TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
214 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዶሃ!

ኮሮና ቫይረስን በተመለከተ ወቅታዊ መረጃዎች፦

- ቀጠር ከህንድ ፣ ፊሊፒንስ ፣ ስሪላንካ ፣ ባንግላዴሽ ፣ ፓኪስታን፣ ቻይና፣ ግብጽ፣ ኢራን፣ ኢራቅ፣ ሌባኖስ፣ ደቡብ ኮሪያ፣ ሶሪያ፣ ኔፓል፣ ታይላንድ በሚነሱ ግለሰቦች ላይ ክልከላ ጥላለች።

- በበሽታው የተጠቁ ግለሰቦች 15 የደረሱ ሲሆን፣ በተለይም በትላንትናው እለት ቫይረሱ ከተገኘባቸው ሶስት ግለሰቦች ጋር ንክኪ ያደረጉ ግለሰቦች እየተፈለጉ አስፈላጊው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑ ተገልጿል።

- የበሽታው ምልክቶች በሚስተዋሉበት ጊዜ 16000 ነጻ የስልክ መስመር ላይ ደውሎ ማሳወቅ፤

- በት/ቤቶች አካባቢ ያለው ስጋት ዝቅተኛ በመሆኑ የመማር ማስተማር ስራው ከከፍተኛ ጥንቃቄ ጋር እንዲቀጥል ተደርጓል። ሆኖም ግን በመንግስት ት/ቤቶች ጠዋት ጠዋት የሚደረጉ ስብሰባዎች እንዲቋረጡ ተወስኗል።

- መወሰድ ያለባቸው ጥንቃቄዎች የመኪና መስኮቶችን መክፈት፣ ከግለሰቦች ጋር በእጅ መጨባበጥን ጨምሮ የሚደረጉ ንክኪዎችን በተቻለ መጠን ማስወገድ፣ እጅን ቢያንስ ለ 20 ሰከንዶች ያክል ደጋግሞ መታጠብ፣ ሲያስሉ እና ሲያስነጥሱ አፍን እና አፍንጫን በክንድዎ መሸፈን፤

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE

የአፋር ክልል ፖሊስ ኮሚሽን 858 የሚሆኑ ለአራት ወር ያሰለጠናቸው የክልል ልዩ ኃይል ሰራዊት አባላት በብር ሸለቆ መደበኛ ሠራዊት ማሰልጠኛ የአፋር ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አሊ ዲኒ በተገኙበት ማስመረቁን ከፌዴራል ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

ዓላማውም በክልሉ የሚካሄደውን 6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ ከማድረግ አንፃር ያለውን የሰው ኃይል እጥረት በመቅረፍ የክልሉንና የህዝቡን ፀጥታ እና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ በመጠበቅ በክልሉ ያለውን የህግ የበላይነት የበለጠ ለማጠናከር ያለመ ነው ተብሏል።

#EBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ ዛሬ ጠዋት የኮሮና ቫይረስን አጠቃላይ ሁኔታ ለመከታተል ከተቋቋመው ቡድን ጋር ተወያይተዋል፡፡

ቡድኑ ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች የተውጣጣ ሲሆን፤ በፌደራል እና በክልል ደረጃ በጤና ሚኒስቴር አማካኝነት እየተመራ ቁልፍ የመከላከልና የቅድመ ዝግጁነት ሥራ በማከናወን ላይ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

መረጋጋት፣ የጤና ሚኒስቴር ያዘጋጀውን የመከላከል መመሪያ ተግባራዊ ማድረግና ማኅበረሰባችን በመከላከልና ቅድመ ዝግጅት ላይ ያለውን ግንዛቤ ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አንስተዋል፡፡

ኮሚቴው ተያያዥ የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ተጽዕኖዎችን በውጤታማነት ለመቋቋም የሚቻልባቸውን አማራጮችም እንደሚያፈላልግ እስካሁን በወሰድናቸው ርምጃዎች እተማመናለሁ ብለዋል ዶ/ር አብይ።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአፍሪካ በኮሮና ቫይረስ የተመዘገበው ሞት!

በግብፅ በኮሮና ቫይረስ ተይዞ ህክምና ሲደረግለት የነበረው ጀርመናዊ ቱሪስት መሞቱና በአፍሪካ አህጉር የመጀመርያው ሆኖ መመዝገቡ ተገልጿል፡፡ የ60 አመቱ ጀርመናዊ ግብፅ በደረሰ ከሳምንት በኋላ ምልክቱ እንደታየበት ተጠቅሷል፡፡

ግለሰቡ በወቅቱ ሬድ ሲ ሪዞርት ሆስፒታል ገብቶ የህክምና ክትትል በማድረግ ላይ እንደነበረ ዘገባው አመልክቷል፡፡ ኤኤፍፒ የዜና ወኪል ጠቅሶ ቢቢሲ እንደዘገበው የአተነፋፈስ ስርዓቱ በአጣዳፊ የሳንባ ምች መጎዳቱን ያሳያል ተብሏል፡፡ በሽተኛው ወደ ገለልተኛ ማቆያ ክፍል መዘዋወር ፈቃደኛ እንዳልሆነ ከገለፀ በኋላ ሊሞት እንደቻለ ተነግሯል፡፡

#BBC #AFP
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#PMOEthiopia

ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት አመራር እና አባላት ጋር ውይይት አድርገዋል። ለሀገራቸው ያላቸው ፍቅር አስደናቂ መሆኑንም ተናግረዋል። አያይዘውም አባላቱ ያላቸውን ሁሉ ለሀገራቸው ለመስጠት ቆራጥ እንደሆኑ መናገራቸውን ነው የተገለፀው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ETHIOPIA

በኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ላይ በልዩ ትኩረት የሚሰሩ ሆስፒታሎችን ማዘጋጀትን ጨምሮ ስርጭቱን ለመቆጣጠር አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ቫይረሱን ለመከላከል የተቋቋመው ብሔራዊ የሚኒስትሮች ኮሚቴ አስታውቋል። በኢትዮጵያ እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰው እንደሌለም ኮሚቴው ገልጿል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የከሸፈው የጠ/ሚር አብደላ ግድያ ሙከራ!

ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሐምዶክ ዛሬ ማለዳ ካርቱም ውስጥ የመግደል ሙከራ ተደርጎባቸው ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምንም ጉዳት እንዳልደረሰባቸውና የተሻለ ጥበቃ ወዳለበት ቦታ መወሰዳቸውን የአገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE

የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ኢጋድ በሱዳን ጠቅላይ ሚንስትር አብደላህ ሀምዶክ ላይ የተቃጣውን የግድያ ሙከራ አውግዟል፡፡ የኢጋድ ዋና ፀሀፊ የሆኑት ዶክተር ወርቅነህ ገበየው በሰጡት መግለጫ በጠቅላይ ሚንስትሩ ላይ የተሞከረው የግድያ ሙከራን አውግዘዋል፡፡

#ኢቢሲ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደህና መሆናቸው አሳውቀዋል!

ዛሬ ጥዋት የግድያ ሙከራ የተደረገባቸው የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላህ ሀምዶክ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በይፋዊ የትዊተር ገፃቸው ላይ ባሰራጩት መልዕክት ደህና መሆናቸውን ለሱዳን ህዝብ ገልፀዋል።

ጠ/ሚር አብደላ ሀምዶክ 'የተፈፀመው ጥቃት ከጀመርነው የሽግግር መንገድ የሚያስቆመን አይደለም፤ ይልቁንም ለሱዳን ለውጥ በርትተን እንድንሰራ ያግዘናል' ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ዶ/ር አብይ አህመድ፦

"በጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ ላይ ዛሬ የተቃጣውን የግድያ ሙከራ አወግዛለሁ። የሱዳን ሕዝብ ሰላሙን ለማስጠበቅ ከፍተኛ ዋጋ ከፍሎ የሚደነቅ ርምጃ ወስዷል። እንዲህ ያሉ ክሥተቶች የሱዳንን መረጋጋትና የለውጥ ጉዞ ሊያደናቅፉ አይገባም።"

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አጫጭር መረጃዎች፦

- በስፔን በ24 ሰዓት ውስጥ 9 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ሞተዋል። በአጠቃላይ በሀገሪቱ በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 26 ደርሰዋል።

- በኢራን በኮሮና ቫይረስ [COVID-19] የሞቱ ሰዎች ቁጥር 237 ደርሰዋል። በ24 ሰዓት ውስጥ የ43 ሰዎች ሞት ሪፖርት ተደርጓል።

- አልባኒያ በሀገሯ የኮሮና ቫይረስ [COVID-19] የተገኘበት ግለሰብ እንደሚገኝ በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጋለች።

- ሳዑዲ አረቢያ ከዚህ ቀጥሎ ወደተዘረዘሩት ሀገራት የሚዲረጉና ከሀገራቱም ወደ ሀገሯ የሚደረጉትን በረራዎች አግዳለች፦ ጣልያን፣ ደቡብ ኮሪያ፣ UAE፣ ኩዌት፣ ባህሬን፣ ሊባኖስ፣ ሶሪያ፣ ግብፅ፣ ኢራቅ!

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አጫጭር መረጃዎች ከአፍሪካ፦

- በግብፅ በኮሮና ቫይረስ [COVID-19] የተያዙ ሰዎች ቁጥር 55 ደርሰዋል። ለሀገሪቱም ለአህጉሪቱም የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ ሞት ዛሬ ተመዝግቧል።

- በናይጄሪያ በኮሮና ቫይረስ [COVID-19] የተጠቃው ሰው ቁጥር ሁለት ሆኗል። ዛሬ በሀገሪቱ በቫይረሱ የተጠቃ ሁለተኛ ሰው እንዳለ ሪፖርት ተደርጓል።

- በቶጎና ቱኒዝያ፣ በኮሮና ቫይረስ የተያዘው ሰው ቁጥር ላይ ለውጥ የለም። ዛሬ አዲስ በቫይረሱ የተገኘበት ሰው ሪፖርት አልተደረገም። ትላንት በሀገራቱ አንድ አንድ ሰው ብቻ በኮሮና ቫይረስ እንደተያዘ አሳውቀናል።

- ካሜሮን እና ሞሮኮ በሀገራቸው ሁለት ሁለት የኮሮና ቫይረስ ኬዞች አሉ፤ በደቡብ አፍሪካ 3፤ በሴኔጋል 4 ሰዎች በቫይረሱ ተጠቅተዋል።

- በአልጄርያ በኮሮና ቫይረስ [COVID-19] የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 20 ደርሰዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

በኢትዮጵያ ምንም የኮሮና ቫይረስ ኬዝ የለም። ከቀናት በፊት የኮሮና ቫይረስ ተመሳሳይ ምልክት የታየባቸውና በለይቶ ማቆያ ክትትል ሲደረግላቸው የነበሩ ሰዎችም ከቫይረሱ ነፃ መሆናቸውን ሰምተናል።

በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ አንድ የበሽታውን ምልክት ያሳየ ግለሰብ በለይቶ ማቆያ ሆኖ የለቦራቶሪ ምርመራ ውጤቱን በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኝም ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሰምተናል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE

UAE ስለሚገኙት እና በኮሮና ቫይረስ እንደተጠቁ ስለተነገረላቸው 2 ሰዎች ከዚህ ቀደም መረጃ መለዋወጣችን ይታወሳል፤ ዛሬ ከሀገሪቱ መንግስት በወጣው መግለጫ ሁለቱም እንዳገገሙ፤ በዳግም ምርመራውም ቫይረሱ እንዳልተገኘባቸው ተሰምቷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ወይዘሮ ነፃነት አስፋው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ!

ከዚህ ቀደም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ረዳት ተጠሪ፣ የኢፌዴሪ የማስታወቂያ ሚኒስትር ዲኤታና በሌሎች የስራ ሀላፊነቶች ላይ የሰሩት በተጨማሪ በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ውስጥ የሰላምና ፀጥታ ዘርፍ ዳይሬክተር በመሆን ያገለገሉት ወይዘሮ ነፃነት አስፋው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰምቷል።

#TPLF #FBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#TikvahFamily

የዓለም ስጋት በሆነው ኮሮና ቫይረስ ምክንያት ሳዑዲ አረቢያ የትምህርት ተቋሞች እንዲዘጉ መወሰኗን በሳዑዲ አረቢያ ነዋሪነታቸውን ያደረጉና በትምህርት ላይ የሚገኙ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት አሳውቀዋል።

በነገራችን ላይ በትናንትናው ዕለት ብቻ በሀገሪቱ በኮሮና ቫይረስ [COVID-19] የተጠቁ 4 ሰዎች ሪፖርት ተደርገዋል ይህም በሀገሪቱ አጠቃላይ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎችን ቁጥር ወደ 15 ሰዎች ከፍ አድርጎታል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ኮቪድ-19 ለመከላከል ምን ማድረግ ይኖርብዎታል?

- ከሚያስነስጥሱ፣ ከሚያስሉ እና ትኩሳት ካለባቸው ሰዎች ጋር ንክኪ አለማድረግ

- እጅዎትን በሳሙናና ውሃ አዘውትረው መታጠብ

- አለመጨባበጥ

- አይን፣ አፍንጫ እና አፍን ባልታጠበ እጅ አለመንካት

#share #ሼር

#ጤናሚኒስቴር
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
149 መንገደኞችንና ስምንት የበረራ ቡድን አባላትን አሳፍሮ፣ ወደ ናይሮቢ ለመብረር፣ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለምቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ከተነሣ ከስድስት ደቂቃ በኋላ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን፣ ጊምቢቹ ወረዳ የተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነው ቦይንግ 737 ማክስ ኤይት ጄት አደጋ ህይወታቸው ላጡ፣ የመታሰቢያ ሥነ ስርዓት ተካሂዷል።

#አሶሼትድፕሬስ #ቪኦኤ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia