ሾልከው ሊገቡ ስለሚችሉ ህብረተሰቡ አካባቢውን ነቅቶ እንዲጠብቅ ማሳሰቢያ አስተላልፏል።
የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በቅርቡ፤ በኑዌር ዞን እና አኙዋ ዞኖች ገብተው 4 ሕፃናት አፍነው በመውሰድ፣ የከብት ዝርፊያ በማካሄድ አስራ አንድ ሰዎችም ሕይወታቸውን ማጣታቸው ይታወሳል።
መረጃው የጋምቤላ ክልል ፕሬስ ሴክሬተሪያት ነው።
@tikvahethiopia
ትላንትና በጋምቤላ ክልል ከደቡብ ሱዳን የሚነሱ የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ድንበር አቋርጠው በመግባት በዲማ ስደተኛ ካምፕና በጎግ ወረዳ ጥቃት ማድረሳቸውን የጋምቤላ ክልል አስታውቋል።
በጥቃቱ የአንድ ሠው ህይወትሲያልፍ ሁለት ሠዎች ላይ ጉዳት መድረሱንና ሶስት ህፃናት ታፍነው ተወስደዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በጎግ ወረዳ ከፑኝዶ ከተማ ወደ ቴዶ ቀበሌ የሚሄድ ሞተር ሳይክል ላይ ባደረሱት ጥቃት የአንድ ሰው ህይወት ተገልጿል።
በቅርቡም መነሻውን ከጋምቤላ ከተማ አድርጎ ወደ ኑዌር ዞን በመጓዝ ላይ ባለ የጭነት መኪና ላይ ማንነታቸው ያልታወቁ ግለሰቦች ባደረሱት ጥቃት የመኪናው አሽከርካሪ እና ረዳቱ ህይወታቸው እንዳለፈ የክልሉ መንግሥት አስታውቋል።
ጥቃት ያደረሱትን ግለሰቦች በክልሉ ልዩ ሀይልና ሚሊሻዎች አማካኝነት ተከታትሎ አስፈላጊውን እርምጃ ለመውሰድ ጠንካራ ስራ እየተከናወነ እንደሆነ ክልሉ ገልጿል።
ህብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጎን በመሆን አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ተጠይቋል።
በአሁኑ ሰዓት ክልሉ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ በመጠቀም ጥቃት በደረሰባቸው አካባቢዎች ሰላምና ፀጥታ የማስከበር ስራውን እየሰራ መሆኑንና የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በየቦታው ሾልከው ሊገቡ ስለሚችሉ ህብረተሰቡ አካባቢውን ነቅቶ እንዲጠብቅ ማሳሰቢያ አስተላልፏል።
የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በቅርቡ፤ በኑዌር ዞን እና አኙዋ ዞኖች ገብተው 4 ሕፃናት አፍነው በመውሰድ፣ የከብት ዝርፊያ በማካሄድ አስራ አንድ ሰዎችም ሕይወታቸውን ማጣታቸው ይታወሳል።
መረጃው የጋምቤላ ክልል ፕሬስ ሴክሬተሪያት ነው።
@tikvahethiopia
#Gambella , #Akobo📍
" የኔትወርክና የመንገድ መሠረተ ልማት ባለመሟላቱ የሚፈጠሩ የፀጥታ ችግሮችን በፍጥነት ለመፍታት አዳጋች ሆኗል " - አቶ ኮንግ ጋትዮቴ
በጋምቤላ ክልል በአኮቦ ወረዳ ከደቡብ ሱዳን በሚነሱ የሙርሌ ታጣቂዎች ድንበር አቋርጠው ህብረተሰቡ ላይ ጉዳት እንዳያደርሱ ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት እየሰራ መሆኑን የወረዳዉ አስተዳደር አስታውቋል።
የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኮንግ ጋትዮቴ እንዳሉት ከደቡብ ሱዳን የሚነሱ የሙሩሌ ጎሳ ታጣቂዎች በተለያዩ ጊዜያት ድንበር አቋርጠዉ በመግባት ጥቃት ሲፈፅሙ ቆይተዋል ብለዋል።
