TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#SENEGAL

ሴኔጋል በኮቪድ-19 ምክንያት በውጭ ሃገራት የሞቱ ዜጎቿን አስከሬን መቀበል ጀመረች ፤ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት በሚል የትኛውም አስከሬን ወደ ሃገሯ እንዳይገባ ከልክላ የነበረችው ሴኔጋል ክልከላዋን አንስታለች - #AlAin

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#BorisJhonson

275 የጤና ባለሞያዎች ህይወታቸውን አጥተዋል!

በዩናይትድ ኪንግደም 275 የጤና ባለሙያዎች በኮሮና ቫይረስ (COVID-19) ምክንያት ህይወታቸው አልፏል። ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ኮሮና ቫይረስ በዩናይትድ ኪንግደም 144 የጤና ባለሙያዎችንና 131 የማህበረሰብ ክብካቤ (ሶሻል ወርክ) ሰራተኞችን ህይወት እንደቀጠፈ ገልጸዋል - #AlAin

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የኮሮና ክትባት በአመት ውስጥ እውን ሊሆን ይችላል!

በአውሮፓ ለሚዘጋጁ ክትባቶች ፍቃድ የሚሰጠው የአውሮፓ ህብረት ኤጀንሲ ተስፋ የተጣለበት የኮሮና ቫይረስ #ክትባት በቀጣዩ አንድ (1) ዓመት ውስጥ እውን ሊሆን እንደሚችል አስታውቋል - #AlAin

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
አጫጭር መረጃዎች ፦

- በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክያት የተዘጋው የአሜሪካ እና የካናዳ ድንበር እስከ ሰኔ 14/2012 ዓ/ም ድረስ ተዘግቶ እንደሚቆይ ጠ/ሚ ጀስቲን ትሩዶ ገልፀዋል።

- ብሪታኒያ ሰዎች ራሳቸውን ችለው እንዲገለሉ ከሚያደርጉ የኮሮና ቫይረስ ምልክቶች ዝርዝር ውስጥ ማሽተት አለመቻል ወይም ጣዕም ማጣትን አካታለች - #BBC

- 2ተኛ ቀኑን በያዘው የWHO 73ኛ ዓመታዊ የቪዲዮ ጉባዔ ላይ የተሳተፉ አባል ሃገራት ድርጅቱ /WHO/ እና በስሩ ያሉ ኤጀንሲዎች ለኮሮና ወረርሽኝ የሰጡት ምላሽ በገለልተኛ አካል እንዲጣራ ተስማምተዋል - #AlAin

- የቻይና ሳንቲስቶች ኮቪድ-19ኝን የሚያቆም መድሀኒት አግኝተናል እያሉ ነው። ወረርሽኙን ክትባት ያቆመዋል ተብሎ ይገመት ነበር የሚሉት የቻይና ላብራቶሪ ተመራማሪዎች የኮሮናን ስርጭት በፍጥነት የማቆም ኃይል ያለው መድሀኒት እያዘጋጀን ነው ብለዋል - https://telegra.ph/EthioFM-05-19-2

- በህንድ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ከ100,000 በላይ ሆኗል። የሟቾች ቁጥር ከ3,000 በላይ ሆኖ ተመዝግቧል።

- በብራዚል የኮሮና ቫይረስ እየበረታ ነው፤ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከUK፣ ከጣልያን፣ ከፈረንሳይ በልጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 261,567 ደርሷል።

- በጣልያን ባለፉት 24 ሰዓት 162 ሰዎች ሞተዋል፤ 813 ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።

- በማዳጋስካር ሁለተኛው (2) ሞት በትላትናው ዕለት ምሽት ተመዝግቧል። በሌላ በኩል በሀገሪቱ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 326 ደርሰዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia