ዲቪ (DV) 2023 ይፋ ሆኗል።
የ2023 ዲቪ ሎተሪ ዛሬ ማታ ይፋ የሆነ ሲሆን ሞልታችሁ ስትጠባበቁ የነበራችሁ በሙሉ የዲቪ ውጤታችሁን በዚህ ሊንክ https://dvprogram.state.gov/ESC/Default.aspx መመልከት ትችላላችሁ ተብሏል።
@tikvahethiopia
የ2023 ዲቪ ሎተሪ ዛሬ ማታ ይፋ የሆነ ሲሆን ሞልታችሁ ስትጠባበቁ የነበራችሁ በሙሉ የዲቪ ውጤታችሁን በዚህ ሊንክ https://dvprogram.state.gov/ESC/Default.aspx መመልከት ትችላላችሁ ተብሏል።
@tikvahethiopia
ፎቶ ፦ የነዳጅ ሰልፍ በአዲስ አበባ ከተማ !
ነዳጅ ለማግኘት ረጅም የሆኑ ሰልፎችን መጠበቅ ከተጀመረ ሰነባብቷል። ይህ ችግር በርካታ ጊዜያት ተደጋግሞ ቢነሳም መፍትሄ አልተገኘለትም።
በዚህ ምክንያት ዜጎች ሰዓታቸውን በነዳጅ ሰልፍ ሳይባክን ሰርተው ለመብላት የዕለት ገቢያቸውን ለማግኘት ፈተና እየሆነባቸው ነው።
ተሽከርካሪ ያላቸው ሰራተኞችም ስራቸውን እየተው ለነዳጅ እየተሰለፉ በመሆኑ ስራቸው እየተበደለ ነው።
ነዳጅ ላይ የዋጋ ማስተካከያ ቢደረግም በተባለው ዋጋ ለማግኘት እንኳን ፈተና ሆኗል። የዓለም ነዳጅ ዋጋ ንረት እንደተጠበቀ ሆኖ ኢትዮጵያ ውስጥ እውነት በቂ ነዳጅ ስለሌለ/ስለማይገባ ነው ? ወይስ ያለውን በአግባቡ የማስተዳደር ችግር ? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው።
በክልል ከተሞች ማደያዎች ነዳጅ የለም ይላሉ ፤ ህገወጥ በሆነ መልኩ በየመንገዱ፣ በየሱቁ ላይ ሲሸጥ ይታያል ፤ ማደያዎች ለሊት ላይ በጄሪካን ለተለያዩ አካላት እንደሚቀዱ ነው የሚነገረው።
ይህን ለማስቆም ሰፊ ጥረት ሲደረግ አይታይም፤ ምክንያቱም ችግሩ ወራትን ስላስቆጠረ በዚህ ህገወጥ ድርጊት የሚሳተፉ እና እጃቸው ያለበት ብዙ አካላት እንዳሉ ግን እሙን ነው።
ይህ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣ ችግር ልጓም ካልተበጀለት የሚፈጥረው ቀውስ ከፍተኛ ነውና ትኩረትን ይሻል።
@tikvahethiopia
ነዳጅ ለማግኘት ረጅም የሆኑ ሰልፎችን መጠበቅ ከተጀመረ ሰነባብቷል። ይህ ችግር በርካታ ጊዜያት ተደጋግሞ ቢነሳም መፍትሄ አልተገኘለትም።
በዚህ ምክንያት ዜጎች ሰዓታቸውን በነዳጅ ሰልፍ ሳይባክን ሰርተው ለመብላት የዕለት ገቢያቸውን ለማግኘት ፈተና እየሆነባቸው ነው።
ተሽከርካሪ ያላቸው ሰራተኞችም ስራቸውን እየተው ለነዳጅ እየተሰለፉ በመሆኑ ስራቸው እየተበደለ ነው።
ነዳጅ ላይ የዋጋ ማስተካከያ ቢደረግም በተባለው ዋጋ ለማግኘት እንኳን ፈተና ሆኗል። የዓለም ነዳጅ ዋጋ ንረት እንደተጠበቀ ሆኖ ኢትዮጵያ ውስጥ እውነት በቂ ነዳጅ ስለሌለ/ስለማይገባ ነው ? ወይስ ያለውን በአግባቡ የማስተዳደር ችግር ? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው።
በክልል ከተሞች ማደያዎች ነዳጅ የለም ይላሉ ፤ ህገወጥ በሆነ መልኩ በየመንገዱ፣ በየሱቁ ላይ ሲሸጥ ይታያል ፤ ማደያዎች ለሊት ላይ በጄሪካን ለተለያዩ አካላት እንደሚቀዱ ነው የሚነገረው።