ታጣቂ ቡድኑ በሰዉ ህይወት ላይ ከሚያደርሰው ጉዳት ባለፈ ህፃናትንና የቁም እንስሳትን ሲዘርፉ እንደነበር ጠቅሰዉ በአሁኑ ወቅት ከክልሉ የጠጥታ አካላት ጋር በመቀኛጀትና የስጋት ቀጠናዎችን በመለየት መሰል ጥቃት እንዳይፈፀም እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በወረዳዉ የኔትወርክና የመንገድ መሠረተ ልማት ባለመሟላቱ የሚፈጠሩ የፀጥታ ችግሮችን በፍጥነት ለመፍታት አዳጋች እንደሆነባቸዉ ገልፀዉ መንግስት እነዚህ መሠረተ ልማቶች ላይ ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በሌላ በኩል የክልሉ መንግስት በጥቃቱ ለተጎዱ እና ለተፈናቀሉ ከ2,500 በላይ ወገኖች በ2 ሚሊዮን ብር 600 ኩንታል በቆሎ በመግዛት ድጋፍ ማድረግ መቻሉን የክልሉ አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ኤጀንሲ መግለፁን ከጋምቤላ ፕሬስ ሴክሬተሪያት ያገኘነው መረጃ ያሳያል
@tikvahethiopia
" የኔትወርክና የመንገድ መሠረተ ልማት ባለመሟላቱ የሚፈጠሩ የፀጥታ ችግሮችን በፍጥነት ለመፍታት አዳጋች ሆኗል " - አቶ ኮንግ ጋትዮቴ
በጋምቤላ ክልል በአኮቦ ወረዳ ከደቡብ ሱዳን በሚነሱ የሙርሌ ታጣቂዎች ድንበር አቋርጠው ህብረተሰቡ ላይ ጉዳት እንዳያደርሱ ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት እየሰራ መሆኑን የወረዳዉ አስተዳደር አስታውቋል።
የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኮንግ ጋትዮቴ እንዳሉት ከደቡብ ሱዳን የሚነሱ የሙሩሌ ጎሳ ታጣቂዎች በተለያዩ ጊዜያት ድንበር አቋርጠዉ በመግባት ጥቃት ሲፈፅሙ ቆይተዋል ብለዋል።
ታጣቂ ቡድኑ በሰዉ ህይወት ላይ ከሚያደርሰው ጉዳት ባለፈ ህፃናትንና የቁም እንስሳትን ሲዘርፉ እንደነበር ጠቅሰዉ በአሁኑ ወቅት ከክልሉ የጠጥታ አካላት ጋር በመቀኛጀትና የስጋት ቀጠናዎችን በመለየት መሰል ጥቃት እንዳይፈፀም እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በወረዳዉ የኔትወርክና የመንገድ መሠረተ ልማት ባለመሟላቱ የሚፈጠሩ የፀጥታ ችግሮችን በፍጥነት ለመፍታት አዳጋች እንደሆነባቸዉ ገልፀዉ መንግስት እነዚህ መሠረተ ልማቶች ላይ ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በሌላ በኩል የክልሉ መንግስት በጥቃቱ ለተጎዱ እና ለተፈናቀሉ ከ2,500 በላይ ወገኖች በ2 ሚሊዮን ብር 600 ኩንታል በቆሎ በመግዛት ድጋፍ ማድረግ መቻሉን የክልሉ አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ኤጀንሲ መግለፁን ከጋምቤላ ፕሬስ ሴክሬተሪያት ያገኘነው መረጃ ያሳያል
@tikvahethiopia
#Gambella
ትናንት ምሽት ላይ በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ በተፈጠረ ግጭት የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ አንድ ሰው ላይ የመቁሰል አደጋ መደረሱ ተገልጸ።
የክልሉ ፖሊስ ፤ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በክልል ፖሊስ እና በፌደራል ፖሊስ መካከል በተፈጠረ ግጭት የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ በአንድ ሰው ላይ የመቁሰል አደጋ ደርሷል ሲል አሳውቋል።
በአሁኑ ሰዓት የአካባቢው ሠላም ወደነበረበት ተመልሷል፤ ግጭት ፈጥረዋልም የተባሉ ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር በማዋል ተገቢው ማጣራት እየተካሄደ ነው ሲል የክልሉ ፖሊስ ገልጿል።
ፖሊስ የግጭቱን መንስኤ እያጣራ እንደሆነም አሳውቋል።
ከተማዋ ሰላም መሆኗን እና ህብረተሰቡም ወደ ተለመደው የሰላም ሁኔታ መመለሱንም ገልጿል።
የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ነዋሪዎች ረብሻና ሁከት ከሚፈጥሩ አንዳንድ ማህበራዊ የሚዲያ ገፆችና ያልተረጋገጠ መረጃ ከሚሰጡ ዘገባዎች እራሳቸውን እንዲጠብቁ አስገንዝቧል።
@tikvahethiopia
ትናንት ምሽት ላይ በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ በተፈጠረ ግጭት የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ አንድ ሰው ላይ የመቁሰል አደጋ መደረሱ ተገልጸ።
የክልሉ ፖሊስ ፤ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በክልል ፖሊስ እና በፌደራል ፖሊስ መካከል በተፈጠረ ግጭት የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ በአንድ ሰው ላይ የመቁሰል አደጋ ደርሷል ሲል አሳውቋል።
በአሁኑ ሰዓት የአካባቢው ሠላም ወደነበረበት ተመልሷል፤ ግጭት ፈጥረዋልም የተባሉ ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር በማዋል ተገቢው ማጣራት እየተካሄደ ነው ሲል የክልሉ ፖሊስ ገልጿል።
ፖሊስ የግጭቱን መንስኤ እያጣራ እንደሆነም አሳውቋል።
ከተማዋ ሰላም መሆኗን እና ህብረተሰቡም ወደ ተለመደው የሰላም ሁኔታ መመለሱንም ገልጿል።
የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ነዋሪዎች ረብሻና ሁከት ከሚፈጥሩ አንዳንድ ማህበራዊ የሚዲያ ገፆችና ያልተረጋገጠ መረጃ ከሚሰጡ ዘገባዎች እራሳቸውን እንዲጠብቁ አስገንዝቧል።
@tikvahethiopia
#Gambella
በጋምቤላ ክልል መዠንገር ዞን ፤ ሜጢ ከተማ ከፍርድ ቤት ቀጠሮ ወደ ማረሚያ ቤት 22 እስረኞችን ሲመልስ የነበረ የፖሊስ ተሽከርካሪ ተገልብጦ ከባድ አደጋ መድረሱ ተሰምቷል።
በአደጋው የአንድ እስረኛ ህይወት አልፏል።
አጠቃላይ በተሽከርካሪው 22 እስረኞችና 4 የፖሊስ አባላት (26 ሰዎች) የአደጋው ሰለባ ሲሆኑ በአደጋው የሞት፣ ከባድ ፣እና ቀላል ጉዳት ተመዝግቧል።
የመዠንገር ዞን ፀጥታ መምሪያ ለሸገር ኤፍ ኤም በሰጠው ቃል ፤ መኪናው ከፊት ለፊት ባጃጅ ገብቶበት እሱን አድናለው ሲል መገልበጡን ገልጾ ጉዳት የደረሰባቸው እስረኞች እና የፖሊስ አባላት ቴፒ ሆስፒታል ተወስደዋል።
ከእስረኞች መካከል ያመለጠ እንደሌለ ያሳወቀው ፀጥታ መምሪያው አንድ ታራሚ ህይወቱ እንዳለፈ ሌሎቹ ግን በሆስፒታል ህክምና ላይ እንደሚገኙ ገልጿል።
22ቱ ግለሰቦች በተለያየ ጥፋት ተጠርጥረው ማረሚያ የወረዱ መሆናቸውን የገለፀው የፀጥታ መምሪያው ከአዲስ አበባ የሚላክ " የስንዴ እርዳታ " ወደ ህዝብ ሳይደርስ መንገድ ላይ ሲሸጡ እና ለግል ጥቅም ሲያውሉ የነበሩ ሰዎች መኖራቸውን መጠቆሙን ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ዘግቧል።
@tikvahethiopia
በጋምቤላ ክልል መዠንገር ዞን ፤ ሜጢ ከተማ ከፍርድ ቤት ቀጠሮ ወደ ማረሚያ ቤት 22 እስረኞችን ሲመልስ የነበረ የፖሊስ ተሽከርካሪ ተገልብጦ ከባድ አደጋ መድረሱ ተሰምቷል።
በአደጋው የአንድ እስረኛ ህይወት አልፏል።
አጠቃላይ በተሽከርካሪው 22 እስረኞችና 4 የፖሊስ አባላት (26 ሰዎች) የአደጋው ሰለባ ሲሆኑ በአደጋው የሞት፣ ከባድ ፣እና ቀላል ጉዳት ተመዝግቧል።
የመዠንገር ዞን ፀጥታ መምሪያ ለሸገር ኤፍ ኤም በሰጠው ቃል ፤ መኪናው ከፊት ለፊት ባጃጅ ገብቶበት እሱን አድናለው ሲል መገልበጡን ገልጾ ጉዳት የደረሰባቸው እስረኞች እና የፖሊስ አባላት ቴፒ ሆስፒታል ተወስደዋል።
ከእስረኞች መካከል ያመለጠ እንደሌለ ያሳወቀው ፀጥታ መምሪያው አንድ ታራሚ ህይወቱ እንዳለፈ ሌሎቹ ግን በሆስፒታል ህክምና ላይ እንደሚገኙ ገልጿል።
22ቱ ግለሰቦች በተለያየ ጥፋት ተጠርጥረው ማረሚያ የወረዱ መሆናቸውን የገለፀው የፀጥታ መምሪያው ከአዲስ አበባ የሚላክ " የስንዴ እርዳታ " ወደ ህዝብ ሳይደርስ መንገድ ላይ ሲሸጡ እና ለግል ጥቅም ሲያውሉ የነበሩ ሰዎች መኖራቸውን መጠቆሙን ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ዘግቧል።
@tikvahethiopia
#Gambella
ትናንት ከቀኑ 10 ሰዓት ገደማ በጋምቤላ ወረዳ ጎሊ በሚባል አካባቢ በተፈፀመ ጥቃት በእርሻ ሥራ ላይ የነበሩ 2 ሰዎች (አንድ ወንድ እና አንድ ሴት) ሲገደሉ 3 ሠዎች (2 ወንድ እና አንስ ሴት) ታፍነው መወሰዳቸውን የጋምቤላ ክልል አሳውቋል።
ክልሉ ለጥቃቱ የጋምቤላ ነፃነት ግንባር (ጋነግ) ተብሎ የሚጠራውን ቡድን እና በህ/ተ/ም/ቤት በአሸባሪነት የተፈረጀውን " ሸኔ " / እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እያለ የሚጠራውን የታጠቀ ቡድን ተጠያቂ አድርጓል።
የክልሉ መንግስት የፀጥታ ሀይሎች ጥቃት አድራሾቹ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ክትትል እያደረጉ እንደሚገኝ ገልጾ ህብረተሰቡ ተገቢውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ ማቅረቡን ከክልሉ ኮሚኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopia
ትናንት ከቀኑ 10 ሰዓት ገደማ በጋምቤላ ወረዳ ጎሊ በሚባል አካባቢ በተፈፀመ ጥቃት በእርሻ ሥራ ላይ የነበሩ 2 ሰዎች (አንድ ወንድ እና አንድ ሴት) ሲገደሉ 3 ሠዎች (2 ወንድ እና አንስ ሴት) ታፍነው መወሰዳቸውን የጋምቤላ ክልል አሳውቋል።
ክልሉ ለጥቃቱ የጋምቤላ ነፃነት ግንባር (ጋነግ) ተብሎ የሚጠራውን ቡድን እና በህ/ተ/ም/ቤት በአሸባሪነት የተፈረጀውን " ሸኔ " / እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እያለ የሚጠራውን የታጠቀ ቡድን ተጠያቂ አድርጓል።
የክልሉ መንግስት የፀጥታ ሀይሎች ጥቃት አድራሾቹ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ክትትል እያደረጉ እንደሚገኝ ገልጾ ህብረተሰቡ ተገቢውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ ማቅረቡን ከክልሉ ኮሚኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopia
#Gambella 📍
ትላንት ምሽት በጋምቤላ ከተማ 01 ቀበሌ ኒዉላንድ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አካባቢ ተኩስ ተከፍቶ እንደነበር የክልሉ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት አሳውቋል።
ፅ/ቤቱ ፤ ተኩስ ከፍቶ የነበረው ራሱን የጋምቤላ ነፃነት ግንባር (ጋነግ) ብሎ የሚጠራው ድርጅት ነው ብሏል።
" ቡድኑ ህዝብ የማሸበር ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል " ያለው ፅ/ቤቱ ትላንት ምሽት 3 ሰዓት ገደማ በ01 ቀበሌ በከፈተው ተኩስ በአንድ የመንግስት ልዩ ሀይል ላይ ጉዳት አድርሷል ሲል አመልክቷል።
መንግስት የፀጥታ ሀይሉን በማደራጀት የከፋ ጉዳት እንዳይደርስ የመከላከል ስራ እያከናወነ መሆኑን የጠቀሰው ፅ/ቤቱ ህብረተሰቡ ከፀጥታ ሀይሉ ጎን በመሆን ተገቢውን መረጃ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopia
ትላንት ምሽት በጋምቤላ ከተማ 01 ቀበሌ ኒዉላንድ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አካባቢ ተኩስ ተከፍቶ እንደነበር የክልሉ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት አሳውቋል።
ፅ/ቤቱ ፤ ተኩስ ከፍቶ የነበረው ራሱን የጋምቤላ ነፃነት ግንባር (ጋነግ) ብሎ የሚጠራው ድርጅት ነው ብሏል።
" ቡድኑ ህዝብ የማሸበር ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል " ያለው ፅ/ቤቱ ትላንት ምሽት 3 ሰዓት ገደማ በ01 ቀበሌ በከፈተው ተኩስ በአንድ የመንግስት ልዩ ሀይል ላይ ጉዳት አድርሷል ሲል አመልክቷል።
መንግስት የፀጥታ ሀይሉን በማደራጀት የከፋ ጉዳት እንዳይደርስ የመከላከል ስራ እያከናወነ መሆኑን የጠቀሰው ፅ/ቤቱ ህብረተሰቡ ከፀጥታ ሀይሉ ጎን በመሆን ተገቢውን መረጃ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopia
#Gambella
ጋምቤላ በተኩስ ልውውጥ እየተናጠች ነው።
በጋምቤላ ክልል ዋና ከተማ " ጋምቤላ " ዛሬ ከማለዳ ጀምሮ ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ እየተደረገ መሆኑን እና ከፊል የከተማው ክፍል ውስጥ ታጣቂዎች እንደሚታዩ ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ቢቢሲ ዘግቧል።
ጋምቤላ ውስጥ ታጣቂዎች ዛሬ ሰኔ 07/2014 ዓ.ም. ከንጋት 11 ሰዓት ተኩል ጀምሮ ነው ተኩስ ከፈቱ የተባለው። እስካሁን ጥቃቱን የሰነዘሩት ታጣቂዎች እነማን መሆናቸው የታወቀ ነገር የለም።
የታጣቂዎቹ ጥቃት ኢላማ የርዕሰ መስተዳደሩን ጽ/ ቤት ለመቆጣጠር ያለመ ሳይሆን እንደማይቀር የከተማዋ ነዋሪዎች ገልጸዋል።
ሁለት የከተማዋ ነዋሪዎች እንዳሉት በዚሁ ክስተት ሳቢያ ፦
- የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች፣
- የንግድ ሥራዎች
- መደበኛ እንቅስቃሴዎች የተስተጓጎሉ ሲሆን ነዋሪዎችም በቤታቸው ዘግተው መቀመጣቸውን ተናግረዋል።
በክልሉ ርዕሰ መስተዳድሩ ቢሮ አካባቢም ከፍተኛ የተኩስ ድምጽ ላለፉት አራት ሰዓታት እየተሰሙ እንደሚገኙ አንድ በአቅራቢያው ያሉ ነዋሪ አክለዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ በከተማዋ ስለተከሰተው የተኩስ ልውውጥና አሁን ስላለው ሁኔታ " ምንም የምንሰጠው መረጃ የለም’ " ሲሉ መናገጋቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።
በሌላ በኩል የጋምቤላ ቲክቫህ አባላት የላኳቸው መልዕክቶች ፦
📩 " Gambella lay cheger ale mesarya yetateku sewoch bezat eyegebu new tekus betam ale "
