ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ ወደ አዲስ አበባ ተመልሰዋል!
"ጠቅላይ ሚንስትሩ(ዶ/ር አብይ አህመድ)እና ከሳቸው ጋር ያሉት አባላት በሰላም ወደ ሸገር ተመልሰዋል። የመከላከያ ሰራዊት እስከአሁን ላሰየው እርጋታ ክብር ይገባዋል። ህዝቡም በተቻለ መጠን ሰላማዊ በሆነ መልኩ ለመሪዎቹ ደስተኛ አለመሆኑን በመግለፅ ወደ ድንጋይ ውርወራ አለመግባቱ እና ያደረገውን በሙሉ #በሰላም መድረጉ ያስመሰግነዋል። በአጠቃላይ ነገሮች በሰላም እንዲሆኑ ያደረጉት በሙሉ ክብር ይገባቸዋል። ከዚህ በኃላም ሁሉም ነገር በሰላም እንዲጠናቀቅ አለመዘናጋት ጥሩ ነው።" ዶክተር ደረጄ ገረፋ ቱሉ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ጠቅላይ ሚንስትሩ(ዶ/ር አብይ አህመድ)እና ከሳቸው ጋር ያሉት አባላት በሰላም ወደ ሸገር ተመልሰዋል። የመከላከያ ሰራዊት እስከአሁን ላሰየው እርጋታ ክብር ይገባዋል። ህዝቡም በተቻለ መጠን ሰላማዊ በሆነ መልኩ ለመሪዎቹ ደስተኛ አለመሆኑን በመግለፅ ወደ ድንጋይ ውርወራ አለመግባቱ እና ያደረገውን በሙሉ #በሰላም መድረጉ ያስመሰግነዋል። በአጠቃላይ ነገሮች በሰላም እንዲሆኑ ያደረጉት በሙሉ ክብር ይገባቸዋል። ከዚህ በኃላም ሁሉም ነገር በሰላም እንዲጠናቀቅ አለመዘናጋት ጥሩ ነው።" ዶክተር ደረጄ ገረፋ ቱሉ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአምባሳደር ዲና ሙፍቲ ለውጭ ሀገር ሚዲያዎች የሰጡት መገለጫ ሲዳሰስ !
[በጋዜጠኛ ሰለሞን ሙጬ/DW]
የመግለጫው ዋነኛ ጉዳዮች የነበሩት፦
- የታላቁ ህዳሴ ግድብ ድርድር
- የሱዳን ወረራ እና ያልተገባ ጫና
- 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ
የታላቁ የህዳሴ ግድብን ግንባታ በተመለከተ ግብፅ በውሃ ላይ ምንም አበርክቶ ሳይኖራት እያሳደረች ያለው ጫና ተገቢነት እንደሌለው አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ አሁንም ድርድሩን በአፍሪካ ህብረት ማዕቀፍ ማስቀጠል እንደምትቀጥል አሳውቀዋል።
አምባሳደር ዲና የሁለተኛው ዙር ሙሌት በተያዘለት ጊዜ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
ግብፅና ሱዳን በሙሌቱ ላይ ስምምነት ካልደረሱ ምን ይሆናል ተብለው የተጠየቁ አምባሳደሩ ተከታዩን ምላሽ ነው የሰጡት፦
"በ3ቱ ሀገሮች በ2015 በሱዳን ካርቱም በተፈራረሙት የመርሆች መግለጫ መሰረት የግድቡ ሙሌት የግድቡ የስራ ሂደት አካል ነው። ስለዚህ የውሃ ሙሌቱ የግድቡ አካል ነው። ግድብ ከገነባህ ውሃ መሙላትህ እርግጥ ነው፤ ያ ነው ሊሆን የሚችለው ፤ በመጀመሪያው ዙር የግድቡ ሙሌት የሆነውም ይኸው ነው። አሁንም ተስፋ የምናደርገው በአሞላሉ እና በሂደቱ ላይ እንደምንስማማ ነው።"
የኢትዮ-ሱዳን ድንበር ውዝግብን አስመልክቶ ሱዳን ከሰሞኑ ቤኒሻንጉል ጉምዝ ላይ የባለቤትነት ጥያቄን ማንሳቷን አውግዘዋል።
በተለይ የሱዳን ወታደራዊ ክንፍ የውክልና ተልዕኮ አስፈፃሚነት ውስጥ መግባቱን አሳይቷል ብለዋል።
ኢትዮጵያ ጉዳዩ አሁንም #በሰላም እንዲፈታ ግፊት ማድረጓን ቀጥላለች ብለዋል።
ምርጫ 2013 በተመለከተ አምባሳደር ዲና ፥ ከትላንት ጀምሮ የአውሮፓ ህብረት የባለሞያዎች ቡድን ለመላክ መስማማቱን አሳውቀዋል።
ያንብቡ : telegra.ph/MFA-Ethiopia-05-08
@tikvahethiopia
[በጋዜጠኛ ሰለሞን ሙጬ/DW]
የመግለጫው ዋነኛ ጉዳዮች የነበሩት፦
- የታላቁ ህዳሴ ግድብ ድርድር
- የሱዳን ወረራ እና ያልተገባ ጫና
- 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ
የታላቁ የህዳሴ ግድብን ግንባታ በተመለከተ ግብፅ በውሃ ላይ ምንም አበርክቶ ሳይኖራት እያሳደረች ያለው ጫና ተገቢነት እንደሌለው አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ አሁንም ድርድሩን በአፍሪካ ህብረት ማዕቀፍ ማስቀጠል እንደምትቀጥል አሳውቀዋል።
አምባሳደር ዲና የሁለተኛው ዙር ሙሌት በተያዘለት ጊዜ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
ግብፅና ሱዳን በሙሌቱ ላይ ስምምነት ካልደረሱ ምን ይሆናል ተብለው የተጠየቁ አምባሳደሩ ተከታዩን ምላሽ ነው የሰጡት፦
"በ3ቱ ሀገሮች በ2015 በሱዳን ካርቱም በተፈራረሙት የመርሆች መግለጫ መሰረት የግድቡ ሙሌት የግድቡ የስራ ሂደት አካል ነው። ስለዚህ የውሃ ሙሌቱ የግድቡ አካል ነው። ግድብ ከገነባህ ውሃ መሙላትህ እርግጥ ነው፤ ያ ነው ሊሆን የሚችለው ፤ በመጀመሪያው ዙር የግድቡ ሙሌት የሆነውም ይኸው ነው። አሁንም ተስፋ የምናደርገው በአሞላሉ እና በሂደቱ ላይ እንደምንስማማ ነው።"
የኢትዮ-ሱዳን ድንበር ውዝግብን አስመልክቶ ሱዳን ከሰሞኑ ቤኒሻንጉል ጉምዝ ላይ የባለቤትነት ጥያቄን ማንሳቷን አውግዘዋል።
በተለይ የሱዳን ወታደራዊ ክንፍ የውክልና ተልዕኮ አስፈፃሚነት ውስጥ መግባቱን አሳይቷል ብለዋል።
ኢትዮጵያ ጉዳዩ አሁንም #በሰላም እንዲፈታ ግፊት ማድረጓን ቀጥላለች ብለዋል።
ምርጫ 2013 በተመለከተ አምባሳደር ዲና ፥ ከትላንት ጀምሮ የአውሮፓ ህብረት የባለሞያዎች ቡድን ለመላክ መስማማቱን አሳውቀዋል።
ያንብቡ : telegra.ph/MFA-Ethiopia-05-08
@tikvahethiopia