TIKVAH-ETHIOPIA
#SNNPRS የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል መግለጫ አውጥቷል። የክልሉ መንግስት በመግለጫው ትላንት ሚያዝያ 20/2014 ዓ/ም በስልጤ ዞን በወራቤ ከተማ እና በሳንኩራ ወረዳ ላይ በሀይማኖት ተቋማት ላይ ያነጣጠረ ጥቃት መፈፀሙን ገልጿል። የተፈፀመው ጥቃት ለዘመናት ተቻችለው እና ተከባብረው በኖሩ የልዩ ልዩ እምነት ተከታይ ህዝቦች ላይ የሚፈጥረው አሉታዊ ተጽዕኖ ከፍተኛ ነው ብሏል። …
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ፤ ወንጀልን በሌላ ወንጀል ለማረም መሞከር ሕገ ወጥነት ነው ሲል ገልጿል።
ጉባኤው በደቡብ ክልል ስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አብያተ ክርስቲያናት እና በፕሮቴስታንት አማኞች ቤተ አምልኮዎች ላይ ሕገ ወጥና የወንጅል ተግባር መፈፀሙን ገልጿል።
የፈፀመውን ወንጀልና ህገወጥ ድርጊት በእጅጉ እንደሚያወግዝ አሳውቋል።
የተፈፀመው ተግባር በየትኛውም ሃይማኖት ተቀባይነት የሌለው መሆኑን ገልጾ ደረቅ ወንጅል እና በህግ ሊያስጠይቅ የሚገባው ተግባር መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን ጉባኤው ገልጿል።
(ዝርዝር መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
ጉባኤው በደቡብ ክልል ስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አብያተ ክርስቲያናት እና በፕሮቴስታንት አማኞች ቤተ አምልኮዎች ላይ ሕገ ወጥና የወንጅል ተግባር መፈፀሙን ገልጿል።
የፈፀመውን ወንጀልና ህገወጥ ድርጊት በእጅጉ እንደሚያወግዝ አሳውቋል።
የተፈፀመው ተግባር በየትኛውም ሃይማኖት ተቀባይነት የሌለው መሆኑን ገልጾ ደረቅ ወንጅል እና በህግ ሊያስጠይቅ የሚገባው ተግባር መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን ጉባኤው ገልጿል።
(ዝርዝር መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
#መልዕክት
ከሰዓታት በኃላ 2ኛው " የታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር በኢትዮጵያ " መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
ለታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር 2 ለመታደም ሲመጡ ፦
👉 የራሳችሁን መስገጃ ይዛችሁ ኑ።
👉 አዘጋጆች የሚዘጋጁት ምግብ ቢኖርም ሁሉም የቻለውን ያህል ለሰዎች ጭምር የሚሆን ምግብ ይዞ ይምጣ።
👉 ሁሉም የተመገበበትን እቃ የሚያነሳበትን ፌስታል መያዝ እንዳይዘነጋ።
👉 በመሃል ሌባ ሊኖር ስለሚችል ከፍተኛ ጥንቃቄ ይደረግ።
👉 አቅመ ዳካማዎችን፣ታላላቆችንና ሴቶች የተሻለ ቦታ እንዲያገኙ አድርጉ።
👉 ለአስተናጋጆች፣ ለኻዲሞችና ለፀጥታ አካላት ፍፁም ታዛዥ ይሁኑ።
👉 በጦርነትና በድርቅ የተጎዱ ወገኖችን ለማገዝ ለሚንቀሳቀሱ አስተባባሪዎች ድጋፍ ያድርጉ።
👉 እርስ በእርስ በመከባበር እና በመተዛዘን እጅግ የሰለጠነና ምስኪኖችን ታሳቢ ያደረገ ኢፍጣር እንዲሆን ሁላችንም ባለቤቶች እንደሆንን በማሰብ ተግባራዊ ያድርጉ።
📞 ማንኛውም አይነት አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙ በቦታው ለሚገኙ የፀጥታ አካላትና አስተባባሪዎች ወይም በፖሊስ የመረጃ ስልኮች 0111110111 እና ነፃ የስልክ መስመር 991 ላይ በመደወልና መረጃ በመስጠት ይተባበሩ።
(ከአዘጋጆች)
መልካም የኢፍጣር ስነስርዓት !
