"... እስራኤል ራሷን ከጥቃት መከላከል መብቷ ነው " - አንቶኒ ብሊንከን
የኤሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን እስራኤል እና ሃማስ ባለፈው ሳምንት ያደረጉትን የተኩስ አቁም ሥምምነት ለማጎልበት ወደመካከለኛው ምስራቅ ይገኛሉ።
ትላንት ማክሰኞ በእየሩሳሌም ጉብኝታቸው፣ እስራኤል ራሷን ከጥቃት መከላከል መብቷ መሆኑን አጥብቀው ሲናገሩ ተደምጠዋል።
ብሊንከን ከእስራኤል ጠ/ሚር ቢኒያሚን ኔታንያሁ ጋር ሆነው በሰጡት መግለጫ በውጊያው እስራኤልም ፍልስጥኤማውያንም ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል ብለዋል።
ለመጻኢው ጊዜ ተስፋ፣ መከባበር እና መተማመንን ለማስፈን ብዙ ሥራ መሰራት ይኖርበታል ሲሉ አሳስበዋል።
ሰው ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች ብዙውን ጊዜ በቁጥር ደረጃ ዝቅ ተደርገው የሚገለጹ ቢሆንም በእያንዳንዷ ቁጥር የሚገለጸው አባት፣ እናት፣ ልጅ፣ አያት፣ ጓደኛ ሰብዓዊ ፍጡር ነው።
ጥንታዊው የአይሁድ ሃይማኖታዊ ህግ እንደሚያስተምረውም፣ ህይወት ሲጠፋ የእስራኤላዊም ይሁን የፍልሥዔማዊ ህይወት መጥፋት ከመላው ዓለም መጥፋት የሚቆጠር ነው ብለዋል።
አሜሪካ ሃማስ በማይጠቀምበት መንገድ ጋዛን መልሶ ለመገንባት ዓለም አቀፍ ድጋፍ ለማሰባሰብ ትሰራለች ሲሉም ተደምጠዋል።
ብሊንከን ፥ በጋዛ እና በዌስት ባንክ ለሚኖሩ ፍልስጤማውያን የኢኮኖሚ ዕድሎችን ለማጎልበት እንሰራለን ሲሉ ቃል የገቡንሲሆን እስራኤልንም ፍልስጥኤሞችንም የሚጠቅም የተረጋጋ ድባብ ሊያመጣ ይችላል ብለዋል።
አንቶኒ ብሊንከን ከፍልስጤም ፕሬዚደንት ማህሙድ አባስ እና ከጠ/ሚ ማሃማድ ሲታዬህ ጋር በራማላህ ተገናኝተው አሜሪካ የምታሰጠውን እርዳታ ይፋ አድርገዋል። #VOA
@tikvahethiopia
የኤሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን እስራኤል እና ሃማስ ባለፈው ሳምንት ያደረጉትን የተኩስ አቁም ሥምምነት ለማጎልበት ወደመካከለኛው ምስራቅ ይገኛሉ።
ትላንት ማክሰኞ በእየሩሳሌም ጉብኝታቸው፣ እስራኤል ራሷን ከጥቃት መከላከል መብቷ መሆኑን አጥብቀው ሲናገሩ ተደምጠዋል።
ብሊንከን ከእስራኤል ጠ/ሚር ቢኒያሚን ኔታንያሁ ጋር ሆነው በሰጡት መግለጫ በውጊያው እስራኤልም ፍልስጥኤማውያንም ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል ብለዋል።
ለመጻኢው ጊዜ ተስፋ፣ መከባበር እና መተማመንን ለማስፈን ብዙ ሥራ መሰራት ይኖርበታል ሲሉ አሳስበዋል።
ሰው ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች ብዙውን ጊዜ በቁጥር ደረጃ ዝቅ ተደርገው የሚገለጹ ቢሆንም በእያንዳንዷ ቁጥር የሚገለጸው አባት፣ እናት፣ ልጅ፣ አያት፣ ጓደኛ ሰብዓዊ ፍጡር ነው።
ጥንታዊው የአይሁድ ሃይማኖታዊ ህግ እንደሚያስተምረውም፣ ህይወት ሲጠፋ የእስራኤላዊም ይሁን የፍልሥዔማዊ ህይወት መጥፋት ከመላው ዓለም መጥፋት የሚቆጠር ነው ብለዋል።
አሜሪካ ሃማስ በማይጠቀምበት መንገድ ጋዛን መልሶ ለመገንባት ዓለም አቀፍ ድጋፍ ለማሰባሰብ ትሰራለች ሲሉም ተደምጠዋል።
ብሊንከን ፥ በጋዛ እና በዌስት ባንክ ለሚኖሩ ፍልስጤማውያን የኢኮኖሚ ዕድሎችን ለማጎልበት እንሰራለን ሲሉ ቃል የገቡንሲሆን እስራኤልንም ፍልስጥኤሞችንም የሚጠቅም የተረጋጋ ድባብ ሊያመጣ ይችላል ብለዋል።
አንቶኒ ብሊንከን ከፍልስጤም ፕሬዚደንት ማህሙድ አባስ እና ከጠ/ሚ ማሃማድ ሲታዬህ ጋር በራማላህ ተገናኝተው አሜሪካ የምታሰጠውን እርዳታ ይፋ አድርገዋል። #VOA
@tikvahethiopia