ኢቀመማ በትግራይ ክልል ውስጥ በግጭት ለተጎዱ ወገኖች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠሉን አሳውቋል !
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በትግራይ ክልል ተከስቶ በነበረው ግጭት ለተፈናቀሉ እና ጉዳት ለደረሰባቸው 2000 ወገኖች ከብር 3 ሚሊዮን በላይ ወጪ በማድረግ ልዩ ልዩ ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች ድጋፍ አድርጓል፡፡
ማኅበሩ በትግራይ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ካደረገው ድጋፍ መካከል ብርድ ልብስ፣ ምንጣፍ የመመገቢያ እና የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች እና መሠረታዊ መድኃኒት ድጋፍ ይገኝበታል፡፡
ኢቀመማ ግጭቱ ከተከሰተ በኋላ ከዓለም ዓቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ እና ከሌሎች ተባባሪ አካላት ጋር በመሆን ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች አስቸኳይ ሠብዓዊ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል፡፡
ከዚህም መካከል የመጀመሪያ ደረጃ የህክምና እርዳታ ፣ የአምቡላንስ አገልግሎት፣ የተጠፋፉ ቤተሰቦችን የማገናኘት፣ የተለያዩ የምግብ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች ድጋፍ ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
ማኅበሩ በመቀለ ከተማ ተፈጥሮ የነበረውን የንፁህ መጠጥ ውሀ እጥረትን ተከትሎ ለከተማዋ ነዋሪዎች መጠጥ ውሀ ድጋፍ እንደተደረገ ይታወቃል፡፡
(የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር)
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በትግራይ ክልል ተከስቶ በነበረው ግጭት ለተፈናቀሉ እና ጉዳት ለደረሰባቸው 2000 ወገኖች ከብር 3 ሚሊዮን በላይ ወጪ በማድረግ ልዩ ልዩ ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች ድጋፍ አድርጓል፡፡
ማኅበሩ በትግራይ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ካደረገው ድጋፍ መካከል ብርድ ልብስ፣ ምንጣፍ የመመገቢያ እና የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች እና መሠረታዊ መድኃኒት ድጋፍ ይገኝበታል፡፡
ኢቀመማ ግጭቱ ከተከሰተ በኋላ ከዓለም ዓቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ እና ከሌሎች ተባባሪ አካላት ጋር በመሆን ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች አስቸኳይ ሠብዓዊ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል፡፡
ከዚህም መካከል የመጀመሪያ ደረጃ የህክምና እርዳታ ፣ የአምቡላንስ አገልግሎት፣ የተጠፋፉ ቤተሰቦችን የማገናኘት፣ የተለያዩ የምግብ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች ድጋፍ ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
ማኅበሩ በመቀለ ከተማ ተፈጥሮ የነበረውን የንፁህ መጠጥ ውሀ እጥረትን ተከትሎ ለከተማዋ ነዋሪዎች መጠጥ ውሀ ድጋፍ እንደተደረገ ይታወቃል፡፡
(የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር)
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
በአማራ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና እየተሰጠ ነው!
በአማራ ክልል የስምንተኛ ክፍል ክልል ዓቀፍ ፈተና መሰጠት ተጀምሯል።
ፈተናው ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት ይሰጣል፡፡
ፈተናው እየተሰጠ የሚገኘው በ5,162 የፈተና ጣቢያዎች ሲሆን በመደበኛ ፣ የማታ እና የግል ተፈታኞችን ጨምሮ ከ400 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ምንጭ፦ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
በአማራ ክልል የስምንተኛ ክፍል ክልል ዓቀፍ ፈተና መሰጠት ተጀምሯል።
ፈተናው ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት ይሰጣል፡፡
ፈተናው እየተሰጠ የሚገኘው በ5,162 የፈተና ጣቢያዎች ሲሆን በመደበኛ ፣ የማታ እና የግል ተፈታኞችን ጨምሮ ከ400 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ምንጭ፦ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#SurConstruction
የሱር ኮንስትራክሽን ሠራተኞች የሁለት (2) ወር ደምወዝ አልተከፈለንም እንዳልተከፈላቸው ለኢዲስ ማለዳ ጋዜጣ ተናግሩ።
በአዲስ አበባ በሱር ኮንስትራክሽን ዋናው መሥሪያ ቤት የሚሠሩ ሠራተኞች የ2 ወር ደምወዝ እንዳልተከፈላቸው እና ችግር ላይ እንደሆኑ አሳውቀዋል።
በመሥሪያ ቤቱ በተለያየ የኀላፊነት ቦታ የሚሠሩ ሠራተኞች ቅሬታቸውን ሲገልጹ ላለፉት 2 ወራት ምንም ዓይነት ክፍያ ስላልተሰጠን ችግር ውስጥ ወድቀናል ብለዋል።
MORE : https://buff.ly/3mAtTVN
ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ ጋዜጣ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የሱር ኮንስትራክሽን ሠራተኞች የሁለት (2) ወር ደምወዝ አልተከፈለንም እንዳልተከፈላቸው ለኢዲስ ማለዳ ጋዜጣ ተናግሩ።
በአዲስ አበባ በሱር ኮንስትራክሽን ዋናው መሥሪያ ቤት የሚሠሩ ሠራተኞች የ2 ወር ደምወዝ እንዳልተከፈላቸው እና ችግር ላይ እንደሆኑ አሳውቀዋል።
በመሥሪያ ቤቱ በተለያየ የኀላፊነት ቦታ የሚሠሩ ሠራተኞች ቅሬታቸውን ሲገልጹ ላለፉት 2 ወራት ምንም ዓይነት ክፍያ ስላልተሰጠን ችግር ውስጥ ወድቀናል ብለዋል።
MORE : https://buff.ly/3mAtTVN
ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ ጋዜጣ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#Hawassa
የሀዋሳ ከተማ ምክትል ከንቲባ ረ/ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል በደማቅ ሁኔታ ሃይማኖታዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል።
ምክትል ከንቲባው ከወዲሁ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በዓሉን ለመታደም ወደ ሀዋሳ የሚመጡ እንግዶችን ያለምንም የፀጥታ እና ደህንነት ችግር ከተማዋን ጎብኝተው እንዲሄዱ የማድረግ ስራ እንደተሰራ አሳውቀዋል።
ረ/ፕሮፌሰር ፀጋዬ አሁን ላይ ሀዋሳ እጅግ ሰላማዊ፣ የደህንነትና የፀጥታ ችግር የሌለባት ሁሉም ነገር ሰላማዊ የሆነባት ከተማ መሆኗን ገልፀው ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
እንግዶችም ወደ ሀዋሳ ከተማ ሲመጡ ምንም አይነት የደህንነት እና የፀጥታ ችግር ሳይገጥማቸው በተሻለ ሁኔታ እንደሚስተናገዱ ምክትል ከንቲባው ተናግረዋል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የሀዋሳ ከተማ ምክትል ከንቲባ ረ/ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል በደማቅ ሁኔታ ሃይማኖታዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል።
ምክትል ከንቲባው ከወዲሁ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በዓሉን ለመታደም ወደ ሀዋሳ የሚመጡ እንግዶችን ያለምንም የፀጥታ እና ደህንነት ችግር ከተማዋን ጎብኝተው እንዲሄዱ የማድረግ ስራ እንደተሰራ አሳውቀዋል።
ረ/ፕሮፌሰር ፀጋዬ አሁን ላይ ሀዋሳ እጅግ ሰላማዊ፣ የደህንነትና የፀጥታ ችግር የሌለባት ሁሉም ነገር ሰላማዊ የሆነባት ከተማ መሆኗን ገልፀው ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
እንግዶችም ወደ ሀዋሳ ከተማ ሲመጡ ምንም አይነት የደህንነት እና የፀጥታ ችግር ሳይገጥማቸው በተሻለ ሁኔታ እንደሚስተናገዱ ምክትል ከንቲባው ተናግረዋል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
ከፍተኛ ስጋትን የደቀነው አዲሱ የኮቪድ ዝርያ !
በርካታ የአውሮፓ አገራት ብሪታኒያ ላይ የጉዞ እቀባ እያደረጉ ነው።
ለዚህ ምክንያቱ በብሪታኒያ አዲስ ዓይነት የኮቪድ ዝርያ መገኘቱ ነው።
አዲሱ ዝርያ ገና በስፋት ያልተጠና ቢሆንም ከቁጥጥር ውጭ በሆነ መንገድ ከሰው ወደ ሰው ይዛመታል የሚለው ፍርሃት በርካታ አገራትን ድንጋጤ ውስጥ ከቷቸዋል።
እስከ አሁን ጀርመን ፣ አየርላንድ፣ ፈረንሳይ፣ ጣሊያንና ኔዘርላንድስ እና ቤልጂየም ሁሉም ወደ ብሪታኒያ የአየር በረራን አቋርጠዋል።
ዛሬ የአውሮፓ ኅብረት መሪዎች ስብሰባ ስለሚቀመጡ ከዚህ የባሰ የእቀባ ውሳኔ ሊኖር እንደሚችል እየተጠበቀ ነው።
አዲሱ ኮቪድ-19 ዝርያ በለንደንና በደቡብ ምሥራቅ ኢንግላንድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ነው በስፋት የተሰራጨው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ቅዳሜ በሰጡት አስቸኳይ ትእዛዝ ደረጃ 4 የጥንቃቄ ደንቦች እንዲከበሩ አዘዋል።
ለፈረንጆች ገና እና አዲስ ዓመት የእንቅስቃሴ ገደቦች ይላላሉ ተብሎ ታስቦ የነበረውን ሐሳብ ሰርዘዋል።
የጤና ባለሙያዎች አዲሱ የተህዋሲው ዝርያ ይበልጥ ገዳይ ስለመሆኑ ሆነ ለክትባት እጅ የማይሰጥ ስለመሆኑ ገና እርግጠኛ አልሆኑም።
ሆኖም ግን ከለመድነው የኮሮና ቫይረስ በ70 በመቶ በይበልጥ የመሰራጨት አቅም አለው መባሉ ማን ይተርፋል ? እንዲባል አድርጓል።
የብሪታኒያ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ይህ አዲስ ዝርያ ቫይረስ ከቁጥጥር ውጭ ሆኖብናል ፤ በቁጥጥራችን ልናውለው ይገባል ብለዋል።
የዓለም ጤና ድርጅት አዲሱን የኮሮና ቫይረስ ዝርያ በተመለከተ ከዩኬ (UK) ባለሥልጣናት ጋር በቅርበት እየተነጋገረ እንደሆነ አስታውቋል።
ምንጭ፦ ቢቢሲ
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
በርካታ የአውሮፓ አገራት ብሪታኒያ ላይ የጉዞ እቀባ እያደረጉ ነው።
ለዚህ ምክንያቱ በብሪታኒያ አዲስ ዓይነት የኮቪድ ዝርያ መገኘቱ ነው።
አዲሱ ዝርያ ገና በስፋት ያልተጠና ቢሆንም ከቁጥጥር ውጭ በሆነ መንገድ ከሰው ወደ ሰው ይዛመታል የሚለው ፍርሃት በርካታ አገራትን ድንጋጤ ውስጥ ከቷቸዋል።
እስከ አሁን ጀርመን ፣ አየርላንድ፣ ፈረንሳይ፣ ጣሊያንና ኔዘርላንድስ እና ቤልጂየም ሁሉም ወደ ብሪታኒያ የአየር በረራን አቋርጠዋል።
ዛሬ የአውሮፓ ኅብረት መሪዎች ስብሰባ ስለሚቀመጡ ከዚህ የባሰ የእቀባ ውሳኔ ሊኖር እንደሚችል እየተጠበቀ ነው።
አዲሱ ኮቪድ-19 ዝርያ በለንደንና በደቡብ ምሥራቅ ኢንግላንድ በአጭር ጊዜ ውስጥ ነው በስፋት የተሰራጨው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ቅዳሜ በሰጡት አስቸኳይ ትእዛዝ ደረጃ 4 የጥንቃቄ ደንቦች እንዲከበሩ አዘዋል።
ለፈረንጆች ገና እና አዲስ ዓመት የእንቅስቃሴ ገደቦች ይላላሉ ተብሎ ታስቦ የነበረውን ሐሳብ ሰርዘዋል።
የጤና ባለሙያዎች አዲሱ የተህዋሲው ዝርያ ይበልጥ ገዳይ ስለመሆኑ ሆነ ለክትባት እጅ የማይሰጥ ስለመሆኑ ገና እርግጠኛ አልሆኑም።
ሆኖም ግን ከለመድነው የኮሮና ቫይረስ በ70 በመቶ በይበልጥ የመሰራጨት አቅም አለው መባሉ ማን ይተርፋል ? እንዲባል አድርጓል።