📩 " Here Gambella city upto now high fighting really we are worried please inform for concerned body "
📩 " እባካችሁ ጋምቤላ ሰላም አደለም "
በሌላ መረጃ የክልሉ መንግስት ፥ " በጋምቤላ ከተማ ያለውን አንፃራዊ ሰላም ለማደፍረስ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙት የፀረ ሰላም ሀይሎችን ለመመከት የከተማው ማህበረሰብ ሳይረበሽ ከፀጥታ ሀይሉ ጎን እንዲሆን ጥሪ እናቀርባለን " ብሏል።
ዛሬ ከጠዋቱ 12:30 ጀምሮ የጠላት ጦር እና የመንግስት የፀጥታ ሀይል የተኩስ ልውውጥ እያደረጉ ናቸው። " ሲል ገልጾ ዝርዝር ዜናው ይገለፃል ብሏል።
ጠላት ሲል የጠራውን ኃይል በስም አልገለፀም።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
ጋምቤላ በተኩስ ልውውጥ እየተናጠች ነው።
በጋምቤላ ክልል ዋና ከተማ " ጋምቤላ " ዛሬ ከማለዳ ጀምሮ ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ እየተደረገ መሆኑን እና ከፊል የከተማው ክፍል ውስጥ ታጣቂዎች እንደሚታዩ ነዋሪዎችን ዋቢ አድርጎ ቢቢሲ ዘግቧል።
ጋምቤላ ውስጥ ታጣቂዎች ዛሬ ሰኔ 07/2014 ዓ.ም. ከንጋት 11 ሰዓት ተኩል ጀምሮ ነው ተኩስ ከፈቱ የተባለው። እስካሁን ጥቃቱን የሰነዘሩት ታጣቂዎች እነማን መሆናቸው የታወቀ ነገር የለም።
የታጣቂዎቹ ጥቃት ኢላማ የርዕሰ መስተዳደሩን ጽ/ ቤት ለመቆጣጠር ያለመ ሳይሆን እንደማይቀር የከተማዋ ነዋሪዎች ገልጸዋል።
ሁለት የከተማዋ ነዋሪዎች እንዳሉት በዚሁ ክስተት ሳቢያ ፦
- የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች፣
- የንግድ ሥራዎች
- መደበኛ እንቅስቃሴዎች የተስተጓጎሉ ሲሆን ነዋሪዎችም በቤታቸው ዘግተው መቀመጣቸውን ተናግረዋል።
በክልሉ ርዕሰ መስተዳድሩ ቢሮ አካባቢም ከፍተኛ የተኩስ ድምጽ ላለፉት አራት ሰዓታት እየተሰሙ እንደሚገኙ አንድ በአቅራቢያው ያሉ ነዋሪ አክለዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ በከተማዋ ስለተከሰተው የተኩስ ልውውጥና አሁን ስላለው ሁኔታ " ምንም የምንሰጠው መረጃ የለም’ " ሲሉ መናገጋቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።
በሌላ በኩል የጋምቤላ ቲክቫህ አባላት የላኳቸው መልዕክቶች ፦
📩 " Gambella lay cheger ale mesarya yetateku sewoch bezat eyegebu new tekus betam ale "
📩 " Here Gambella city upto now high fighting really we are worried please inform for concerned body "
📩 " እባካችሁ ጋምቤላ ሰላም አደለም "
በሌላ መረጃ የክልሉ መንግስት ፥ " በጋምቤላ ከተማ ያለውን አንፃራዊ ሰላም ለማደፍረስ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙት የፀረ ሰላም ሀይሎችን ለመመከት የከተማው ማህበረሰብ ሳይረበሽ ከፀጥታ ሀይሉ ጎን እንዲሆን ጥሪ እናቀርባለን " ብሏል።
ዛሬ ከጠዋቱ 12:30 ጀምሮ የጠላት ጦር እና የመንግስት የፀጥታ ሀይል የተኩስ ልውውጥ እያደረጉ ናቸው። " ሲል ገልጾ ዝርዝር ዜናው ይገለፃል ብሏል።
ጠላት ሲል የጠራውን ኃይል በስም አልገለፀም።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT