TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59K photos
1.5K videos
211 files
4.08K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ETH302

ለቦይንግ 737 አውሮፕላን ሰለባዎች ሙት አመት መታሰቢያ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ካህናት ጸሎት አድርገዋል። የአካባቢው ፈረሰኞች ዛሬ ለአመት የዘለቀው ሀዘን የሚያበቃበት ቀን መሆኑን ለማሣወቅ ጥቁር እና ነጭ ሰንደቅ አላማዎችን በመያዘ ተገኝተው ነበር። አባ ገዳዎችም ምስጋና አቅርበዋል።

#EPA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪዎችን የትራንስፖርት ችግር ለመፍታት በተያዘው በጀት ዓመት አንድ ሺ የሚሆኑ የግል ታክሲዎችን ለማስገባት መታቀዱን የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ባለሥልጣን አስታውቋል። በመንግሥት ሦስት ሺ የህዝብ ማመላለሻ አውቶብሶችን ለማስገባት እየተሠራ መሆኑንም ተሰምቷል።

#EPA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ItsMyDam

ኢትዮጵያ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ ያላትን አቋም ለማስረዳት በተለያዩ አገራት ከፍተኛ የልኡካን ቡድን በመላክ ላይ ትገኛለች።

በዚሁ መሰረት በኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ የተመራ ከፍተኛ የልኡካን ቡድን ዛሬ መጋቢት 3 ቀን 2012 ዓም ኬንያ ናይሮቢ በመገኘት ኢትዮጵያ በታላቁ የህዳሴው ግድብ ጋር በተያያዘ ያላትን ግልጽ አቋም ለፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ አስረድቷል።

ሁለቱ መሪዎች ከህዳሴው ግድብ ጋር በተያያዘ ያደረጉትን ውይይት ተከትሎም የጋራ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል።

በፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የሚመራው የልኡካን ቡድን በቀጣይም በሌሎቹ የአባይ ተፋሰስ አገራት ተመሳሳይ ጉብኝት በማድረግ ለአባል አገራቱ መሪዎች የኢትዮጵያን አቋም እንደሚያስረዳ ይጠበቃል።

#EPA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የመርካቶ የአውቶብስ ተርሚናል!

የመርካቶ የአውቶቡስ ተርሚናል ግንባታ በመፋጠን ላይ መሆኑን የትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል። የተርሚናሉ ግንባታ 84 በመቶ ላይ የደረሰ ሲሆን፥ በ2012 በጀት አመት ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ርብርብ በመደረግ ላይ ነው፡፡

የአውቶቡስ ተርሚናሉ የተሳፋሪዎችን ምቾት በመጠበቀ በርካታ አገልግሎቶችን መስጠት ያስችላል፡፡ ተርሚናሉ በአንዴ ለ20 አውቶቡሶች አገልግሎት መስጠት የሚያስችል፤ የራሳቸው መግቢያ እና መውጫ ያላቸው ሁለት ወለሎችን አካቷል፡፡

#EPA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia