#ICRC #Oromia #Afar
ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሀረርጌ ዞን፣ ኩምቢ ለሚገኙ 5000 አባወራዎች የእንስሳት መኖ እያከፋፈለ ይገኛል።
ስርጭቱ በአካባቢው ለተከሰተው ድርቅ ምላሽ ሲሆን በዚህ ኦፕሬሽን እስከ 150,000 እንስሳት ይመገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ድርጅቱ አስታውቋል።
በሌላ በኩል ድርጅቱ ፤ ባሳለፍነው ሳምንት በአፋር ክልል ሲልሳ ለሚገኙ 9,000 የተፈናቀሉ ሰዎች መሰረታዊ የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሶችን ማለትም ሶላር የእጅ ባትሪዎችን፣ ጀሪካኖችን፣ የማዕድ ቤት እቃዎችን፣ ምንጣፍ እና መጠለያ ድጋፍ ማድረጉን ገልጿል።
@tikvahethiopia
ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሀረርጌ ዞን፣ ኩምቢ ለሚገኙ 5000 አባወራዎች የእንስሳት መኖ እያከፋፈለ ይገኛል።
ስርጭቱ በአካባቢው ለተከሰተው ድርቅ ምላሽ ሲሆን በዚህ ኦፕሬሽን እስከ 150,000 እንስሳት ይመገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ድርጅቱ አስታውቋል።
በሌላ በኩል ድርጅቱ ፤ ባሳለፍነው ሳምንት በአፋር ክልል ሲልሳ ለሚገኙ 9,000 የተፈናቀሉ ሰዎች መሰረታዊ የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሶችን ማለትም ሶላር የእጅ ባትሪዎችን፣ ጀሪካኖችን፣ የማዕድ ቤት እቃዎችን፣ ምንጣፍ እና መጠለያ ድጋፍ ማድረጉን ገልጿል።
@tikvahethiopia
#Somali #Afar
በሶማሌ እና አፋር ክልል አዋሳኝ ቀበሌዎች የሚከሰቱ ግጭቶችን በዘላቂነት መፍታት እንዲቻል 2ቱ ክልሎች ከስምምነት መድረሳቸውን አስታወቁ።
ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት ያስችላል የተባለው መሠረታዊ ስምምነት የታጠቁ ኃይሎች ከግጭት አካባቢዎች እንዲወጡ እና የፌደራል ፀጥታ ኃይሎች ወደነዚህ ቦታዎች እንዲገቡ የሚፈቅድ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ዑስማን መናገራቸውን የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል።
በአዋሳኝ ቀበሌዎች በየቦታው ተኩስ ፣ ስርቆት እና መፈናቀል ይከሰቱ እንደነበር የተናገሩት አቶ ኢብራሂም ዘላቂ ሰላም ለማምጣትም የተፈናቀሉ ሰዎችን ወደቀያቸው መመለስ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።
አቶ ኢብራሂም « ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ችግር እንዳይከሰት፣… ዘላቂ የሆነ ሰላም እንዲመጣ እና ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ሚና መሆን እንዳለበትም ነው ትናንት ከስምምነት ላይ የደረስነው።» ብለዋል።
የሶማሌ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ዑስማን ማሣረጊያ እንዲሆን የሁለቱ ክልሎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ኮንፈረንስ እንደሚያካሂዱም ተናግረዋል።
በሶማሌ ክልል መቀመጫ ጅግጅጋ በተካሄደው ውይይት የሰላም ሚንስትሩ አቶ ብናልፍ አንዱአለም ጨምሮ የአፋር እና የሶማሌ ክልል ከፍተኛ ባለስልጣናት ተገኝተው እንደነበር ሬድዮ ጣቢያው ዘግቧል።
@tikvahethiopia