#ሼር #Share
@tikvahethiopia
ከሰዓታት በኃላ 2ኛው " የታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር በኢትዮጵያ " መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
ለታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር 2 ለመታደም ሲመጡ ፦
👉 የራሳችሁን መስገጃ ይዛችሁ ኑ።
👉 አዘጋጆች የሚዘጋጁት ምግብ ቢኖርም ሁሉም የቻለውን ያህል ለሰዎች ጭምር የሚሆን ምግብ ይዞ ይምጣ።
👉 ሁሉም የተመገበበትን እቃ የሚያነሳበትን ፌስታል መያዝ እንዳይዘነጋ።
👉 በመሃል ሌባ ሊኖር ስለሚችል ከፍተኛ ጥንቃቄ ይደረግ።
👉 አቅመ ዳካማዎችን፣ታላላቆችንና ሴቶች የተሻለ ቦታ እንዲያገኙ አድርጉ።
👉 ለአስተናጋጆች፣ ለኻዲሞችና ለፀጥታ አካላት ፍፁም ታዛዥ ይሁኑ።
👉 በጦርነትና በድርቅ የተጎዱ ወገኖችን ለማገዝ ለሚንቀሳቀሱ አስተባባሪዎች ድጋፍ ያድርጉ።
👉 እርስ በእርስ በመከባበር እና በመተዛዘን እጅግ የሰለጠነና ምስኪኖችን ታሳቢ ያደረገ ኢፍጣር እንዲሆን ሁላችንም ባለቤቶች እንደሆንን በማሰብ ተግባራዊ ያድርጉ።
📞 ማንኛውም አይነት አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙ በቦታው ለሚገኙ የፀጥታ አካላትና አስተባባሪዎች ወይም በፖሊስ የመረጃ ስልኮች 0111110111 እና ነፃ የስልክ መስመር 991 ላይ በመደወልና መረጃ በመስጠት ይተባበሩ።
(ከአዘጋጆች)
መልካም የኢፍጣር ስነስርዓት !
#ሼር #Share
@tikvahethiopia
" አባታዊ የሰላም ጥሪ "
አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቀነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበር ተክለሃይማኖት ሰሞኑን በተለይ በጎንደርና አካባቢው ፤ በደቡብ ክልል በስልጤ ዞን አካባቢ በተፈጠረው አለመረጋጋት እና የሰው ህይወት መውደቅ እጅግ ማዘናቸውን ገልፀዋል።
አባታዊ የሰላም ጥሪም አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸውም ፦
" ከእልቂት የሚያተርፈው ፀላዔ ሠናያት የሆነው ዲያብሎስ ብቻ ነው።
እሳትን በእሳት ማጥፋት አይቻልምና ስንናገር ስንራመድ ፈሪሃ እግዚአብሔር እንዲኖረን በብርቱ እማፀናለሁ።
ይህም ጠብና እልቂት የሞራል ውድቀት ፣ የኃጢያት አውራ ተብሎ ከመመዝገብ ውጭ ስምና ታሪክ አይሆነንምና ሁላችንም ለሰላም እንድንቆም እለምናለሁ።
የእኛን ድጋፍ የሚፈልጉ በሰሜን ፣ በምስራቅ ፣ በምዕራብ ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ብዙ ወገኖች ሳሉ ሌላ ችግር በመጨመር አገርን ወደ አዘቅት መስደድ ፍፁም የተወገዘ ግብር ነው።
በሞቱት ወገኖች እጅግ አዝናለሁ።
አብያተ እምነትም የሰው ልጆች የምስጋና የነፍስ መማፀኛ ናቸው እንጂ የእሳት ግብር የሚሰጣቸው አይደሉምና ይህንን ድርጊት ተገቢ አለመሆኑን እገልፃለሁ።
እርስ በእርስ በመጣላት ላይ ሀገርም እያፈረስን ነው። ተጣልቶ ለመታረቅም ሀገር ያስፈልገናልና ሀገራችንን ልንሳሳላት ይገባናል።
ሁላችንም #ለሰላም_እንድንቆም ፤ መንግስትም ከሰው እና ከእግዚአብሔር የተቀበለውን አደራ ፈጥኖ እንዲያስፈፅም ፣ የሃይማኖት አባቶችም ትውልድን የማነጽ ተግባራቸውን በርትተው እንዲቀጥሉ አደራ ጭምር ጠይቃለሁ። " ብለዋል።
(ተጨማሪ ከላይ ያንብቡ)
@tikvahethiopia
አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቀነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበር ተክለሃይማኖት ሰሞኑን በተለይ በጎንደርና አካባቢው ፤ በደቡብ ክልል በስልጤ ዞን አካባቢ በተፈጠረው አለመረጋጋት እና የሰው ህይወት መውደቅ እጅግ ማዘናቸውን ገልፀዋል።
አባታዊ የሰላም ጥሪም አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸውም ፦
" ከእልቂት የሚያተርፈው ፀላዔ ሠናያት የሆነው ዲያብሎስ ብቻ ነው።
እሳትን በእሳት ማጥፋት አይቻልምና ስንናገር ስንራመድ ፈሪሃ እግዚአብሔር እንዲኖረን በብርቱ እማፀናለሁ።
ይህም ጠብና እልቂት የሞራል ውድቀት ፣ የኃጢያት አውራ ተብሎ ከመመዝገብ ውጭ ስምና ታሪክ አይሆነንምና ሁላችንም ለሰላም እንድንቆም እለምናለሁ።
የእኛን ድጋፍ የሚፈልጉ በሰሜን ፣ በምስራቅ ፣ በምዕራብ ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ብዙ ወገኖች ሳሉ ሌላ ችግር በመጨመር አገርን ወደ አዘቅት መስደድ ፍፁም የተወገዘ ግብር ነው።
በሞቱት ወገኖች እጅግ አዝናለሁ።
አብያተ እምነትም የሰው ልጆች የምስጋና የነፍስ መማፀኛ ናቸው እንጂ የእሳት ግብር የሚሰጣቸው አይደሉምና ይህንን ድርጊት ተገቢ አለመሆኑን እገልፃለሁ።
እርስ በእርስ በመጣላት ላይ ሀገርም እያፈረስን ነው። ተጣልቶ ለመታረቅም ሀገር ያስፈልገናልና ሀገራችንን ልንሳሳላት ይገባናል።
ሁላችንም #ለሰላም_እንድንቆም ፤ መንግስትም ከሰው እና ከእግዚአብሔር የተቀበለውን አደራ ፈጥኖ እንዲያስፈፅም ፣ የሃይማኖት አባቶችም ትውልድን የማነጽ ተግባራቸውን በርትተው እንዲቀጥሉ አደራ ጭምር ጠይቃለሁ። " ብለዋል።
(ተጨማሪ ከላይ ያንብቡ)
@tikvahethiopia
#AddisAbaba 🪪
" ላልተወሰነ ጊዜ አዲስ መታወቂያ መስጠት አቁመናል " - የአዲስ አበባ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ
የአዲስ አበባ ከተማ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ ላልተወሰነ ጊዜ " አዲስ መታወቂያ " የመስጠት አገልግሎት ማቆሙን አስታውቋል።
ኤጀንሲው የመታወቂያ ፣ የልደት ፣ የጋብቻና የሞት ማስረጃዎችን ይመዘግባል ፤ ዜጎች በሚፈልጉበት ወቅትም አገልግሎቱን ይሰጣል፡፡