ይህን ለማስቆም ሰፊ ጥረት ሲደረግ አይታይም፤ ምክንያቱም ችግሩ ወራትን ስላስቆጠረ በዚህ ህገወጥ ድርጊት የሚሳተፉ እና እጃቸው ያለበት ብዙ አካላት እንዳሉ ግን እሙን ነው።
ይህ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣ ችግር ልጓም ካልተበጀለት የሚፈጥረው ቀውስ ከፍተኛ ነውና ትኩረትን ይሻል።
@tikvahethiopia
" የነዳጅ ዋጋን ለማረጋጋት በሚያዚያ ወር 12.8 ቢሊዮን ብር በላይ ድጎማ ተደርጓል " - የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን
የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ፤ የዓለም ነዳጅ ዋጋ ባሻቀበበት በዚህ ወቅት መንግሥት በሚያዚያ ወር ብቻ የነዳጅ ዋጋን ለማረጋጋት ከ12.8 ቢሊዮን ብር በላይ ድጎማ ማድረጉ ገልጿል።
ይህን የተገለፀው ከቀናት በፊት የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ስለ አዲሱ የታለመ የነዳጅ ድጎማና ዋጋ ማሻሻያ በተመለከተ ለሚዲያ አካላት በተዘጋጀ መድረክ ላይ ነው።
እስከ ሚያዚያ ወር ማጠናቀቂያ ድረስ በአንድ ወር ብቻ ከ12.8 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ድጎማ መደረጉ ታውቋል።
ከሐምሌ 2014 ዓ.ም. አንስቶ በጠቅላላው ባለፉት አሥር ወራት በመንግሥት የተደረገው የተመዘገበ የድጎማ መጠን ከ73.5 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን ሪፖርተር ጋዜጣ የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋቢ አድርጎ አስነብቧል።
https://telegra.ph/Reporter-05-08
@tikvahethiopia
የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ፤ የዓለም ነዳጅ ዋጋ ባሻቀበበት በዚህ ወቅት መንግሥት በሚያዚያ ወር ብቻ የነዳጅ ዋጋን ለማረጋጋት ከ12.8 ቢሊዮን ብር በላይ ድጎማ ማድረጉ ገልጿል።
ይህን የተገለፀው ከቀናት በፊት የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ስለ አዲሱ የታለመ የነዳጅ ድጎማና ዋጋ ማሻሻያ በተመለከተ ለሚዲያ አካላት በተዘጋጀ መድረክ ላይ ነው።
እስከ ሚያዚያ ወር ማጠናቀቂያ ድረስ በአንድ ወር ብቻ ከ12.8 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ድጎማ መደረጉ ታውቋል።
ከሐምሌ 2014 ዓ.ም. አንስቶ በጠቅላላው ባለፉት አሥር ወራት በመንግሥት የተደረገው የተመዘገበ የድጎማ መጠን ከ73.5 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን ሪፖርተር ጋዜጣ የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋቢ አድርጎ አስነብቧል።
https://telegra.ph/Reporter-05-08
@tikvahethiopia
#ጥቆማ
ነፃ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና !
በቅዱስ ጳዉሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ኮሌጅ የዓይን ህክምና ትምህርት ክፍል HCP በተባለ ግብረሰናይ ድርጅት እገዛ 500 የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና /CATARACT SURGERY/ ከሰኔ 6 እስከ ሰኔ 12/2014 ዓ.ም ለማድረግ አስቧል፡፡
ይህን ነፃ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና ለማድረግ ቅድመ ምርመራ፣ ልየታና ምዝገባ በግንቦት ወር ባሉት ቅዳሜና እሁድ ቀናቶች ማለትም (ግንቦት 6፣ 7፣ 13፣ 14፣20፣ 21፣27 ፣28 ) ይካሄዳል።
በኮሌጁ የስልክ አገልግሎት 976 በመደወል ለቅድመ ምርመራ፣ ልየታና ምዝገባ ቀጠሮ ማስያዝ ይቻላል።
#ማሳሰቢያ ፡- በስልክ ቀጠሮ ያልተሰጠዉ ታካሚ ቅድመ ምርመራም፣ ልየታም ይሁን ምዝገባ ማድረግ አይችልም ተብሏል።
(ውድ ቤተሰቦቻችን መልዕክቱን አጋሩ)
@tikvahethiopia
ነፃ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና !
በቅዱስ ጳዉሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ኮሌጅ የዓይን ህክምና ትምህርት ክፍል HCP በተባለ ግብረሰናይ ድርጅት እገዛ 500 የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና /CATARACT SURGERY/ ከሰኔ 6 እስከ ሰኔ 12/2014 ዓ.ም ለማድረግ አስቧል፡፡
ይህን ነፃ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና ለማድረግ ቅድመ ምርመራ፣ ልየታና ምዝገባ በግንቦት ወር ባሉት ቅዳሜና እሁድ ቀናቶች ማለትም (ግንቦት 6፣ 7፣ 13፣ 14፣20፣ 21፣27 ፣28 ) ይካሄዳል።
በኮሌጁ የስልክ አገልግሎት 976 በመደወል ለቅድመ ምርመራ፣ ልየታና ምዝገባ ቀጠሮ ማስያዝ ይቻላል።
#ማሳሰቢያ ፡- በስልክ ቀጠሮ ያልተሰጠዉ ታካሚ ቅድመ ምርመራም፣ ልየታም ይሁን ምዝገባ ማድረግ አይችልም ተብሏል።
(ውድ ቤተሰቦቻችን መልዕክቱን አጋሩ)
@tikvahethiopia
የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ፦
🛢️ከአንድ አመት በፊት 👉 68 የአሜሪካ ዶላር
🛢️አሁን 👉 113 የአሜሪካ ዶላር
ለነዳጅ ዋጋ እንዲህ መናር ሩስያ እና ዩክሬን የገቡበት እና ዛሬም ድረስ መቋጫ ያላገኘው ጦርነት ዋነኛው ሲሆን ጦርነቱ በአጠቃላይ ዓለምን አናግቷል ማለት ይቻላል።
@tikvahethiopia
🛢️ከአንድ አመት በፊት 👉 68 የአሜሪካ ዶላር
🛢️አሁን 👉 113 የአሜሪካ ዶላር
ለነዳጅ ዋጋ እንዲህ መናር ሩስያ እና ዩክሬን የገቡበት እና ዛሬም ድረስ መቋጫ ያላገኘው ጦርነት ዋነኛው ሲሆን ጦርነቱ በአጠቃላይ ዓለምን አናግቷል ማለት ይቻላል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሌተናል_ኮሎኔል_ፍሥሐ_ደስታ በድረግ ዘመነ መንግስት ኢትዮጵያን በምክትል ፕሬዝዳንትነት የመሩት ሌ/ኮሎኔል ፍሰሐ ደስታ በ81 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። የቀድሞው መሪ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃ/ማሪያም ምክትል በመሆን የኢሕዲሪ ምክትል ፕሬዝዳንት የነበሩት ሌ/ኮሎኔል ፍሰሐ ደስታ፣ ኢሕአዴግ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ ለ20 ዓመታት ያህል በእስር ቆይተዋል። ቤተሰቦቻቸው ለቢቢሲ በሰጡት ቃል ፤…
ፎቶ ፦ ዛሬ የቀድሞ የኢትዮጵያ ምክትል ፕሬዜዳንት ሌተናል ኮለኔል ፍስሐ ደስታ የቀብር ሥነ ስርዓት በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል።
በቀብር ስነ ስርዓቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስን ጨምሮ የሃይማኖት አባቶች እንዲሁም የቀድሞ የስራ ባልደረቦች እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ተገኝተው ነበር።
ሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ በህይወት ሳሉ " አብዮቱ እና ትዝታዬ " በተሰኛው መፃፍ ላይ ከፃፉት ፦
" ቂምን ቋጥሮ ቁርሾን ተሸክሞ ዴሞክራሲና ሀገር ለመገንባት ፣ እድገትን እና ብልፅግና ለማምጣት የማይታሰብ ነው። በመሆኑም በዚያ አስከፊ የርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ያለፍነው ሁሉ የታሪኩ አካልና የትውልዱ አባል በመሆናችን የታመቁ ቅራኔዎችን ከማራገብ ይልቅ ያለፈውን ታሪካችንንና ያለንበትን ሁኔታ በቅንነትና በንፁህ ሕሊና በመገምገም ይቅር ለታሪክና ለትውልድ መባባል አለብን "
▪️ሌተናል ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ ከአባታቸው ብላታ ደስታ ወልደማርያም ከእናታቸው ወ/ሮ ሕርይተሥላሴ ትኩዕ ሚያዚያ 13/1933 ትግራይ ዓድዋ ከተማ ነው የተወለዱት ፤ አርብ ሚያዚያ 28/2014 ዓ. ም. እኩለ ሌሊት በ81 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፤ ሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ ባለትዳርና የ1 ልጅ አባት ነበሩ▪️
@tikvahethiopia
በቀብር ስነ ስርዓቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስን ጨምሮ የሃይማኖት አባቶች እንዲሁም የቀድሞ የስራ ባልደረቦች እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ተገኝተው ነበር።
ሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ በህይወት ሳሉ " አብዮቱ እና ትዝታዬ " በተሰኛው መፃፍ ላይ ከፃፉት ፦
" ቂምን ቋጥሮ ቁርሾን ተሸክሞ ዴሞክራሲና ሀገር ለመገንባት ፣ እድገትን እና ብልፅግና ለማምጣት የማይታሰብ ነው። በመሆኑም በዚያ አስከፊ የርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ያለፍነው ሁሉ የታሪኩ አካልና የትውልዱ አባል በመሆናችን የታመቁ ቅራኔዎችን ከማራገብ ይልቅ ያለፈውን ታሪካችንንና ያለንበትን ሁኔታ በቅንነትና በንፁህ ሕሊና በመገምገም ይቅር ለታሪክና ለትውልድ መባባል አለብን "
▪️ሌተናል ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ ከአባታቸው ብላታ ደስታ ወልደማርያም ከእናታቸው ወ/ሮ ሕርይተሥላሴ ትኩዕ ሚያዚያ 13/1933 ትግራይ ዓድዋ ከተማ ነው የተወለዱት ፤ አርብ ሚያዚያ 28/2014 ዓ. ም. እኩለ ሌሊት በ81 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፤ ሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ ባለትዳርና የ1 ልጅ አባት ነበሩ▪️
@tikvahethiopia
የአሠልጣኞች ሥልጠና ጥሪ - #CARD
ለሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የሥነ ዜጋና ሥነ ምግባር ትምህርት መምህራን መሠረታዊ የሰብዓዊ መብቶች ፅንሰ-ሐሳቦች ላይ ያተኮረ የአሠልጣኞች ሥልጠና !
የመብቶች ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (CARD) በአዲስ አበባ፣ ቢሾፍቱ ፣ አዳማ፣ ደብረብርሀን፣ ድሬዳዋ፣ ሀዋሳና ሀረሪ ክልሎች ውስጥ ለሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የስነዜጋና ስነምግባር ትምህርት መምህራን የሰብዓዊ መብቶች ፅንሰ-ሐሳቦች ላይ ያተኮረ የአሠልጣኞች ሥልጠና ለመስጠት አቅዷል።
ሥልጠናው “የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች አዲስ ትውልድ’’ የተባለውና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ላይ ትኩረቱን አድርጎ የሚሠራው ፕሮጀክት አንዱ አካል ነው መሆኑን ገልጿል።
ከስልጠናው በኋላ ተቋሙ በተጠቀሱት አካባቢዎች በቀጣይነት ለሚኖረው የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች መሰረታዊ የሰብዓዊ መብቶች ስልጠና ሂደቶችን በማስተባበር ተሳታፊዎች እንዲሆኑ ለማድረግ አቅዷል።
ለመመዝገብ https://bit.ly/3vu4rZK
@tikvahethiopia
ለሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የሥነ ዜጋና ሥነ ምግባር ትምህርት መምህራን መሠረታዊ የሰብዓዊ መብቶች ፅንሰ-ሐሳቦች ላይ ያተኮረ የአሠልጣኞች ሥልጠና !
የመብቶች ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (CARD) በአዲስ አበባ፣ ቢሾፍቱ ፣ አዳማ፣ ደብረብርሀን፣ ድሬዳዋ፣ ሀዋሳና ሀረሪ ክልሎች ውስጥ ለሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የስነዜጋና ስነምግባር ትምህርት መምህራን የሰብዓዊ መብቶች ፅንሰ-ሐሳቦች ላይ ያተኮረ የአሠልጣኞች ሥልጠና ለመስጠት አቅዷል።
ሥልጠናው “የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች አዲስ ትውልድ’’ የተባለውና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ላይ ትኩረቱን አድርጎ የሚሠራው ፕሮጀክት አንዱ አካል ነው መሆኑን ገልጿል።
ከስልጠናው በኋላ ተቋሙ በተጠቀሱት አካባቢዎች በቀጣይነት ለሚኖረው የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች መሰረታዊ የሰብዓዊ መብቶች ስልጠና ሂደቶችን በማስተባበር ተሳታፊዎች እንዲሆኑ ለማድረግ አቅዷል።
ለመመዝገብ https://bit.ly/3vu4rZK
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዲቪ (DV) 2023 ይፋ ሆኗል። የ2023 ዲቪ ሎተሪ ዛሬ ማታ ይፋ የሆነ ሲሆን ሞልታችሁ ስትጠባበቁ የነበራችሁ በሙሉ የዲቪ ውጤታችሁን በዚህ ሊንክ https://dvprogram.state.gov/ESC/Default.aspx መመልከት ትችላላችሁ ተብሏል። @tikvahethiopia
#ዲቪ_ሎተሪ
ዳይቨርሲቲ ቪዛ ሎተሪ (ዲቪ) አሜሪካ በዕጣ የምትሰጠው የቪዛ መርሀ ግብር ሲሆን ከተወሰኑ ሀገራት በስተቀር ከመላው ዓለም በየዓመቱ ከ50 ሺህ በላይ ፍልሰተኖች አሜሪካ ገብተው የመኖር እና የመስራት ፍቃድ ያገኛሉ።
የአሜሪካ መንግስት ከዐለም የተለያዩ ሀገራት ዜጎችን የዲቪ ሎተሪን እየተጠቀሙ ወደ ግዛቱ እንዲገቡ ማድረግ ከጀመር በርካታ አመታት ተቆጥረዋል።
ለተሻለ ኑሮና ጥሩ የሆነ ግቢ አግኝቶ ሰርቶ ቤተሰብን ለመቀየረ የዲቪ ሎተሪ የሚያመለክቱ በየዓመቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ናቸው።
አሜሪካ ከተወሰኑ ሀገራት በቀር በመላው ዓለም ላሉ ሀገራት በምታመቻቸው ከ50 ሺህ በላይ የቪዛ ዕድል አንድ ሀገር የሚደርሰው ከሰባት በመቶ የማይበልጥ ነው።
ከሀገራችን ኢትዮጵያ ለዚህ ዕድል የሚያመለክቱ እጅግ በርካቶች ናቸው።
ለዲቪ የሚያመለክቱ አንድም በትምህርት አልያም በስራ ልምድ የሚወጡ መስፍርቶችን እንዲያሟሉ የሚጠበቅ ሲሆን በትምህርት ደረጃ ቢያንስ የ2ኛ ደረጃን ማጠናቀቅ አለባቸው፤ የኮሌጅና የዩኒቨርሲቲ ምሩቃን ቢሆኑ ደግሞ ጥሩ ነው፤ የትምህርት መመዘኛውን የማያሟሉ በስራ ልምድ ማካካስ የሚችሉ ሲሆን የስራ ልምድ ማስረጃ መያዝ አለባቸው።
በየዓመቱ የዲቪ ሎተሪ ሲሞላ አልያም ሲወጣ የማጭበርበር ድርጊቶች በስፋት ይስተዋላል፤ አጭበርባሪዎች ሰዎችን " የዲቪ እድል ደርሷችኃል " በማለት ያጭበረብራሉ፤ ማንኛውም ሰው ለዲቪ ሲያመለክት ሆነ ውጤት በሚታያይበት ወቅት የአሜሪካ መንግስት ለዚህ ክትትል አንዳች ክፍያ አያስከፍልም።
የ " 2023 የዲቪ ሎተሪ ዕጣ " ትላንት ምሽት ይፋ የተደረገ ሲሆን በዚህ ሊምክ መመልከት ይቻላል : https://dvprogram.state.gov/ESC/Default.aspx
@tikvahethiopia
ዳይቨርሲቲ ቪዛ ሎተሪ (ዲቪ) አሜሪካ በዕጣ የምትሰጠው የቪዛ መርሀ ግብር ሲሆን ከተወሰኑ ሀገራት በስተቀር ከመላው ዓለም በየዓመቱ ከ50 ሺህ በላይ ፍልሰተኖች አሜሪካ ገብተው የመኖር እና የመስራት ፍቃድ ያገኛሉ።
የአሜሪካ መንግስት ከዐለም የተለያዩ ሀገራት ዜጎችን የዲቪ ሎተሪን እየተጠቀሙ ወደ ግዛቱ እንዲገቡ ማድረግ ከጀመር በርካታ አመታት ተቆጥረዋል።
ለተሻለ ኑሮና ጥሩ የሆነ ግቢ አግኝቶ ሰርቶ ቤተሰብን ለመቀየረ የዲቪ ሎተሪ የሚያመለክቱ በየዓመቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ናቸው።
አሜሪካ ከተወሰኑ ሀገራት በቀር በመላው ዓለም ላሉ ሀገራት በምታመቻቸው ከ50 ሺህ በላይ የቪዛ ዕድል አንድ ሀገር የሚደርሰው ከሰባት በመቶ የማይበልጥ ነው።
ከሀገራችን ኢትዮጵያ ለዚህ ዕድል የሚያመለክቱ እጅግ በርካቶች ናቸው።
ለዲቪ የሚያመለክቱ አንድም በትምህርት አልያም በስራ ልምድ የሚወጡ መስፍርቶችን እንዲያሟሉ የሚጠበቅ ሲሆን በትምህርት ደረጃ ቢያንስ የ2ኛ ደረጃን ማጠናቀቅ አለባቸው፤ የኮሌጅና የዩኒቨርሲቲ ምሩቃን ቢሆኑ ደግሞ ጥሩ ነው፤ የትምህርት መመዘኛውን የማያሟሉ በስራ ልምድ ማካካስ የሚችሉ ሲሆን የስራ ልምድ ማስረጃ መያዝ አለባቸው።
በየዓመቱ የዲቪ ሎተሪ ሲሞላ አልያም ሲወጣ የማጭበርበር ድርጊቶች በስፋት ይስተዋላል፤ አጭበርባሪዎች ሰዎችን " የዲቪ እድል ደርሷችኃል " በማለት ያጭበረብራሉ፤ ማንኛውም ሰው ለዲቪ ሲያመለክት ሆነ ውጤት በሚታያይበት ወቅት የአሜሪካ መንግስት ለዚህ ክትትል አንዳች ክፍያ አያስከፍልም።
የ " 2023 የዲቪ ሎተሪ ዕጣ " ትላንት ምሽት ይፋ የተደረገ ሲሆን በዚህ ሊምክ መመልከት ይቻላል : https://dvprogram.state.gov/ESC/Default.aspx
@tikvahethiopia