በሶማሌ እና አፋር ክልል አዋሳኝ ቀበሌዎች የሚከሰቱ ግጭቶችን በዘላቂነት መፍታት እንዲቻል 2ቱ ክልሎች ከስምምነት መድረሳቸውን አስታወቁ።
ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት ያስችላል የተባለው መሠረታዊ ስምምነት የታጠቁ ኃይሎች ከግጭት አካባቢዎች እንዲወጡ እና የፌደራል ፀጥታ ኃይሎች ወደነዚህ ቦታዎች እንዲገቡ የሚፈቅድ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ዑስማን መናገራቸውን የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል።
በአዋሳኝ ቀበሌዎች በየቦታው ተኩስ ፣ ስርቆት እና መፈናቀል ይከሰቱ እንደነበር የተናገሩት አቶ ኢብራሂም ዘላቂ ሰላም ለማምጣትም የተፈናቀሉ ሰዎችን ወደቀያቸው መመለስ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።
አቶ ኢብራሂም « ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ችግር እንዳይከሰት፣… ዘላቂ የሆነ ሰላም እንዲመጣ እና ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ሚና መሆን እንዳለበትም ነው ትናንት ከስምምነት ላይ የደረስነው።» ብለዋል።
የሶማሌ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ዑስማን ማሣረጊያ እንዲሆን የሁለቱ ክልሎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ኮንፈረንስ እንደሚያካሂዱም ተናግረዋል።
በሶማሌ ክልል መቀመጫ ጅግጅጋ በተካሄደው ውይይት የሰላም ሚንስትሩ አቶ ብናልፍ አንዱአለም ጨምሮ የአፋር እና የሶማሌ ክልል ከፍተኛ ባለስልጣናት ተገኝተው እንደነበር ሬድዮ ጣቢያው ዘግቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#WFP #Ethiopia የግጭት ማቆም ውሳኔ ይፋ ከተደረገበት ከመጋቢት ወር ጀምሮ ወደ ትግራይ ክልል ከሚገባው እርዳታ #ከፍተኛ መጠን ያለው ቁሳቁስ በዚህ ሳምንት ወደ ክልሉ መግባቱን የዓለም ምግብ ፕሮግራም አስታውቋል። በዚህ ሣምንት ወደ ትግራይ የገባው 15 ሺህ ቶን ምግብ እና ሌሎች የነፍስ አድን አቅርቦቶች ሲሆን አሁንም ተጨማሪ እርዳታ ወደ ክልሉ እያመራ መሆኑን WFP ገልጿል። ኤድሪያብ ቫን ደር…
#Afar
ሰይድ ሞሃመድ (የዓለም አቀፉ ህፃናት አድን ድርጅት የአፋር ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ዋና ኃላፊ) ለቪኦኤ በሰጡት ቃል የተናገሩት ፦
" ማህበረሰቡ ድብርብርብ ሸክም ነው የገጠመው ፤ የመጀመሪያው በርካታ የውሃ አቅርቦት እና ሌሎችም መሰረታዊ አገልግሎት ተቋማትን ስራ ያስተጓጎለው ፤ ያቋረጠው ግጭት በዚህ ላይ ድርቅ ሌላው ፈተና ነው።
ላለፉት በርካታ አመታት አፋር በተከታታይ በድርቅ ሲጠቃ ነው የቆየው ፤ ስለሆነም ድርቁ ለአፋር ማህበረሰብ ሌላ ፈተና ነው ማለት ይቻላል ። "
@tikvahethiopia
ሰይድ ሞሃመድ (የዓለም አቀፉ ህፃናት አድን ድርጅት የአፋር ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ዋና ኃላፊ) ለቪኦኤ በሰጡት ቃል የተናገሩት ፦
" ማህበረሰቡ ድብርብርብ ሸክም ነው የገጠመው ፤ የመጀመሪያው በርካታ የውሃ አቅርቦት እና ሌሎችም መሰረታዊ አገልግሎት ተቋማትን ስራ ያስተጓጎለው ፤ ያቋረጠው ግጭት በዚህ ላይ ድርቅ ሌላው ፈተና ነው።
ላለፉት በርካታ አመታት አፋር በተከታታይ በድርቅ ሲጠቃ ነው የቆየው ፤ ስለሆነም ድርቁ ለአፋር ማህበረሰብ ሌላ ፈተና ነው ማለት ይቻላል ። "
@tikvahethiopia