የብሪታኒያ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ይህ አዲስ ዝርያ ቫይረስ ከቁጥጥር ውጭ ሆኖብናል ፤ በቁጥጥራችን ልናውለው ይገባል ብለዋል።
የዓለም ጤና ድርጅት አዲሱን የኮሮና ቫይረስ ዝርያ በተመለከተ ከዩኬ (UK) ባለሥልጣናት ጋር በቅርበት እየተነጋገረ እንደሆነ አስታውቋል።
ምንጭ፦ ቢቢሲ
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ከፍተኛ ስጋትን የደቀነው አዲሱ የኮቪድ ዝርያ ! በርካታ የአውሮፓ አገራት ብሪታኒያ ላይ የጉዞ እቀባ እያደረጉ ነው። ለዚህ ምክንያቱ በብሪታኒያ አዲስ ዓይነት የኮቪድ ዝርያ መገኘቱ ነው። አዲሱ ዝርያ ገና በስፋት ያልተጠና ቢሆንም ከቁጥጥር ውጭ በሆነ መንገድ ከሰው ወደ ሰው ይዛመታል የሚለው ፍርሃት በርካታ አገራትን ድንጋጤ ውስጥ ከቷቸዋል። እስከ አሁን ጀርመን ፣ አየርላንድ፣ ፈረንሳይ፣ ጣሊያንና…
#UPDATE
ሳዑዲ አረቢያ በፍጥነት እየተዛመት ነው የተባለውን አዲሱን የኮቪድ ዝርያ በመፍራት ሁሉንም አለም አቀፍ በረራዎች ለጊዜው አግዳለች።
እገዳው ለአንድ (1) ሳምንት ሲሆን ከዚህም ሊራዘም እንደሚችል የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቋል።
የካርጎ በረራዎች ይቀጥላሉ።
ይህ እገዳ ስለአዲሱ የኮቪድ ዝርያ ግልፅ የሆነ የህክምና መረጃ እስኪገኝ ሊቀጥል እንደሚችልም ተጠቁሟል።
የሀገሪቱ የመሬት እና ባህር ወደቦችም ለአንድ ሳምንት ይዘጋሉ ተብሏል።
የሳዑዲ መንግሥት ባለፉት ሶስት ወራት ከአውሮፓ ሀገራት የመጣ ወይም በአውሮፓ ሀገራት በኩል ጉዞ ያደረገ ማንኛውም ሰው በአስቸኳይ የኮቪድ-19 ምርመራ እንዲያደርግ አዟል።
በተመሳሳይ ፦
ኩዌት በረራዎችን አግዳለች ፤ የመሬት እና የባህር ድንበሮቿን ከዛሬ ጀምሮ እስከ Jan 1 (ታህሳስ 23) ዘግታለች።
የካርጎ በረራ ይቀጥላል።
እንዲሁም ኦማን የባህር ፣ አየር፣ የመሬት ድንበሮቿን ከነገ ማክሰኞ ጀምሮ ለአንድ (1) ሳምንት ትዘጋለች።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ሳዑዲ አረቢያ በፍጥነት እየተዛመት ነው የተባለውን አዲሱን የኮቪድ ዝርያ በመፍራት ሁሉንም አለም አቀፍ በረራዎች ለጊዜው አግዳለች።
እገዳው ለአንድ (1) ሳምንት ሲሆን ከዚህም ሊራዘም እንደሚችል የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቋል።
የካርጎ በረራዎች ይቀጥላሉ።
ይህ እገዳ ስለአዲሱ የኮቪድ ዝርያ ግልፅ የሆነ የህክምና መረጃ እስኪገኝ ሊቀጥል እንደሚችልም ተጠቁሟል።
የሀገሪቱ የመሬት እና ባህር ወደቦችም ለአንድ ሳምንት ይዘጋሉ ተብሏል።
የሳዑዲ መንግሥት ባለፉት ሶስት ወራት ከአውሮፓ ሀገራት የመጣ ወይም በአውሮፓ ሀገራት በኩል ጉዞ ያደረገ ማንኛውም ሰው በአስቸኳይ የኮቪድ-19 ምርመራ እንዲያደርግ አዟል።
በተመሳሳይ ፦
ኩዌት በረራዎችን አግዳለች ፤ የመሬት እና የባህር ድንበሮቿን ከዛሬ ጀምሮ እስከ Jan 1 (ታህሳስ 23) ዘግታለች።
የካርጎ በረራ ይቀጥላል።
እንዲሁም ኦማን የባህር ፣ አየር፣ የመሬት ድንበሮቿን ከነገ ማክሰኞ ጀምሮ ለአንድ (1) ሳምንት ትዘጋለች።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ወይዘሮ አዜብ መስፍን ልጃቸው ሰመሓል መለስ በመቐለ ከተማ መታሰሯን ተናገሩ !
(በቢቢሲ የአማርኛው አገልግሎት)
የቀድሞው ጠ/ሚር መለስ ዜናዊ ሴት ልጅ ሰመሐል መለስ ትግራይ መቐለ ውስጥ ተይዛ እንደታሰረች እናቷ ወይዘሮ አዜብ መሰፍን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ወ/ሮ አዜብ ልጃቸው ሰመሐል በምን ምክንያት ለእስር እንደተዳረገች የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ተናገረው ፣ ወደ መቐለ የሄደችው ወታደራዊ ግጭቱ ከመጀመሩ በፊት እንደሆነ ገልጸዋል።
አዲስ አበባ የሚገኙት ወይዘሮ አዜብ ጨምረውም ሰመሐል ወደ መቀለ ያቀናችው በአባቷ የህይወት ታሪክ ላይ የተጻፈ መጽሐፍን ተንተርሶ የተዘጋጀን ቲያትር ለማስመረቅ በርካታ ሰዎች ካሉበት ቡድን ጋር መሆኑን አመልክተዋል።
ሰመሐል "የፖለቲካ አቋም ሊኖራት ይችላል። ነገር ግን የፖለቲካ ፓርቲ አመራርም፣ አባልም፣ ደጋፊም አልነበረችም" ያሉት እናቷ ወ/ሮ አዜብ መስፍን የእስሯ ምክንያት ምን እንደሆነ እንደማያውቁ ተናግረዋል።
ወ/ሮ አዜብ፥ ሰመሐል በየትኛው አካል እንደተያዘችና ምክንያቱ ምን እንደሆነ ከአንዳንድ አካላት ለማወቅ ጥረት ማድረጋቸውን የሚናገሩት ወ/ሮ አዜብ ነገር ግን ምላሽ ለማግኘት እንዳልቻሉ ጠቅሰዋል።
ከሰመሐል በተጨማሪ የጀነራል ኃየሎም አርአያ ልጅ የሆነው ብርሐነመስቀል ኃየሎም በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል።
የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ፕሬስ ሴክሬታሪያት አወል ሱልጣን እና የፌደራል ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጄይላን አብዲን ስለጉዳዩ ቢጠየቁም የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ተናግረዋል።
MORE : https://telegra.ph/BBC-12-21-3
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
(በቢቢሲ የአማርኛው አገልግሎት)
የቀድሞው ጠ/ሚር መለስ ዜናዊ ሴት ልጅ ሰመሐል መለስ ትግራይ መቐለ ውስጥ ተይዛ እንደታሰረች እናቷ ወይዘሮ አዜብ መሰፍን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ወ/ሮ አዜብ ልጃቸው ሰመሐል በምን ምክንያት ለእስር እንደተዳረገች የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ተናገረው ፣ ወደ መቐለ የሄደችው ወታደራዊ ግጭቱ ከመጀመሩ በፊት እንደሆነ ገልጸዋል።
አዲስ አበባ የሚገኙት ወይዘሮ አዜብ ጨምረውም ሰመሐል ወደ መቀለ ያቀናችው በአባቷ የህይወት ታሪክ ላይ የተጻፈ መጽሐፍን ተንተርሶ የተዘጋጀን ቲያትር ለማስመረቅ በርካታ ሰዎች ካሉበት ቡድን ጋር መሆኑን አመልክተዋል።
ሰመሐል "የፖለቲካ አቋም ሊኖራት ይችላል። ነገር ግን የፖለቲካ ፓርቲ አመራርም፣ አባልም፣ ደጋፊም አልነበረችም" ያሉት እናቷ ወ/ሮ አዜብ መስፍን የእስሯ ምክንያት ምን እንደሆነ እንደማያውቁ ተናግረዋል።
ወ/ሮ አዜብ፥ ሰመሐል በየትኛው አካል እንደተያዘችና ምክንያቱ ምን እንደሆነ ከአንዳንድ አካላት ለማወቅ ጥረት ማድረጋቸውን የሚናገሩት ወ/ሮ አዜብ ነገር ግን ምላሽ ለማግኘት እንዳልቻሉ ጠቅሰዋል።
ከሰመሐል በተጨማሪ የጀነራል ኃየሎም አርአያ ልጅ የሆነው ብርሐነመስቀል ኃየሎም በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል።
የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ፕሬስ ሴክሬታሪያት አወል ሱልጣን እና የፌደራል ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጄይላን አብዲን ስለጉዳዩ ቢጠየቁም የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ተናግረዋል።
MORE : https://telegra.ph/BBC-12-21-3
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19Ethiopia
የባለፉት 24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት :
• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ - 4,242
• በበሽታው የተያዙ - 397
• ህይወታቸው ያለፈ - 8
• ከበሽታው ያገገሙ - 701
አጠቃላይ 120,348 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ሲረጋገጥ ፤ የ1,861 ሰዎች ህይወት አልፏል፤ 103,681 ሰዎች ደግሞ ከበሽታው አገግመዋል።
265 ሰዎች በፅኑ ታመው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የባለፉት 24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት :
• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ - 4,242
• በበሽታው የተያዙ - 397
• ህይወታቸው ያለፈ - 8
• ከበሽታው ያገገሙ - 701
አጠቃላይ 120,348 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ሲረጋገጥ ፤ የ1,861 ሰዎች ህይወት አልፏል፤ 103,681 ሰዎች ደግሞ ከበሽታው አገግመዋል።
265 ሰዎች በፅኑ ታመው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#WolaitaSodo ዛሬ ጥዋት በወላይታ ሶዶ "መርካቶ ገበያ" የደረሰው የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ ማለት በሚችል ደረጃ ከፍተኛ ውድመት አድርሷል። አደጋው በበርካታ የንግድ ሱቆች እና ተቋሟት ላይ ውድመት አስከትሏል። ጥዋት የተነሳውን የእሳት አደጋ መቆጣጠር እንደተቻለ የከተማው አስተዳደር ያሳወቀው ከ6:20 በኃላ ነው። እሳቱ ወደ ሌሎች አከባቢዎች እንዳይዛመት የወላይታ ሶዶ ህብረተሰብ ከፍተኛ ርብርብ…
#WolaitaSodo
ትላንት በወላይታ ሶዶ ከተማ 'መርካቶ ገበያ' በደረሰው የእሳት አደጋ ጉዳት የደረሰባቸውን ነጋዴዎች የዞኑ አስተዳደር ከመላው የወላይታ ህዝብ ጋር በመሆን ለመደገፍ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት ዶክተር እንድርያስ ጌታ አሳውቀዋል።