በአገልግሎት አሰጣቱ ውስጥ በተለይ የመታወቂያ አገልግሎቱ ላይ በተቋሙ ውስጥ እና ከተቋሙ ውጭ ባሉ ሃሰተኛ ማስረጃን በሚያድሉ ግለሰቦች የተነሳ ለማይገባቸው ሰዎች መታወቂያ አላግባብ እየተሰጠ መሆኑን ኤጀንሲው ገልጿል።
ይህን ህገ ወጥ የሆነ ድርጊት ሲፈጽሙ የተያዙ ግለሰቦች ላይም እርምጃ መወሰዱን አሳውቋል።
የነዋሪነት መታወቂያ ለማግኘት ሲባል ህገወጥነት እየተባባሰ በመምጣቱ ችግሩን በሚገባ ለማጥራት እንዲቻል በከተማ አስተዳደሩ ደረጃ በተላለፈ ውሳኔ መሰረት አዲስ መታወቂያ እንዳይሰጥ ላልተወሰነ ጊዜ መታገዱን ኤጀንሲው ገልጿል።
የመታወቂያ እድሳትም ሆነ ሌሎች የወሳኝ ኩነት አገልግሎቶች ባሉበት ይቀጥላሉ ተብሏል፡፡
ምንጭ፦ አዲስ ቲቪ
@tikvahethiopia
" ላልተወሰነ ጊዜ አዲስ መታወቂያ መስጠት አቁመናል " - የአዲስ አበባ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ
የአዲስ አበባ ከተማ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ ላልተወሰነ ጊዜ " አዲስ መታወቂያ " የመስጠት አገልግሎት ማቆሙን አስታውቋል።
ኤጀንሲው የመታወቂያ ፣ የልደት ፣ የጋብቻና የሞት ማስረጃዎችን ይመዘግባል ፤ ዜጎች በሚፈልጉበት ወቅትም አገልግሎቱን ይሰጣል፡፡
በአገልግሎት አሰጣቱ ውስጥ በተለይ የመታወቂያ አገልግሎቱ ላይ በተቋሙ ውስጥ እና ከተቋሙ ውጭ ባሉ ሃሰተኛ ማስረጃን በሚያድሉ ግለሰቦች የተነሳ ለማይገባቸው ሰዎች መታወቂያ አላግባብ እየተሰጠ መሆኑን ኤጀንሲው ገልጿል።
ይህን ህገ ወጥ የሆነ ድርጊት ሲፈጽሙ የተያዙ ግለሰቦች ላይም እርምጃ መወሰዱን አሳውቋል።
የነዋሪነት መታወቂያ ለማግኘት ሲባል ህገወጥነት እየተባባሰ በመምጣቱ ችግሩን በሚገባ ለማጥራት እንዲቻል በከተማ አስተዳደሩ ደረጃ በተላለፈ ውሳኔ መሰረት አዲስ መታወቂያ እንዳይሰጥ ላልተወሰነ ጊዜ መታገዱን ኤጀንሲው ገልጿል።
የመታወቂያ እድሳትም ሆነ ሌሎች የወሳኝ ኩነት አገልግሎቶች ባሉበት ይቀጥላሉ ተብሏል፡፡
ምንጭ፦ አዲስ ቲቪ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#መልዕክት ከሰዓታት በኃላ 2ኛው " የታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር በኢትዮጵያ " መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ለታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር 2 ለመታደም ሲመጡ ፦ 👉 የራሳችሁን መስገጃ ይዛችሁ ኑ። 👉 አዘጋጆች የሚዘጋጁት ምግብ ቢኖርም ሁሉም የቻለውን ያህል ለሰዎች ጭምር የሚሆን ምግብ ይዞ ይምጣ። 👉 ሁሉም የተመገበበትን እቃ የሚያነሳበትን ፌስታል መያዝ እንዳይዘነጋ። 👉 በመሃል ሌባ ሊኖር…
ፎቶ ፦ ዛሬ ሁለተኛው " ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር " ስነስርዓት በአዲስ አበባ ተካሂዷል።
ስነስዓቱ ላይ ቁጥሩ እጅግ ከፍተኛ የሆነ ምእመን ተገኝቶ ነበር።
@tikvahethiopia
ስነስዓቱ ላይ ቁጥሩ እጅግ ከፍተኛ የሆነ ምእመን ተገኝቶ ነበር።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ ዛሬ ሁለተኛው " ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር " ስነስርዓት በአዲስ አበባ ተካሂዷል። ስነስዓቱ ላይ ቁጥሩ እጅግ ከፍተኛ የሆነ ምእመን ተገኝቶ ነበር። @tikvahethiopia
ሼህ ሱልጣን አማን ፦
" እስላም ሰላም ነው ፤ እስላም ሰላም ነው ፤ እስላም ሰላም ነው ፤ እስላም ስርዓት ነው።
እኛ ሙስሊሞች ነን ፤ ሰላም ፈላጊዎች ነን፤ ሀገራችን ሰላም ፣ ህዝባችን ሰላም ሁሉም ሰላም እንዲሆን እንፈልጋለን።
ሰላማችንን የሚያደፈርስ አካል በህግ እንቃወማለን፣ ማንም ከማንም አይበልጥም፤ ሁላችን እኩል ነን፤ ሙስሊሙም ክርስቲያኑም ለዚህች ሀገር ዜጋ ነው። ሁላችንም እኩል መብት አለን።
የተሰውት ወንድሞቻችን ፤ በጎንደር በደባርቅ አላህ ይማራቸው፤ ለጀነት አላህ ያርጋቸው፤ የታመሙትን አላህ ያሽራቸው።
እኛ ይሄን በወንድሞቻችን ላይ ያደረሰው አክራሪ ቡድን ላይ ከመንግስት ግልፅ የሆነ፣ ፍትሃዊ የሆነ እርምጃ እንዲወሰድልን እንጠይቃለን።
እኛ ለወንድሞቻችን፣ ተቃውሞ ወይም ድምፃችንን ስናሰማ በስርዓት መሆን አለበት። ሌላውን እንዳንጎዳ ዲናችን ያዘናል። ሌላውም በእነሱ ወንጀል መንካት የለብንም። እራሳችንን መጉዳት የለብንም፤ የሀገራችንን ሰላም መጠበቅ አለብን የኛ ግዴታ ነው።
ዛሬ በዚህ ባማረ መልኩ እንደጨረስን ሁሉ ለኢዳችን አላህ በሰላም እንዲያደርሰን እና በሰላም እንድንጨርስ ወንድሞቼ ፣ እህቶቼ አደራ እላችኃለሁ "
@tikvahethiopia
" እስላም ሰላም ነው ፤ እስላም ሰላም ነው ፤ እስላም ሰላም ነው ፤ እስላም ስርዓት ነው።
እኛ ሙስሊሞች ነን ፤ ሰላም ፈላጊዎች ነን፤ ሀገራችን ሰላም ፣ ህዝባችን ሰላም ሁሉም ሰላም እንዲሆን እንፈልጋለን።
ሰላማችንን የሚያደፈርስ አካል በህግ እንቃወማለን፣ ማንም ከማንም አይበልጥም፤ ሁላችን እኩል ነን፤ ሙስሊሙም ክርስቲያኑም ለዚህች ሀገር ዜጋ ነው። ሁላችንም እኩል መብት አለን።
የተሰውት ወንድሞቻችን ፤ በጎንደር በደባርቅ አላህ ይማራቸው፤ ለጀነት አላህ ያርጋቸው፤ የታመሙትን አላህ ያሽራቸው።
እኛ ይሄን በወንድሞቻችን ላይ ያደረሰው አክራሪ ቡድን ላይ ከመንግስት ግልፅ የሆነ፣ ፍትሃዊ የሆነ እርምጃ እንዲወሰድልን እንጠይቃለን።
እኛ ለወንድሞቻችን፣ ተቃውሞ ወይም ድምፃችንን ስናሰማ በስርዓት መሆን አለበት። ሌላውን እንዳንጎዳ ዲናችን ያዘናል። ሌላውም በእነሱ ወንጀል መንካት የለብንም። እራሳችንን መጉዳት የለብንም፤ የሀገራችንን ሰላም መጠበቅ አለብን የኛ ግዴታ ነው።
ዛሬ በዚህ ባማረ መልኩ እንደጨረስን ሁሉ ለኢዳችን አላህ በሰላም እንዲያደርሰን እና በሰላም እንድንጨርስ ወንድሞቼ ፣ እህቶቼ አደራ እላችኃለሁ "
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ኡስታዝ ከሚል ሸምሱ ፦
" ውድ ወንድሞች እና እህቶች እኛ እንደ ሙስሊሞች በቁርአን ፣ በሀዲስ ነው የምንመራው።
አላህ ሱብሀነ ወተአላ በራሳችን ፣ በስሜታችን ፣ በነብስያችን እንድንመራ አልፈቀደልንም። የመልካም ስራዎች ተምሳሌት ፤ የመልካም ተግባራት አርአያዎች እንጂ እኛ ከሌሎች ሰዎች መጥፎ ነገሮችን የምንኮርጅ ፤ መጥፎ ነገርን በመጥፎ የምንመልስ ሰዎች አይደለንም።
አላህ በቁርአን " ክፉ ነገርን በመልካም መልስ ያ ነው በአንተ እና በሌሎች መካከል ያለን ትስስር ፤ ግንኙነት የሚያስተካክለው " ስለሚለን በስሜት ውስጥ ሆነን የምንራመድ ህዝቦች አይደለንም።
ውድ ወንድሞች ፤ እህቶች እዚህ እንዳማረብን ቀጣዩ ኢዳችንን የተሳካ ኢድ እንዲሆን ፤ የታሳቡ ነገሮች ሁላ ከሽፎ ፤ ለሀገራችን ሰላም ፣ ለሀገራችን አንድነት ፣ የሀገሪቷ ባለቤቶች መሆናችንን በተግባር የምናሳይበት ኢዳችንን በጉጉት እየጠበቅን ባለንበት ሁሉ #ሰላምን መስበክ ፣ በሰላም መኖር ፀረ ሰላም የሆኑ ሰዎችን ደግሞ እነሱ በሚፈልጉት መስመር ውስጥ ሳንገባ መሄድ አለብን።
አላህ ኢዱን የሰላም ኢድ አድርግልን፤ ኢዱን የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የክብር እና የእኩልነት ኢድ ያድርግልን። "
@tikvahethiopia
" ውድ ወንድሞች እና እህቶች እኛ እንደ ሙስሊሞች በቁርአን ፣ በሀዲስ ነው የምንመራው።
አላህ ሱብሀነ ወተአላ በራሳችን ፣ በስሜታችን ፣ በነብስያችን እንድንመራ አልፈቀደልንም። የመልካም ስራዎች ተምሳሌት ፤ የመልካም ተግባራት አርአያዎች እንጂ እኛ ከሌሎች ሰዎች መጥፎ ነገሮችን የምንኮርጅ ፤ መጥፎ ነገርን በመጥፎ የምንመልስ ሰዎች አይደለንም።
አላህ በቁርአን " ክፉ ነገርን በመልካም መልስ ያ ነው በአንተ እና በሌሎች መካከል ያለን ትስስር ፤ ግንኙነት የሚያስተካክለው " ስለሚለን በስሜት ውስጥ ሆነን የምንራመድ ህዝቦች አይደለንም።
ውድ ወንድሞች ፤ እህቶች እዚህ እንዳማረብን ቀጣዩ ኢዳችንን የተሳካ ኢድ እንዲሆን ፤ የታሳቡ ነገሮች ሁላ ከሽፎ ፤ ለሀገራችን ሰላም ፣ ለሀገራችን አንድነት ፣ የሀገሪቷ ባለቤቶች መሆናችንን በተግባር የምናሳይበት ኢዳችንን በጉጉት እየጠበቅን ባለንበት ሁሉ #ሰላምን መስበክ ፣ በሰላም መኖር ፀረ ሰላም የሆኑ ሰዎችን ደግሞ እነሱ በሚፈልጉት መስመር ውስጥ ሳንገባ መሄድ አለብን።
አላህ ኢዱን የሰላም ኢድ አድርግልን፤ ኢዱን የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የክብር እና የእኩልነት ኢድ ያድርግልን። "
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ ዛሬ ሁለተኛው " ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር " ስነስርዓት በአዲስ አበባ ተካሂዷል። ስነስዓቱ ላይ ቁጥሩ እጅግ ከፍተኛ የሆነ ምእመን ተገኝቶ ነበር። @tikvahethiopia
ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ፦
" ... ሰሞኑን ልባችን ተሰብሯል፣ አንጋታችን ተደፍቷል፤ ውስጣችን አዝኗል። መሆን የማይገባቸው ነገሮች ሆነዋል።
እንደ ሀገር ፣ እንደ ማህበረሰብ ሁላችንም በመከባበር ፣ እውቅና በመሰጣጣት ፣ በመተሳሰብ ስንኖርባት ነው ይህች ሀገር ነገ የተሻለ ሆነ ለትውልድ የምታልፈው።
በየትኛውም ጊዜ ነውረኛ ተግባር የሚፈፅሙ አካላት ፣ምንም ይሁን ማንነታቸው ወንጀለኞች ናቸው በህግ እና ለስርዓት ሊዳኙ ይገባል።
መንግስት ይህን የማስከበር ስራ እየሰራ ስላለ አሁንም ከመንግስትና ከፀጥታ መዋቅሩ ጋር በመሆን በሰላም ጉዳዮቻችን መፍትሄ እንዲያገኙ ፣ ያዘንባቸው እንዲታከሙ ሁላችንም በሰላም የምንታወቅበት ባህሪ አለን ያን መስመር ይዘን እንድንሄድ ነው አደራ የምንለው።
ከዛ ባለፈ እንደ ሀገር አሁንም የምንቀጥለው ጥፋት የሚያጠፋ አካል ሲያጠፋ ጥፋትን በመድገም አይደለም ውጤት የሚመጣው ፤ ነውርን በነውር አናክመውም ፤ ጥፋትን በጥፋት አናድነውም።
እስልምናችን እንደሚያዘን የራሳችን የሆነ መለያ ማንነት አለን ያንን መሰረት ተከትለን ነው የምንሄደው።
...በዛሬው ኢፍጣር ፕሮግራም መድረክ ከተለያዩ ቤተ እምነቶች የተወከሉ የሃይማኖት አባቶች ፣ ፓስተሮች ፣ ቀሳውስቶች ጥሬያችንን አክብረው ከጎናችን ቆመዋል እኛ የሚያምርብን እንደ ኡትዮጵያዊነት የሚገልፀን ይሄ ነው።
ተከባብረን ፣ እውቅና ተሰጣጥተን ስንኖር ፤ ይሄንን እናስቀጥላለን ፤ ጥፋቱን እንቃወማለን ፣ እጅ ለእጅ ተያይዘን በሰላም ፣ በአንድነት ሀገራችንን እናስቀጥላለን "
@tikvahethiopia
" ... ሰሞኑን ልባችን ተሰብሯል፣ አንጋታችን ተደፍቷል፤ ውስጣችን አዝኗል። መሆን የማይገባቸው ነገሮች ሆነዋል።
እንደ ሀገር ፣ እንደ ማህበረሰብ ሁላችንም በመከባበር ፣ እውቅና በመሰጣጣት ፣ በመተሳሰብ ስንኖርባት ነው ይህች ሀገር ነገ የተሻለ ሆነ ለትውልድ የምታልፈው።
በየትኛውም ጊዜ ነውረኛ ተግባር የሚፈፅሙ አካላት ፣ምንም ይሁን ማንነታቸው ወንጀለኞች ናቸው በህግ እና ለስርዓት ሊዳኙ ይገባል።
መንግስት ይህን የማስከበር ስራ እየሰራ ስላለ አሁንም ከመንግስትና ከፀጥታ መዋቅሩ ጋር በመሆን በሰላም ጉዳዮቻችን መፍትሄ እንዲያገኙ ፣ ያዘንባቸው እንዲታከሙ ሁላችንም በሰላም የምንታወቅበት ባህሪ አለን ያን መስመር ይዘን እንድንሄድ ነው አደራ የምንለው።
ከዛ ባለፈ እንደ ሀገር አሁንም የምንቀጥለው ጥፋት የሚያጠፋ አካል ሲያጠፋ ጥፋትን በመድገም አይደለም ውጤት የሚመጣው ፤ ነውርን በነውር አናክመውም ፤ ጥፋትን በጥፋት አናድነውም።
እስልምናችን እንደሚያዘን የራሳችን የሆነ መለያ ማንነት አለን ያንን መሰረት ተከትለን ነው የምንሄደው።
...በዛሬው ኢፍጣር ፕሮግራም መድረክ ከተለያዩ ቤተ እምነቶች የተወከሉ የሃይማኖት አባቶች ፣ ፓስተሮች ፣ ቀሳውስቶች ጥሬያችንን አክብረው ከጎናችን ቆመዋል እኛ የሚያምርብን እንደ ኡትዮጵያዊነት የሚገልፀን ይሄ ነው።
ተከባብረን ፣ እውቅና ተሰጣጥተን ስንኖር ፤ ይሄንን እናስቀጥላለን ፤ ጥፋቱን እንቃወማለን ፣ እጅ ለእጅ ተያይዘን በሰላም ፣ በአንድነት ሀገራችንን እናስቀጥላለን "
@tikvahethiopia