TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የአሜሪካን ተራድዖ ኢትዮጵያ ዳይሬክተር (#USAID) Mr. Sean Jones ደም ለግሠዋል። #ETHIOPIA #OCT22

እርሶስ?
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Conflict Sensitive Reporting (Amharic Handbook).pdf
3.4 MB
ግጭት አገናዛቢ ዘገባ - የጋዜጠኞች ማጣቀሻ

'ግጭት አገናዛቢ ዘገባ፤ የጋዜጠኞች ማጣቀሻ' ወደ አማርኛ የተተረጎመው በአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (USAID) ድጋፍ በኢንተርኒውስ ኔትዎርክ (Internews Network) ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ነው።

#USAID #Internews
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
 
#USAID #OCHA

በትግራይ የሰብዓዊ ረድዔት ሠራተኞች ችግር ላይ ያሉ ማህበረሰቦችን ለመድረስ በሚያደርጉት እንቅስቃሴዎች ላይ የሚገጥማቸው መሰናክል ተባብሷል ሲል የተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች ቢሮ (OCHA) አሳስቧል።

አጣዳፊ የምግብ እርዳታ ከሚያስፈልገው 5.2 ሚሊዮን ህዝብ ውስጥ ከመጋቢት ወር መጨረሻ ወዲህ ለመድረስ የተቻለው 1.8 ሚሊዮኑን ብቻ ነው ብሏል።

በክልሉ አሁን ካለው የከፋ የተመጣጠነ ምግብ ዕጥረት እንዳይከሰት አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ያስታወቀው ኦቻ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ሁሉ እስከዚህ የአውሮፓ 2021 ማብቂያ ድረስ በቂ እርዳታ ለማቅረብ 853 ሚሊዮን ዶላር እስከፊታችን ሃምሌ መጨረሻ ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ያስፈልጋል ብሏል።

በሌላ መረጃ ፦ የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ልማት ተራድዖ ድርጅት ወይም USAID/ አስተዳዳሪ ሳማንታ ፓወር የትግራይ ግጭት እጅግ የከበደ ረሃብ እያስከተለ እንደሆነ እና ከ5 ሚሊዮን የሚበልጥ ህዝብ እርዳታ የሚያስፈልገው መሆኑን አሳስበዋል።

ሳምንታ ፓዎር "የቅድመ ማስጠንቀቂያ ቅኝታችን አጣዳፊ የምግብ ችግር መኖሩን ይጠቁማል" ያሉ ሲሆን ችግሩ እጅግ አስከፊው ደረጃ ላይ ደርሷል ብለዋል።

የኢትዮጲያ መንግሥት ግጭቱን ለማቆም እንዲሁም የሰብዓዊ ረድዔት ሠራተኞች የተቸገረውን ህዝብ ለመድረስ እንዲችሉ አሁኑኑ እርምጃ መውሰድ አለበት ሲሉ ገልፀዋል። #VOA

@tikvahethiopia
#USAID

የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት (USAID) በትግራይ ክልል ለአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ የሚውል የ181 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ይፋ ማድረጉን የUSAID ሃላፊ ሳማንታ ፓወር አሳውቀዋል።

ድጋፉ ፦

- አስቸኳይ ጊዜ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው 3 ሚሊየን ዜጎች ይውላል።

- የምግብ፣ የንጹህ መጠጥ፣ መጠለያ፣ የጤና አገልግሎትን ጨምሮ መሰረታዊ አገልግቶችን ለማቅረብ ያስችላል።

- ለአርሶ አደሮች ዘርና ማዳበሪያን ጨምሮ የግብርና ግብአትን ለማቅረብ ይውላል።

- ለማህበራዊና ስነ ልቦናዊ ጫና ማገገሚያ ፕሮግራም ይውላል።

ከዚህ ባለፈ ትላትን የUSAID ኃላፊዋ ሳምንታ ፓወር የኢትዮጵያ መንግሥት ትግራይ ውስጥ ለሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት መሰናክል እየሆነ እንዳለ ትዊተር ገጻቸው ገልጠዋል።

ትግራይ ውስጥ 5.2 ሚሊዮን ዜጎች ምግብ ዕርዳታ እንደሚፈልጉና ሁኔታው ከቀውስ ደረጃ ማለፉን ገልፀዋል፡፡

ዛሬ የአሜሪካ USAID እና የአውሮፓ ኅብረት (EU) የሰብዓዊ እና ልማት ዕርዳታ ሃላፊዎች በክልል ሰብዓዊ ሁኔታ ላይ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው።

የUSAID ኃላፊዋ የኢትዮጵያ መንግሥት ዕርዳታን እንዳያሰናክልና ግጭት እንዲያቆም ጫና እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት ለዚህ የሳማንታ ፓወር ገለፃ በቀጥታ እስካሁን የሰጠው ምላሽ ባይኖርም ትላንት በጠ/ሚ ፅ/ቤት በተሰጠው መግለጫ በትግራይ እየተደረገ ስላለው የሰብዓዊ ድጋፍ ስራ በስፋት ተብራርቷል።

መንግስት ድጋፍ እያደረጉ ላሉ አካላት ከፍተኛ እገዛ እና የእርዳታ አሰጣጥ ሂደሱ እንዲሳካ የማመቻቸት ስራን እሰራ መሆኑን እንዲሁም የሚደረገውን ድጋፍ እየተቆጣጠረ እንደሆነ ገልጿል።

@tikvahethiopia
#USAID-ኢትዮጵያ ባለው መጋዘን 58 ሺ ሜትሪክ ቶን እህል እንዳለው ሳማንታ ፓወር በትዊተር ገፃቸው አሳውቀዋል።

እህሉ በትግራይ ክልል እንዲሁም በሌሎች የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ዜጎችን ሊመግብ የሚችል ነው ብለዋል።

ፓወር የእርዳታ እህሉ ተረጂዎች ጋር ለማድረስ ምቹ እና ያልተገደበ ሁኔታ ሊፈጠር ይገባል ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

@tikvahethiopia