በአደጋው የተጎዱ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋምና ዘላቂ መፍትሔ ለመፍጠር አንድ አቢይ እና የተለያዩ ንዑሳን ኮሚቴዎችን ተቋቁሟል ፤ ከነገ ጀምሮ ወደ ሥራ ይገባል።
የመርካቶ ገበያ መቃጠል የንግዱ ማህበረሰብን ብቻ ሳይሆን በአመዛኙ የሶዶ ከተማ ገቢ የሚመነጨው ከገበያ ማዕከሉ በመሆኑ በከተማይቱ ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።
የትላንቱ የእሳት አደጋ ከባድ በመሆኑ ወደተለያዩ የከተማው ክፍሎች እና አካባቢዎች እንዳይዛመት ፦
- የሐዋሳ ከተማ እሳትና ድንገተኛ አደጋ ማጥፊያ ቡድን፣
- የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር እሳትና ድንገተኛ አደጋ ማጥፊያ ቡድን፣
- የሲዳማ ክልል መንግስት ፣
- የፀጥታ አካላት፣
- የግል ባለሀብቶች እና መላው የወላይታ ሶዶ ነዋሪዎች ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምስጋና ቀርቧል።
ዛሬ የክልል ፣ የዞን እና የወላይታ ሶዶ ከተማ ከፍተኛ አመራሮች በመርካቶ ገበያ የእሳት አደጋው ያደረሰውን ጉዳት ተመልክተዋል።
ወላይታ ሶዶ ከዚህ በፊት አራት ጊዜ እንዲህ አይነት ተመሳሳይ የእሳት አደጋ አስተናግዳለች። የትላንቱ ለአምስተኛ ጊዜ የተከሰተ አደጋ ነው።
ምንጭ፦ የወላይታ ዞን ኮሚኒኬሽን
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ትላንት በወላይታ ሶዶ ከተማ 'መርካቶ ገበያ' በደረሰው የእሳት አደጋ ጉዳት የደረሰባቸውን ነጋዴዎች የዞኑ አስተዳደር ከመላው የወላይታ ህዝብ ጋር በመሆን ለመደገፍ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት ዶክተር እንድርያስ ጌታ አሳውቀዋል።
በአደጋው የተጎዱ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋምና ዘላቂ መፍትሔ ለመፍጠር አንድ አቢይ እና የተለያዩ ንዑሳን ኮሚቴዎችን ተቋቁሟል ፤ ከነገ ጀምሮ ወደ ሥራ ይገባል።
የመርካቶ ገበያ መቃጠል የንግዱ ማህበረሰብን ብቻ ሳይሆን በአመዛኙ የሶዶ ከተማ ገቢ የሚመነጨው ከገበያ ማዕከሉ በመሆኑ በከተማይቱ ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።
የትላንቱ የእሳት አደጋ ከባድ በመሆኑ ወደተለያዩ የከተማው ክፍሎች እና አካባቢዎች እንዳይዛመት ፦
- የሐዋሳ ከተማ እሳትና ድንገተኛ አደጋ ማጥፊያ ቡድን፣
- የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር እሳትና ድንገተኛ አደጋ ማጥፊያ ቡድን፣
- የሲዳማ ክልል መንግስት ፣
- የፀጥታ አካላት፣
- የግል ባለሀብቶች እና መላው የወላይታ ሶዶ ነዋሪዎች ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምስጋና ቀርቧል።
ዛሬ የክልል ፣ የዞን እና የወላይታ ሶዶ ከተማ ከፍተኛ አመራሮች በመርካቶ ገበያ የእሳት አደጋው ያደረሰውን ጉዳት ተመልክተዋል።
ወላይታ ሶዶ ከዚህ በፊት አራት ጊዜ እንዲህ አይነት ተመሳሳይ የእሳት አደጋ አስተናግዳለች። የትላንቱ ለአምስተኛ ጊዜ የተከሰተ አደጋ ነው።
ምንጭ፦ የወላይታ ዞን ኮሚኒኬሽን
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia