TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Guliso

ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ፥ "የጸጥታ አካላት ትላንት ጥቃት ወደተፈጸመበት አካባቢ ተሰማርተዋል ፤ እርምጃም እየወሰዱ ነው" ብለዋል።

በቀጣይም መንግስት የሕዝቡን ደኅንነት የመንግሥትነቱን ሥራ ይሠራል ሲሉ ገልፃዋል።

ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ፥ "ሕዝቡ ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ፣ የጸጥታ አካላት፣ ምሁራንና ሌሎችም መንግሥት ችግሩን ከምንጩ ለማድረቅ የሚወስደውን ርምጃ በመደገፍ የሚጠበቅባቸውን እንዲያደርጉ ጥሪ አቀርባለሁ" ብለዋል።

በሌላ በኩል ፦

ዜጎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በንፁሃን ላይ #ማንነትን መሰረት እያደረገ በሚፈፀመው ተደጋጋሚ ጥቃት ሀዘናቸውን እና ቁጣቸውን እየገለፁ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ መንግስት በየጊዜው ንፁሃን ሞት በኃላ መግለጫ ከማውጣትና አዘንኩ ከማለት በቅድሚያ የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ እንዳለበት በጥብቅ እያሳሳቡ ይገኛሉ።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia