TIKVAH-ETHIOPIA
የአውሮፓ ህብረት ባለስልጣኗ ኢትዮጵያ ይመጣሉ። የአውሮፓ ህብረት የዓለም አቀፍ አጋርነት ኮሚሽነር ጁታ ኡርፒላይነን ወደ ኢትዮጵያ፣ ሩዋንዳ እና ሱዳን ይጓዛሉ። ኮሚሽነር ጁታ በሶስቱ ሀገራት ቆይታ የሚያደርጉት ከጥምቅት 14 እስከ ጥቅምት 17 ድረስ ነው። ጉዟቸው የአውሮፓ ህብረት በአፍሪካ ቀንድ #ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት እንዲሁም ከአፍሪካ ጋር ያለውን ጠንካራ ግንኙነት ለመግለፅ እና ለማጠናከር ነው…
#Update
ከቀናት በፊት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ የተገለፀው የአውሮፓ ህብረት የዓለም አቀፍ አጋርነት ኮሚሽነር ጁታ ኡርፒላይነን ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ተወያዩ።
ጁታ ኡርፒላይን ትላንት ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ፣ ከፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ እና ከምክትል ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጋር መነጋገራቸውን አሳውቀዋል።
ባለስልጣኗ ባይፋዊ የትዊተር ገፃቸው ባወጡት ፅሁፍ ፥ " በሀገሪቱ የፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳዎች፣ በሰሜን ኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው ግጭትና ስለሰብዓዊ ቀውስ ጉዳይ ገንቢ ውይይት አድርገናል" ብለዋል።
ኡርፒላይን ፥ ከላይ የተገለፁትን ተግዳሮቶች ለመፍታት ከኢትዮጵያውያን አጋሮቻችን ጋር አብሮ መስራታችንን ለመቀጠል ቁርጠኛ ነኝ ሲሉም ፅፈዋል።
በቅርቡ ዳግም ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱም አሳውቀዋል።
እንደ አውሮፓ ህብረት መረጃ ባለስልጣኗ በቀጣይ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የሚኒስትሮች ስብሰባን ለመካፍል ኪጋሊ እንደሚገቡ ይጠበቃል።
ቀደም ብሎ በወጣው መርሃ ግብር በመጨረሻ የስራ ቆይራቸው ሱዳን ካርቱም እንደሚገቡ የታቀደ ቢሆን በሱደን አሁን ካለው ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ ጋር በተያያዘ እና በተደረገው መፈንቅለ መንግስት ምክንያት ወደ ሱዳን ያቀናሉ የሚለው አልታወቀም።
ባለስልጣኗ ወደ ሱዳን ሄደው የሽግግሩን አመራሮች ሊያገኙ መርሀ ግብር ተይዞላቸው የነበረ ሲሆን የአውሮፓ ህብረት እና ሱዳን የፖለቲካ ውይይትን ያስጀምራሉ ተብሎም ነበር።
@tikvahethiopia
ከቀናት በፊት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ የተገለፀው የአውሮፓ ህብረት የዓለም አቀፍ አጋርነት ኮሚሽነር ጁታ ኡርፒላይነን ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ተወያዩ።
ጁታ ኡርፒላይን ትላንት ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ፣ ከፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ እና ከምክትል ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጋር መነጋገራቸውን አሳውቀዋል።
ባለስልጣኗ ባይፋዊ የትዊተር ገፃቸው ባወጡት ፅሁፍ ፥ " በሀገሪቱ የፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳዎች፣ በሰሜን ኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው ግጭትና ስለሰብዓዊ ቀውስ ጉዳይ ገንቢ ውይይት አድርገናል" ብለዋል።
ኡርፒላይን ፥ ከላይ የተገለፁትን ተግዳሮቶች ለመፍታት ከኢትዮጵያውያን አጋሮቻችን ጋር አብሮ መስራታችንን ለመቀጠል ቁርጠኛ ነኝ ሲሉም ፅፈዋል።
በቅርቡ ዳግም ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱም አሳውቀዋል።
እንደ አውሮፓ ህብረት መረጃ ባለስልጣኗ በቀጣይ የአፍሪካ ህብረት እና የአውሮፓ ህብረት የሚኒስትሮች ስብሰባን ለመካፍል ኪጋሊ እንደሚገቡ ይጠበቃል።
ቀደም ብሎ በወጣው መርሃ ግብር በመጨረሻ የስራ ቆይራቸው ሱዳን ካርቱም እንደሚገቡ የታቀደ ቢሆን በሱደን አሁን ካለው ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ ጋር በተያያዘ እና በተደረገው መፈንቅለ መንግስት ምክንያት ወደ ሱዳን ያቀናሉ የሚለው አልታወቀም።
ባለስልጣኗ ወደ ሱዳን ሄደው የሽግግሩን አመራሮች ሊያገኙ መርሀ ግብር ተይዞላቸው የነበረ ሲሆን የአውሮፓ ህብረት እና ሱዳን የፖለቲካ ውይይትን ያስጀምራሉ ተብሎም ነበር።
@tikvahethiopia
#HappeningNow : 9ኛ ዙር የአማራ ልዩ ሀይል ፓሊስ የምረቃ ስነ ስርዓት በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በአሁን ሰዓት በደብረማርቆስ ከተማ የአማራ ክልል ፓሊስ ኮሌጅ የ9ኛ ዙር የአማራ ልዩ ሀይል ምልምል ፓሊስ ሰልጣኞችን እያስመረቀ ነው።
@tikvahethiopia
በአሁን ሰዓት በደብረማርቆስ ከተማ የአማራ ክልል ፓሊስ ኮሌጅ የ9ኛ ዙር የአማራ ልዩ ሀይል ምልምል ፓሊስ ሰልጣኞችን እያስመረቀ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በሱዳን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታወጀ። የሱዳን ጦር አዛዥ ሌተናንት ጀነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሀን መግለጫ ሰጥተዋል። በሀገሪቱ የአስቸኳ ጊዜ አዋጄ መታወጁን አስታውቀዋል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለምን ያህል ጊዜ እንደሆነ ጀነራል አልቡርሀን አልተናገሩም። ሌተናንት ጀነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሀን በመግለጫቸው የሉአላዊ ምክር ቤት እና ሚኒስትሮች ምክር ቤት መፍረሱን ፤ የክልሎች አሰተዳዳሪዎች እና ሌሎች…
#SUDAN : የሱዳን መዲና ካርቱም ትላንት ለሊቱን በአብዛኛው ፀጥ ብላ አሳልፋለች።
የሱዳን ጦር መፈንቅለ መንግስት ማድረግን ተከትሎ የተቋረጠው የኢንተርኔት ፣ የስልክ ግንኙነት አሁንም አልተመለሰም።
የሱዳን ጦር ያደረገውን መፈንቅለ መንግስት ለመቃወም አደባባይ በወጡ እና በጦሩ መካከል በተፈጠረ ግጭት 7 ሰዎች መገደላቸውን እና ከ140 በላይ መቁሰላቸውን የሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
በካርቱም በአሁን ሰዓት ሱቆች፣ የንግድ ተቋማት ፣ አገልግሎት ሰጪዎች እንደተዘጉ ሲሆን የተወሰኑ መንገዶች አሁንም በሱዳን ጦር እንደተዘጉ ናቸው።
ትላንት ሌተናንት ጀነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሀን በሰጡት መግለጫ የሉአላዊ ምክር ቤት እና ሚኒስትሮች ምክር ቤት መፍረሱን ፤ የክልሎች አሰተዳዳሪዎች እና ሌሎች አመራሮች ከስልጣን መነሳታቸውን፤ በሀገሪቱም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁን ማስታወቃቸው አይዘነጋም።
ቡርሃን እ.ኤ.አ.በጁላይ 2023 ምርጫ ለማካሄድ እና ለተመረጠ የሲቪል መንግስት ስልጣን እንደሚያስረክቡ ቃል ገብተዋል።
አሁንም ድረስ በእስር ላይ ለሚገኙት ጠ/ ሚ አብደላ ሀምዶክ ታማኝ የሆነው የሱዳን የማስታወቂያ ሚኒስቴር በይፋዊ ፌስቡክ ገጹ ፥ የሽግግር ህገ መንግስቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የማወጅ መብት የሰጠው ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ብቻ ነው ፤ የወታደሩ እርምጃ ወንጀል ነው " ብሎታል።
ሚኒስቴሩ አብደላ ሃምዶክ አሁንም ህጋዊ የሽግግሩ ባለስልጣን ናቸው ሲልም አክሏል።
መረጃው የአልአረቢያ ነው።
@tikvahethiopia
የሱዳን ጦር መፈንቅለ መንግስት ማድረግን ተከትሎ የተቋረጠው የኢንተርኔት ፣ የስልክ ግንኙነት አሁንም አልተመለሰም።
የሱዳን ጦር ያደረገውን መፈንቅለ መንግስት ለመቃወም አደባባይ በወጡ እና በጦሩ መካከል በተፈጠረ ግጭት 7 ሰዎች መገደላቸውን እና ከ140 በላይ መቁሰላቸውን የሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
በካርቱም በአሁን ሰዓት ሱቆች፣ የንግድ ተቋማት ፣ አገልግሎት ሰጪዎች እንደተዘጉ ሲሆን የተወሰኑ መንገዶች አሁንም በሱዳን ጦር እንደተዘጉ ናቸው።
ትላንት ሌተናንት ጀነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሀን በሰጡት መግለጫ የሉአላዊ ምክር ቤት እና ሚኒስትሮች ምክር ቤት መፍረሱን ፤ የክልሎች አሰተዳዳሪዎች እና ሌሎች አመራሮች ከስልጣን መነሳታቸውን፤ በሀገሪቱም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁን ማስታወቃቸው አይዘነጋም።
ቡርሃን እ.ኤ.አ.በጁላይ 2023 ምርጫ ለማካሄድ እና ለተመረጠ የሲቪል መንግስት ስልጣን እንደሚያስረክቡ ቃል ገብተዋል።
አሁንም ድረስ በእስር ላይ ለሚገኙት ጠ/ ሚ አብደላ ሀምዶክ ታማኝ የሆነው የሱዳን የማስታወቂያ ሚኒስቴር በይፋዊ ፌስቡክ ገጹ ፥ የሽግግር ህገ መንግስቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የማወጅ መብት የሰጠው ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ብቻ ነው ፤ የወታደሩ እርምጃ ወንጀል ነው " ብሎታል።
ሚኒስቴሩ አብደላ ሃምዶክ አሁንም ህጋዊ የሽግግሩ ባለስልጣን ናቸው ሲልም አክሏል።
መረጃው የአልአረቢያ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ተጨማሪ የመንግስት የኮሚኒኬሽን አገልግሎት ፥ ዛሬ ጥቅምት 14 ቀን 2014 ዓም፣ ዐድዋ አካባቢ የሚገኝ የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር /TPLF/ ወታደራዊ ትጥቅ እና ወታደራዊ አልባሳትን አመሳስሎ የሚያመርትበት ማዕከል በአየር ድብደባ ከጥቅም ውጭ ሆኗል ሲል አሳውቋል። ከዚሁ ከአየር ጥቃት ጋር በተያያዘ በሽብርተኛ ድርጅትነት የተፈረጀው የትግራይ ነፃ አውጪ ቃል አቃባይ አቶ ጌታቸው ረዳ የጥቃቱን መፈፀሙን…
#EthiopianAirForce
የኢትዮጵያ አየር ኃይል በትግራይ ክልል የሚወስደውን የአየር ጥቃት የቀጠለ ሲሆን በዛሬው ዕለት መቐለ ኵሃ አካባቢ የአየር ጥቃት ፈፅሟል።
የኢትዮጵያ መንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት በይፋዊ ማህበራዊ ትስስር ገፁ እንዳሳወቀው ፥ ዛሬ መቐለ ኲሃ አካባቢ የተፈፀመው የአየር ድብደባ ኢላማው የልዩ ኃይል ፖሊስ ማሠልጠኛ ተቋም ነው።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ፥ በአየር የተመታው ተቋም በአሁኑ ወቅት በርካታ በአሸባሪነት የተፈረጀው የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር (TPLF) ቡድን ታጣቂዎች እየሰለጠኑበት ያለ ተቋም መሆኑን አመልክቷል።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት በአዲሱ የኢትዮጵያ መንግስት የተቋቋመና በተለይም በአሁን ወቅት ወቃታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለውጭ እና ለሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን መረጃዎችን እንዲሁም ለሚነሱ ጥያቄዎችም ምላሽ እየሰጠ የሚገኝ ተቋም ነው።
ፎቶ : ፋይል
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር ኃይል በትግራይ ክልል የሚወስደውን የአየር ጥቃት የቀጠለ ሲሆን በዛሬው ዕለት መቐለ ኵሃ አካባቢ የአየር ጥቃት ፈፅሟል።
የኢትዮጵያ መንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት በይፋዊ ማህበራዊ ትስስር ገፁ እንዳሳወቀው ፥ ዛሬ መቐለ ኲሃ አካባቢ የተፈፀመው የአየር ድብደባ ኢላማው የልዩ ኃይል ፖሊስ ማሠልጠኛ ተቋም ነው።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ፥ በአየር የተመታው ተቋም በአሁኑ ወቅት በርካታ በአሸባሪነት የተፈረጀው የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር (TPLF) ቡድን ታጣቂዎች እየሰለጠኑበት ያለ ተቋም መሆኑን አመልክቷል።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት በአዲሱ የኢትዮጵያ መንግስት የተቋቋመና በተለይም በአሁን ወቅት ወቃታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለውጭ እና ለሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን መረጃዎችን እንዲሁም ለሚነሱ ጥያቄዎችም ምላሽ እየሰጠ የሚገኝ ተቋም ነው።
ፎቶ : ፋይል
@tikvahethiopia
ባድመ እና የአሜሪካ አቋም ?
በኤርትራ፣ አስመራ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ዛሬ በይፋዊ ማህበራዊ ትስስር ገፁ ባድመን በሚመለከት አንድ አጭር ፅሁፍ አሰራጭቷል።
" ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ ብዙዎቻችሁ በባድመ ላይ የአሜሪካ ፖሊሲ ምን እንደሆነ ጠይቃችሁ ነበር " ያለው ኤምባሲው በባድመ ጉዳይ የአሜሪካንን አቋም አሳውቋል።
እኤአ በ2002 የኤርትራ - ኢትዮጵያ የድንበር ኮሚሽን ባድመ እና ተጓዳኝ አወዛጋቢ አካባቢዎችን ለኤርትራ ሰጥቷል የሚለው የአሜሪካ ኤምባሲ ፥ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ እኤአ በ2018 የሰላም ስምምነት ወቅት የኤርትራ እና ኢትዮጵያ የድንበር ኮሚሽን ውሳኔንን ተግባራዊ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆናቸው ገልፀዋል ብሏል።
አሜሪካ ፥ ሁለቱ ሀገራት ይህን ለማድረግ ሁሉንም አስፈላጊ ቀሪ እርምጃዎች እንዲወስዱ ታሳስባለች ብሏል በአስመራ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ።
@tikvahethiopia
በኤርትራ፣ አስመራ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ዛሬ በይፋዊ ማህበራዊ ትስስር ገፁ ባድመን በሚመለከት አንድ አጭር ፅሁፍ አሰራጭቷል።
" ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ ብዙዎቻችሁ በባድመ ላይ የአሜሪካ ፖሊሲ ምን እንደሆነ ጠይቃችሁ ነበር " ያለው ኤምባሲው በባድመ ጉዳይ የአሜሪካንን አቋም አሳውቋል።
እኤአ በ2002 የኤርትራ - ኢትዮጵያ የድንበር ኮሚሽን ባድመ እና ተጓዳኝ አወዛጋቢ አካባቢዎችን ለኤርትራ ሰጥቷል የሚለው የአሜሪካ ኤምባሲ ፥ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ እኤአ በ2018 የሰላም ስምምነት ወቅት የኤርትራ እና ኢትዮጵያ የድንበር ኮሚሽን ውሳኔንን ተግባራዊ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆናቸው ገልፀዋል ብሏል።
አሜሪካ ፥ ሁለቱ ሀገራት ይህን ለማድረግ ሁሉንም አስፈላጊ ቀሪ እርምጃዎች እንዲወስዱ ታሳስባለች ብሏል በአስመራ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር (ኢመማ) ለሁለት ኢትዮጵያውያን እውቅና ሰጠ። የኢትዮጵያ መምህርን ማህበር በ22ኛ ጠቅላላ ግባኤው ላይ ለቀድሞው ጠ/ሚ አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ እና ለጋዜጠኛና መምህር ዮናስ ከበደ እውቅና ሰጥቷል ፤ ጋዜጠኛ እና መምህር ዮናስን የክብር አባሳደርም ሆነዋል። እውቅናው የተሰጣቸው የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስተር አቶ ሀይለማሪያም ደስላኝ በሀገር አቀፍ ደረጃ መምህራን…
#Update
የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ለቀጣይ አራት ዓመት ፕሬዘዳንት አድርጎ ዶክተር ዮሐንስ ባንቲን መረጠ።
ዶ/ር ዮሐንስ ባንቲ ማህበሩን ላለፉት አምስት ዓመት መርተዋል።
በዛሬው እለት በኦሮሚያ ክልል መምህራን ማህበር አቀርቢነት የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ የማህበሩ ፕሬዘዳንት አድርጎ ለዶ/ር ዮሐንስ ባንቲ ሹመት ሰጥቷል።
ማህበሩ 22ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ፕሬዘዳንቱን እና የስራ አስፈፃሚወችን በመምረጥና ለሀገር ሰላም ሁሉም አካላት እንዲሰሩ በማሳሰብ የአቋም መግለጫ በማወጣት 22ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አጠናቋል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ትምህርት ቴሌቪዥን /ጋዜጠኛ ነፃነት ጌታቸው
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ለቀጣይ አራት ዓመት ፕሬዘዳንት አድርጎ ዶክተር ዮሐንስ ባንቲን መረጠ።
ዶ/ር ዮሐንስ ባንቲ ማህበሩን ላለፉት አምስት ዓመት መርተዋል።
በዛሬው እለት በኦሮሚያ ክልል መምህራን ማህበር አቀርቢነት የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ የማህበሩ ፕሬዘዳንት አድርጎ ለዶ/ር ዮሐንስ ባንቲ ሹመት ሰጥቷል።
ማህበሩ 22ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ፕሬዘዳንቱን እና የስራ አስፈፃሚወችን በመምረጥና ለሀገር ሰላም ሁሉም አካላት እንዲሰሩ በማሳሰብ የአቋም መግለጫ በማወጣት 22ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አጠናቋል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ትምህርት ቴሌቪዥን /ጋዜጠኛ ነፃነት ጌታቸው
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#SUDAN : የሱዳን መዲና ካርቱም ትላንት ለሊቱን በአብዛኛው ፀጥ ብላ አሳልፋለች። የሱዳን ጦር መፈንቅለ መንግስት ማድረግን ተከትሎ የተቋረጠው የኢንተርኔት ፣ የስልክ ግንኙነት አሁንም አልተመለሰም። የሱዳን ጦር ያደረገውን መፈንቅለ መንግስት ለመቃወም አደባባይ በወጡ እና በጦሩ መካከል በተፈጠረ ግጭት 7 ሰዎች መገደላቸውን እና ከ140 በላይ መቁሰላቸውን የሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። በካርቱም…
#SUDAN : " ጠ/ሚ አብደላ ሀምዶክ እኔ ቤት ነው ያለው " - ሌ/ጀነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሀን
የሱዳን ጦር አዛዥ ሌተናንት ጀነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሀን ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።
ሌተናንት ጀነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሀን በመግለጫቸው በሱዳን ጦር በቁጥጥር ስር የዋሉት ጠቅላይ ሚኒስትር በአብደላ ሀምዶክ ያሉበትን አስታውቀዋል።
አልቡርሃን ፥ “ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ እኔ ቤት ነው ያለው” ያሉ ሲሆን “ይህ የሆነው ለደህንነታቸው ሲባል ነው” ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክን ወደ ቤታቸው የወሰዷቸው የደህንነት ስጋት ስለነበረ እንደሆነ ያስታወቁት አልቡርሃን፤ “በየቀኑ እተገናኝ እየነጋገርን ነው” ሲሉ አስታውቀዋል።
"ለጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ ክብር አለን" ያሉት አልቡርሃን፤ ደህንነታቸውን ለማስጠበቅ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላህ ሀምዶክ የፖለቲካ ገደብ ስለተጣለባቸው ስራቸውን በነጻነት መስራት እንደማይችሉ አስታውቀዋል።
አልቡርሀን በመግለጫቸው በወንጀል የሚፈለጉ ሰዎች በእስር ቤት እንደሚቆዩ ገልጸው፤ ሌሎቹ ግን ከእስር እንደሚለቀቁ አስታውቀዋል።
በትናትናው እለት የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ነገሮች ሲረጋጉ ይነሳል ሲሉም አስታውቀዋል።
Credit : አል ዐይን ኒውስ
@tikvahethiopia
የሱዳን ጦር አዛዥ ሌተናንት ጀነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሀን ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።
ሌተናንት ጀነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሀን በመግለጫቸው በሱዳን ጦር በቁጥጥር ስር የዋሉት ጠቅላይ ሚኒስትር በአብደላ ሀምዶክ ያሉበትን አስታውቀዋል።
አልቡርሃን ፥ “ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ እኔ ቤት ነው ያለው” ያሉ ሲሆን “ይህ የሆነው ለደህንነታቸው ሲባል ነው” ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክን ወደ ቤታቸው የወሰዷቸው የደህንነት ስጋት ስለነበረ እንደሆነ ያስታወቁት አልቡርሃን፤ “በየቀኑ እተገናኝ እየነጋገርን ነው” ሲሉ አስታውቀዋል።
"ለጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ ክብር አለን" ያሉት አልቡርሃን፤ ደህንነታቸውን ለማስጠበቅ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላህ ሀምዶክ የፖለቲካ ገደብ ስለተጣለባቸው ስራቸውን በነጻነት መስራት እንደማይችሉ አስታውቀዋል።
አልቡርሀን በመግለጫቸው በወንጀል የሚፈለጉ ሰዎች በእስር ቤት እንደሚቆዩ ገልጸው፤ ሌሎቹ ግን ከእስር እንደሚለቀቁ አስታውቀዋል።
በትናትናው እለት የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ነገሮች ሲረጋጉ ይነሳል ሲሉም አስታውቀዋል።
Credit : አል ዐይን ኒውስ
@tikvahethiopia
#AddisAbaba : ዛሬ አዲስ አበባ " ቄራ በረት " አካባቢ ከቀኑ 8:00 ገደማ አካባቢ በተከሰተ የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን የን/ስ/ላ/ክ/ከ አሳውቋል።
የን/ስ/ላ/ክ/ከ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ነፃነት ዳባ በስፍራው ተገኝተው በአደጋው የደረሰውን ጉዳት ተመልክተዋል።
የን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ይፋ ባደረገው መረጃ የአደጋው መንስኤ አልተገለፀም።
በእሳት አደጋው የወደመው አጠቃላይ ንብረት መጠን አልታወቀም።
Video Credit : Elias Workneh (Tikvah-Family)
@tikvahethiopia
የን/ስ/ላ/ክ/ከ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ነፃነት ዳባ በስፍራው ተገኝተው በአደጋው የደረሰውን ጉዳት ተመልክተዋል።
የን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ይፋ ባደረገው መረጃ የአደጋው መንስኤ አልተገለፀም።
በእሳት አደጋው የወደመው አጠቃላይ ንብረት መጠን አልታወቀም።
Video Credit : Elias Workneh (Tikvah-Family)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዶ/ር ዐቢይ ጠ/ሚ ሆነው ተሾሙ። ዶክተር ዐቢይ አህመድ አሊ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል። @tikvahethiopia
#RecepTayyipErdoğan
የቱርኩ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ጠ/ሚ ዶክተር አብይ አህመድ የደስታ መግለጫ ላኩ።
ዶክተር ዐቢይ አህመድ መስከረም 24 ቀን 2014 ዓ/ም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሀገሪቱን በጠቅላይ ሚኒስትርነት እንዲመሩ መሾማቸው ይታወሳል።
ሹመቱን ተከትሎ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች የ "እንኳን ደስ አልዎት!" መግለጫ ሲልኩ እንደነበር አይዘነጋም።
ዛሬ ጥቅምት 16/2014 ዓ/ም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መረጃ ፤ የቱርኩ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዴጋን ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ሆነው በመሾማቸው የደስታ መግለጫ ልከዋል።
ፕሬዚዳንት ኤርዶጋን በቀጣይ ከጠ/ሚ ዶክተር አብይ አህመድ ጋር በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር እና የህዝቦችን የጋራ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንደሚሰሩ ገልፀዋል።
ከዚህ በፊት ቱርክ 🇹🇷 እና ኢትዮጵያ 🇪🇹 መካከላቸው ያለውን ዘርፈ ብዙ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚያችሉ ስምምነቶችን መፈራረማቸው ይታወሳል።
@tikvahethiopia
የቱርኩ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ጠ/ሚ ዶክተር አብይ አህመድ የደስታ መግለጫ ላኩ።
ዶክተር ዐቢይ አህመድ መስከረም 24 ቀን 2014 ዓ/ም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሀገሪቱን በጠቅላይ ሚኒስትርነት እንዲመሩ መሾማቸው ይታወሳል።
ሹመቱን ተከትሎ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች የ "እንኳን ደስ አልዎት!" መግለጫ ሲልኩ እንደነበር አይዘነጋም።
ዛሬ ጥቅምት 16/2014 ዓ/ም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መረጃ ፤ የቱርኩ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዴጋን ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ሆነው በመሾማቸው የደስታ መግለጫ ልከዋል።
ፕሬዚዳንት ኤርዶጋን በቀጣይ ከጠ/ሚ ዶክተር አብይ አህመድ ጋር በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር እና የህዝቦችን የጋራ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንደሚሰሩ ገልፀዋል።
ከዚህ በፊት ቱርክ 🇹🇷 እና ኢትዮጵያ 🇪🇹 መካከላቸው ያለውን ዘርፈ ብዙ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚያችሉ ስምምነቶችን መፈራረማቸው ይታወሳል።
@tikvahethiopia